አማርኛ (Amharic): Translation Words Print

Updated ? hours ago # views See on WACS

Key Terms

ጸያፍ

  • ርኩስ ወይም የተጠላ ነገርን ለመግላጽ “ጸያፍ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።
  • ግብፃውያን የዕብራውያን ሰዎችን እንደ “ጸያፍ” ይቆጥሩ ነበር። ይህም ማለት ግብጻውያን ዕብራውያንን ይጠሏቸው ነበር፤ከእነርሱ ጋር ለመተባበር ወይም አጠገባቸው ለመሆን አይፈልጉም ነበር ማለት ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ “ለያህዌ ጸያፍ” ከሚላቸው ነገሮች ጥቂቶቹ ውሸት ትዕቢት፣ሰዎችን መስዋዕት አድርጎ ማቅረብ፣ጣዖት ማምለክ፣መግደል፣የዝሙት ኅጢአቶችና ከወንድ ጋር ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን የመሳሰሉት ናቸው።
  • የመጨረሻ ቀኖችን አስመልክቶ ለደቀ መዛሙርቱ ሲያስተምር ኢየሱስ በእግዚአብሔር ላይ በዓመፅ የአምልኮ ቦታውን ለማርከስ ስለማቆመው ትንቢተ ዳንኤል ላይ ያለውን፣ የጥፋት ርኩሰት አመልክቷል።

ልጅነት/ልጅ አድርጎ መቀበል

“ልጅነት” የተሰኘው ቃል አንድን ሰው በተፈጥሮ ወላጆቹ ያልሆኑ ሰዎች ሕጋዊ ልጅ የማድረግ ሂደት ያመለክታል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ “ልጅነት” ወይም “ልጅ አድርጎ መውሰድ” የተሰኙትን ቃሎች እግዚአብሔር ሰዎችን እንዴት የቤተሰብ አካል፣የእርሱ መንፈሳዊ ወንዶችና ሴቶች ልጆች እንደሚያደርግ ለመግለጽ በምሳሌያዊ መልኩ ይጠቀምበታል።
  • ልጆች እንደሆኑ ተቀባይነት በመግኘታቸው አማኞች የእግዚአብሔር ወንዶችና ሴቶች ልጆች መብት ሁሉ ያላቸው ከክርስቶስ ጋር አብሮ ወራሾች ሆነዋል።

ዝሙት፣ዘማዊነት፣ዘማዊ፣ዘማዊት

“ዝሙት” አንድ ያገባ ሰው የትዳር ጓደኛው ካልሆነች ጋር ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን ኃጢአት ያመለክታል። “ዘማዊነት”የዚህ ዐይነት ተግባርን ወይም ይህን ኃጢያት የሚያደርግ ሰው ድትጊት ያመለክታል።

  • አንዳንዴ “ዘማዊት” የሚለው ቃል ዝሙት የፈጸመችው ሴት መሆንዋን ለይቶ ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።
  • ዝሙት ባልና ሚስት በጋብቻ ኪዳን አንዳቸው ለሌላው ያገቡትን ቃል ያፈርሳል።
  • ዝሙት እንዳያደርጉ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዝዟል።
  • ብዙውን ግዜ ዘማዊነት የሚለው ቃል የእስራኤል ሕዝብ ለእግዚአብሔር ታማኝ ያልሆኑበትን በተለይ ደግሞ ሐሰተኛ አማልክትን ያመለከበትን ሁኔታ ለመግለጽ ምሳሌያዊ በሆነ ቋንቋ ጥቅም ላይ ውሏል።

ሁሉን ቻይ

“ሁሉን ቻይ” የሚለው ቃል በቃል “ኃይል ሁሉ የእርሱ የሆነ” ማለት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሉም የሚያመልክተው እግዚኣብሔርን ነው።

  • “ሁሉን ቻይ” ወይም “ሁሉን ቻይ” የሚለው መጠለያ የሚመለከተው እግዚአብሔርን ነው፤ እርሱ በሁሉም ላይ ፍጹም ኅይልና ሥልጣን ያለው መሆኑን ይገለጻል።
  • ይህ ቃል “ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር” ወይም “እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ” ወይም “ሁሉን ቻይ ጌታ” ወይም፣ “ሁሉን ቻይ ጌታ እግዚአብሔር” በተሰኙት መጠሪያዎች እግዚአብሔር ለመግለጽ ጥቅም ላይ ይውላል።

መሠዊያ

መሠዊያ ለእግዚአብሔር መባ(ስጦታ)እንዲሆን እስራኤላውያን እንስሳትና የእህል ዓይነቶችን የሚያቃጥልበት ከፍ ብሎ የሚሠራ ነገር ነው።

  • በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን የቦካ በመካብ ወይም ክምር እስኪሆን ድረስ ድንጋዮችን በመደርደር ቀለል ያሉ መሠዊያዎች ይሠሩ ነበር።
  • ከእንጨት ሳጥን መሰል መሠዊያዎች ይሠሩና በኋላ እንጨቱ ወርቅን፣ናስን ውይም መዳብን በመሳሰሉ ነገሮች ይለበጡ ነበር።
  • እስራኤላውያን በነበሩበት አካባቢ የነበሩት ሕዝቦችም ለአማልክቶቻቸው መዋዕት ማቅረቢያ መሠዊያዎች ይሠሩ ነበር።

አሜን፣በእውነት ይሁን

“አሜን” የሚለውለንድ ሰው የተናገረውን አጽንዖት ለመስጠት ወይም ትኩረት እንዲሰጠው ለማድረግ ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። ኢያሱስ ይህን ቃል ሲናገር ብዙውን ጊዜ አሜን ይሁን እንደ ማለት ነው።

  • ጸሎት መጨረሻ ላይ “አሜን” ከተባለ ከጸሎት ጋር መስማማትን ወይም ጸሎት እንዲፈጽም መፈለግን ያሳያል።
  • በትምህርቱ የተናገረውን ለማስረገጥ ኢየሱስ “አሜን” በሚለው ተጠቅሟል ብዙውን ጊዜ እንዲህ ያደርግ የነበረው ከተናገረው ጋር የሚያያዝ ሌላ ትምህርት ለማቅረብ፣ “እኔ እንዲህ እላችኋለው” በሚልበት ጊዜ ነው።
  • አንዳንድ የእንግሊዝኛ ትርጉሞች ይህን፣ በእውነት ይሁን በማለት ተርጉመውታል ለተወሰነ ነገር አጽንዖት ለመስጠት ይተነገረው ቅን ወይም እውነት መሆኑን ለመግለጥ ጥቅም ላይ ይውላል።

መልአክ፤የመላእክት አለቃ

መልአክ በእግዚአብሔር የተፈጠረ ሃያል መንፈዊ ፍጡር ነው፤መላአኮች የተፈጥጠሩት እርሱ የሚነግራቸውን በማድረግ እግዚአብሔርን እንድያገለግሉ ነው፤የመላክት አለቃ ሌሎች መላአኮችን ሁሉ የሚያዝዝ ወይም የ መልአክን ያመለክታል።

  • ቃል በቃል መልአክ መልክትኛ ማለት ነው፤
  • የመላእክት አለቃ ማለት ዋና መልእክትኛ ማልት ነው፤መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመላዕክቱ አለቃ ተበሎ ሚካኤል ብቻ ነው፤
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው መላእኮች መልክቶችን ከእግዚአብሔር ለሰዎች አድርሰዋል፤እነዚህ መልክቶች እግዚአብሔር ሰዎች ምን እንዲያደርጉ እንደሚፈልግ ለሰዎች መመሪያ መስጠትን ይጨምራል።
  • መላአክቱ ወደ ራት የሚሆኑ ነገሮችን ወይም ቀደም ሲል የሆኑ ነገሮችን በተመለከተም ለሰዎች ተናግረዋል።
  • መላእክቱ የእግዚአብሔር ሥልጣን አላቸው፤የእርሱ ተወካዩች እንደ መሆናቸው መጠን መጽሐፍ ቅድስ ውስጥ አንዳንዴ ልክ እንደ ራሱ እንደ እግዚአብር ተናግርዋል።
  • መላእክት የእግዚአበሔርን የሚያገለግሉት ሌላው መንግድ ሰዎችን በመጠንቅና ሰዎችን በማበረታት ነው፤
  • የያህዌ(የእግዚአብሔር) መልአክ ይ ለየት ያለ ሐርግ ከአንድ በላይ ትርጉም አልው፤1)’’ያህዌን የሚወክል መልአክ ወይም ያህዌን የሚያገለግል መልክተኛ ማለት ሊሆን ይችላል።

ለሰወች ሲናገር በመልአክ ተመስሎ የመጣ ራሱ እግዚአብሔር ሊያመለክት ይችላል፤አንድ መልአክ ያህዌ ራሱ የተናገረ ያህል’’እኔ’’እያለ የተናገረው ለምን እንደ ነበር ከእነዚህ ትርጉሞች አንዱ በቂ ገለጻ ይሰጠን ይሆናል።


መቃባት፤የተቀባ

“መቀባት” የሚለው ቃል ሰውን ወይም አንድን ነገር በ ማሰብ ወይም ላይ ላይ ዘይት ማፍሰስ ማለት ነው፤አንዳንዴ ዘይቱ ከተለዩ ቅመሞች ጋር ስለሚቀላቀል በጣም ጣፋጭ መዕዛ ያለው ሽቶ ይሆናል፤ቃሉ ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ መንፈስ ቅዱስ ሰው መምረጡንና ሃይል ማስታጠቁን ያመለክታል።

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን ለ የእግዚአብሔር እገልግሎት ሰዎችን ለመለየት ካህናት ነገስታትናነቢያት ዘይት ይቀቡ ነበር።
  • እግዚአብሔርን ለማምለክና እርሱን ለማክበር የተለዩ መሆናቻውን ለማሳየት መሠዊያና መገናኛ ድን ዅኑን የመሳሰሉ ነገሮች ዘይት ይቀቡ ነበር፤
  • በአዲስ ኪዳን የተመሙ ሰዎች እንዲፈወሱ ዘይት ይቀቡ ነበር፤እርሱም ማምልከዎን ለማሳየት አንዲት እየሱስን ጥሩ ሽታ ባለው ዘይት እንድ ቅባት አዲስ ኪዳን ሁለት ጊዜ
  • እየሱስ ከሞተ በሃላ ዘይትና ቅመማ ቅመም በመቀባት ወዳጆችቹ ሥ ለቀብር አዘጋጁ፤
  • የዕብራይስጡ መሲሕ እና የግሪኩ ክርስቶስ፥የተቀባ የሚል ትርጉም አላችው፤
  • ነቢይ ሊቀ ካህንና ንጉሥ እንደሆነ፤የተመረጠውና የተቀባው መሲሑ እየሱስ ነው፤

የክርስቶስ ተቃዋሚ

የክርስቶስ ተቃዋሚ የሚለው አገላለጽ እየሱስ ክርስቶስንና ሥራውን የሚቃወም ሰውን ወይም ትምህርትን ነው የሚያመለክተው በዓለም ውስጥ ብዙ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች አሉ።

  • አንድ ሰው እየሱስ መሲሕ አይደለም በማለት ሰዎችን የሚያሳሳትና እርሱ እ ሰውም መሆኑን የሚክድ ሰው ከሆነ ያ ሰው የክርስቶስ ተቃዋሚ መሆኑን ሐዋርያው ዩሐንስ ጵፎአል።
  • የእየሱስ ሥራ የሚቃወም ግልጽ ያልሆነ የክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ በዓለም እንዳለ አዲስ ኪዳን ያስተምራል።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ያለው የዩሐንስ ራእይ በመጨረሻው ዘመን የሚገለጥ የክርስቶስ ተቃዋሚ የሚባል ሰው እንደሚኖር ይናገራል፤ይህ ሰው የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለማጥፋት ይሞክራል ግን በእየሱስ ይሸነፋል።

ሐዋርያ ፣ ሐዋርያነት

ሐዋርያት ስለ እግዚአበሔር ስለ መንግሥቱ ለሰዎች እንዲሰበኩ እየሱስ የላካቸው ሰዎች ነበሩ፤ሐዋርያነት የሚለው ቃል ሐዋርያነት ለመሆን የተመረጡ ሰወች የነበራቸውን ቦታና ስልጣን ያመለክታል።

  • ሐዋርያ የሚለው ቃል ለአንድ ለተለየ ዓላማ የተላከ ማለት ነው፤ሐዋርያ እርሱን የላከው ሥልጣን አለው።
  • ለእየሱስ በጣም ቅርበ የነበሩ አሥራ ሁለት ደቀመዛሙርት የመጀመሪዎቹ ሐዋርያት ሆኑ፤ጻውሎስንና ያዕቆበን የመሳሰሉ ሰዎችም ሐዋርያት ሆነዋል።
  • በእግዚአብሔር ሓይል ሐዋርያት አጋንንት ከሰዎች እንዲወጡ ማዘዝን ጨምሮ በድፍረት ወንጌልን ሰብከዋል፤የታመሙትን ፈውሰዋል።

መሾም፤ይሾም

መሾም እና የተሾመ የተሰኙት ቃላት አንድ የተለየ ተግባርን ወይም ተልኮን እንዲሁም አንድን ሰው መምረጥን ያመለክታል።

  • መሾም እንደ የዘላለም ትይውን የመሳሰሉ ነገሮችን ለመቀብል መመረጥን ያመለክታል፤እንዲህ ማለት የዘላለምን ት

እንዲቀበሉ ተመርጠዋል ማለት ነው።

  • የተወሰነው ጊዜ የሚለው ሐረግ እግዚአብሔር የመረጠውን ጊዜ ወይም አንዳች ነገር እንዲደረግ የታቀደ ጊዜን ያመለክታል።
  • መሾም የሚለው ቃል አንድ ሰው አንዳች ነገርን እንዲያደርግ ማዘዝ ወይም ተልዕኮ መስጠት ማለት ሊሆንም ይችላል።

ታቦት

  • የቃል ኪዳኑ ታቦት፥ የኪዳኑ ሕግ ታቦት፥ የያህዌ (እግዚአብሔር) ታቦት፥ እነዚህ ቃሎች ዐሥሩ ትእዛዞች የተጻፉባቸው ሁለት የድንጋይ ጽላቶች የያዘ በወርቅ የተለበጠ ይተለየ የእንጨት ሳጥን ያመለክታሉ። የአሮን በትርና መና የነበረበትንም ዕቃ ይይዛል።
  • እዚህ ላይ፥ “ታቦት” የሚለው፥ “ሳጥን” ወይም፥ “ሰንዱቅ” ወይም፥ “መያዣ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።
  • በዚህ ሳጥን ወይም ሰንዱቅ ውስጥ ያሉ ነገሮች ለእስራኤላውያን እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር የገባውን ኪዳን ያስታውሷቸዋል።
  • የኪዳኑ ታቦት የሚቀመጠው፥ “ቅድስተ ቅዱሳን” ውስጥ ነበር
  • የእግዚአብሔር ሐልዎት ወይም መገኘት ቅድስት ቅዱስን ውስጥ ካለው ከታቦቱ በላይ ነበር፤ እስራኤላውያንን በተመለከተ ለሙሴ የሚናገረው ከዚያ ነበር
  • የቃል ኪዳኑ ታቦት ቤተ መቅደሱ ውስጥ በነበረው ቅድስተ ቅዱሳን በነበረበት ዘመን በዓመት አንዴ በስርዓት ቀን ወደታቦቱ መቅረብ የሚችል ሊቀ ካህኑ ብቻ ነበር።
  • አንዳንድ ትርጉሞች፥ የኪዳኑ ታቦት የሚለውን ቃል በቃል፥ “የምስክሩ ታቦት” በማለት ተርጉመውታል። ይህ የሚያመለክተው አሥሩ ትእዛዞች እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያደረገው ኪዳን ምስክር ከመሆናቸው አንጻር ነው “ የሕጉ ኪዳን” ተብሎም ተተርጉሟል።

ቤዛነት፥ቤዛ

“ቤዛ” እና “ቤዛነት” ለሰው ልጆች ኃጢአት የሚከፈልና የእርሱን በኃጢአት መቆጣት የሚያበርድ መሥዋዕት እግዚአብሔር ያዘጋጀበትን ሁኔታ ያመለክታል

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን እንስሳን በመግደል ለእስራኤላውያን ኃጢአት የደም መሥውዕትን በማቅረብ ጊዜያዊ ቤዛ እንዲደረግ እግዚአብሔር ፈቅዶ ነበር
  • በአዲስ ኪዳን እንደተጻፈው እውነተኛና ዛላቂ የኃጢአት ቤዛ የክርስቶስ መስቀል ላይ ሞት ብቻ ነው
  • ክርስቶስ የሞት ጊዜ ከኃጢአታቸው የተነሣ ሰዎች ሊቀበሉት ይገባ የነበረውን ቅጣት ወሰደ። በመሥዋዕታዊ ሞቱ የቤዛነት ዋጋ ከፈለ።

የስርየት መክደኛ

“የስርየት መክደኛ” ከወርቅ የተሠራ ጠፍጣፋ ነገር ሲሆን የታቦቱን የላይኛ ክፍል ለመሸፈን ጥቅም ላይ ይውል ነበር። አንዳንድ ትርጉሞች “የስርየት መሸፈኛ” ይሉታል

  • የስርየት መክደኛ 115 ሳንቲሜትር ርዝመትና 70 ሳንቲሜትር ስፋት ነበረው
  • ከስርየት መክደኛው በላይ ክንፎቻቸው እርስ በርስ የተነካኩ ሁለት የወርቅ ኪሩቤል ነበሩ
  • ከስርየት መክደኛው በላይ፥ ከተዘረጉት የኪሩቤል ክንፎች በታች ከእስራኤላውያን ጋር እንደሚገናኝ ያህዌ ተናግሮአል። እንደሕዝቡ ተወካይ ይህን ማድረግ የተፈቀደለት ሊቀ ካህኑ ብቻ ነበር
  • ይህ የስርየት መክደኛ አንዳንዴ፥ “የምሕረት መቀመጫ” ተብሎአል፤ እንዲህ የተባለበት ምክንያት ኃጢአተኛ የሰው ልጆችን ለመዋጀት የሚመጣው የእግዚአብሔር ምሕረት መተለለፊያ ስለሆነ ነው

ሥልጣን

“ሥልጣን” የተሰኘው ቃል አንድ ሰው ሌላው ሰው ላይ ያለውን ተፅዕኖ የማሳደር ወይም የመቆጣጠር ኅይልን ያመለክታል

  • ነገሥታትና ሌሎች ገዦች በሚገዟቸው ሰዎች ላይ ሥልጣን አላቸው
  • “ሥልጣን” የሚለው ቃል ሌሎች ላይ ሥልጣን ያላቸውን ሰዎች፥ መንግስታትና ድርጅቶች ያመለክታል

ማጥመቅ፥ ጥምቀት

አዲስ ኪዳን ውስጥ “ማጥመቅ” እና፥ “ጥምቀት” የተሰኙ ቃሎች ብዙውን ጊዜ ከኃጢአት መንጻቱንና ከክርስቶስ ጋር መተባበሩን ለማሳየት ክርስቲያኑን ውሃ ውስጥ የመንከር ስርዓትን ያመለክታል

  • ከውሃ ጥምቀት በተጨማሪ መጽሐፍ ቅዱስ፥ “በመንፈስ መጠመቅ” እና “በእሳት መጠመቅ” ስለመሳሰሉ ነገሮች ይናገራል
  • በታላቅ መከራ ውስጥ ማለፍን ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፥ “ጥምቀት” የተሰኘውም ቃል ጥቅም ላይ ውሏል

ማመን፥ አመነ፥ እምነት

“ማመን” እና “አመነ” በጣም የተያያዙ ቢሆንም በመጠኑ የሚለያይ ትርጉም አላቸው

  • “ማመን” የሚለው ቃል፥ “እውነት መሆኑን ማወቅ” ወይም፥ “ትክክል መሆኑን ማወቅ” ተብሎ ሊተርጎም ይችላል
  • “አመነ” የሚለው ቃል፥ “ሙሉ በሙሉ መተማመን” ወይም፥ “መተማመንና መታዘዝ” ወይም፥ “በፍጹም ልብ መደገፍና መከተል” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል

የተወደደ

“የተወደደ” በሌላው ሰው የተወደደና ውድ የሆነ ሰውን የሚያሳይ የፍቅር መገለጫ ቃል ነው

  • “የተወደደ” ቃል በቃል፥ “ የሚወደድ ሰው” ወይም፥ “ውድ የሆነ ሰው” ማለት ነው
  • እግዚአብሔር ኢየሱስን፥ “የተወደደ” ወይም፥ “የምወደው ልጄ” ብሎታል
  • ለአብያት ክርስቲያናት በጻፉት መልእክት ሐዋርያት አማኞችን “የተወደዳችሁ” በማለት ይጠሯቸው ነበር

የመወለድ መብት

“የመወለድ መብት” የተሰኘው ቃል ከቤተ ሰቡ የተወለዱ የመጀመሪያ ወንድ ልጅ ያለውን ክብር፣ ከቤተ ሰቡ መጠራትንና ሀብት መወሰድን መደበኛ መብት ያመለክታል።

  • የመጀመሪያው ወንድ ልጅ ያለው የመወለድ መብት ዕጥፍ የአባቱን ሀብት የመውሰድ መብትንም ይጨምራል።
  • የአንድ ንጉሥ የመጀመሪያ ወንድ ልጅ አባቱ ከሞተ በኋላ ሥልጣኑን ወስዶ የመግዛት የመወለድ መብት አለው።
  • ኤሳው ብኵርናውን ወይም የመወለድ መብቱን ለታናሽ ወንድሙ ለያዕቆብ ሸጠ። ከዚህም የትነሣ ከኤሳው ይልቅ ያዕቆብ የመጀመሪያ ልጅ የሚያገኘውን በረከት ወሰደ።
  • የመወለድ መብት በቤተ ሰቡ የዘር ሐረግ ውስጥ የመጀምሪያ ሆኖ የመጠራት ክብርንም ይጨምራል።

ነቀፋ የሌለበት

“ነቀፋ የሌለበት” የሚለው ቃል በቃል፣ “ነውር፣ እንከን” የሌለበት ማለት ነው። በፍጹም ልቡ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝ ሰውን የሚያመለክት ቢሆንም፣ ያ ሰው ምንም ኃጢአት የለበትም ማለት አይደለም።

  • አብርሃምና ኖኅ በእግዚአብሔር ፊት ነቀፋ የሌለባቸው ተብለዋል።
  • “ ነቀፋ የሌለበት” ተብሎ የሚታወቅ ሰው እግዚአብሔርኝ በሚያስከብር መንገድ ይኖራል።
  • አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ እንደሚያመለክተው ነቀፋ የሌለበት ሰው፣ “እግዚአብሔርብ የሚፈራና ከክፋትም የራቀ” ነው።

ስድብ፣ ተሰደበ

መጽሐፍ ቁስ ውስጥ፣ “ስድብ” እግዚአብሔርንና ሰውን በጣም በሚያንቋሽሽ መንገድ መናገርግን ያመለክታል። አንድን ሰው፣ “መስደብ” ሰዎች ሐሰት የሆነ መጥፎ ነገር እንዲያስቡ በዚያ ሰው ላይ ክፉ ነገር መናገር ማለት ነው።

  • ብዙውን ጊዜ እግዚአብሔርን መሳደብ ሲባል እርሱን ማማት ወይም እርሱን በተመለከተ እውነት ያልሆነ ነገርን በመናገር መሳደብን ወይም እርሱን በማያስከብር ሁኔታ ውስጥ መኖርን ያመለክታል።
  • አንድ ሰው እግዚአብሔር ነኝ ቢል ወይም ከአንዱ እውነተኛ አምላክ ሌላ እግዚአብሔር እንዳለ ቢናገር ያ ሰው ተሳድቦአል።
  • አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕሞች ሰዎችን ስለ መሰደብ የሚያመለክት ከሆነ ይህን “ሐሜት” በማለት ተርጕመውታል።

መባረክ፣ ተባረክ፣ በረከት

አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር፣ “መባረክ” በዚያ ሰው ወይም ነገር ላይ መልካምና ጠቃሚ ነገር እንዲሆን ማድረግ ማለት ነው።

  • አንድን ሰው መባረክ በዚያ ሰው ላይ ጠቃሚ እና ቀና ነገር እንዲሆን ምኞትን መግለጽም ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጊዜ አባት ለልጆቹ የበረከት ቃል ይናገር ነበር።
  • ሰዎች እግዚአብሔርን “ሲባርኩ” ወይም እግዚአብሔር እንዲባረክ ምኞታቸውን ሲገልጹ እርሱን እያመሰገኑ ነው ማለት ነው።
  • “መባረክ” የሚለው ቃል ምግብ ከመበላቱ በፊት እንዲቀደስ ወይም ስለዚያ ምግብ እግዚአብሔርን ለማመስገን ጥቅም ላይ ይውላል።

ደም

“ደም” ጉዳት ወይም ቁስል ሲኖር ከአንድ ሰው ቆዳ የሚወጣ ቀይ ፈሳሽ ነገርን ያመለክታል። ደም ለሰው አካል ሕይወት ሰጪ ምግብን ያመጣል።

  • ደም የሕይወት ምሳሌ ነው፤ የደም መፍሰስ የሕይወት መጥፋት ወይም የሞት ምሳሌ ነው።
  • ሰዎች ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ሲያቀርቡ እንስሳ ያርዱና ደሙን መሠዊያው ላይ ያፈስሱ ነበር። ይህም ለሰዎች ኃጢአት ክፍያ እንዲሆን የእንስሳው ሕይወት መሥዋዕት የመሆኑ ምስላ ነበር።
  • በመስቀል ላይ ሞቱ የኢየሱስ ደም ሰዎችን ከኃጢአታቸው የነጻቸዋል፤ ለኃጢአታቸው ይገባቸው የነበረው ቅጣት የመከፈሉ ምሳሌ ነው።
  • “ሥጋና ደም” የሰው ልጆችን የሚመለከት ፈሊጣዊ አንጋገር ነው።
  • “ሥጋና ደም” በዝምድና የተሳሰሩ ሰዎችን የሚመለከት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው።

መመካት፣ ትምክህተኛ

“መመካት” በሰዎች ወይም በነገሮች በመመካት በትዕቢት መናገር ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ስለ አራስ በእብሪት መናገር ማለት ነው።

  • “ትምክህተኛ” ሰው ስለ ራሱ በትዕቢት ይናገራል።
  • በጣዖቶቻቸው በመመካታቸው እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ገሥጾአል። በእውነተኛው አምላክ ይልቅ በግትርነት ጣዖቶቻቸውን እያመለኩ ነበር።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ሀብትን፣ ብርታትን፣ ፍሬያማ እርሻንና ሕጎቻቸውን በመሳሰሉ ነገሮች ስለሚመኩ ሰዎችም ይናገራል። ይህም ማለት እነዚህን ነገሮች የሚሰጥ እግዚአብሔር መሆኑን ከመገንዘብ ይልቅ፣ በእነዚህ ነገሮች ትዕቢት አድሮባቸዋል ማለት ነው።
  • በእነዚህ ነገሮች ከመመካት ወይም ከመታመን ይልቅ እርሱን በማወቃቸው እንዲመኩ እግዚአብሔር አጥብቆ ለእስራኤላውያን ተናግሮአል።
  • ሐዋርያው ጳውሎስ በጌታ ስለ መመካት ይናገራል፤ ይህም ማለት እርሱ ስላደረገላቸው ሁሉ በእርሱ ደስ መሰኘትና እርሱን ማመስገን ማለት ነው።

አካል

“አካል” ቃል በቃል የሰው ወይም የእንስሳ ሥጋ ማለት ነው። ይህ ቃል አንድን ነገር ወይም በአንድ ቡድን ውስጥ ያሉ ግለ ሰቦችን ለማመልከትም ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

  • ቃል በቃል ሲወሰድ “አካል” የሞተ ሰው ወይም እንስሳን ይመለከታል። አንዳንዴ “የሞተ አካል” ወይም፣ “ሬሳ” ያመለክታል።
  • የመጨረዓው የፋሲካ ራት ላይ ኢየሱስ፣ “ይህ ሥጋዬ ነው” በማለት ሲናገር፣ ለኃጢአታቸው ክፍያ ለመሆን. “የሚቆረሰውን” (የሚገደለውን) ሥጋዊ አካሉን ማመልከቱ ነበር።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ክርስቲያኖች እንደ አንድ ቡድን፣ “የክርስቶስ አካል” ተብለው ተጠርተዋል።
  • የሰው አካል ብዙ ክፍሎች እንዳሉት ሁሉ፣ “የክርስቶስ አካል” ብዙ ግለ ሰብ አባሎች አሉት።
  • በአንድነት እግዚአብሔርን ለማገልገልና ለእርሱ ክብር እንዲሆን ለማገዝ እያንዳንዱ አማኝ የክርስቶስ አካል ውስጥ የራሱ የሆነ ተግባር አለው።
  • ኢየሱስ በእርሱ የሚያምኑ ሰዎች፣ “አካል ራስ (መሪ)” ተብሎአል። የአንድ ሰው ራስ አካሉ ምን ማድረግ እንዳለበት እንደሚናገር ሁሉ፣ እንደ “አካሉ” ብልቶች ክርስቲያኖችን የሚመራና አቅጣጫ የሚያስይዝ ኢየሱስ ነው።

ማሰር፣ ማሰሪያ፣ አሰረ

“ማሰር” አንድን ነገር ጥብቅ አድርጎ ማሰር ወይም እንዳይበታተን አድርጎ መቋጠር ማለት ነው። አንድ ነገር የሚያስር ወይም እርስ በርስ የሚያያይዝ፣ “ማሰሪያ” ይባላል።

  • “አሰረ” የሚባለው አንድ ነገር ሲታሰር ወይም ዙሪያውን ሲጠመጠምበት ነው።
  • “ማሰሪያ” ማንኛውንም የሚያስር ነገር ይመለከታል። ብዙውን ጊዜ አንድን ሰው ማሰሪያ ከመንቀሳቀስ የሚያግድ ሰንሰለትን፣ ገመድን፣ ጠፍርን ወይም ሌላ ነገርን ያመለክታል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ገመዶች ወይም ሰንሰለቶች እስረኞችን ከግድግዳ ወይም ከወለል ጋር አጣብቆ ለመያዝ ያገለግሉ ነበር።
  • “ማሰር” የሚለው ቃል ቁስሉ እንዲፈወስ ለመርዳት ቁስሉን በጨርቅ መጠቅለሉን ለመናገር ያገለግል ነበር።
  • የሞተ ሰውን ለቀብር ለማዘጋጀት በጨርቅ “ይታሰር” ወይም ይጠቀለል ነበር።
  • “ማሰሪያ” የሚለው ቃል በምሳሌያዊ አነጋገር አንድ ሰው የሚቆጣጠር ወይም ባርያ የሚያደርግ ኃጢአትን የመሳሰሉ ነገሮችን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውል ነበር።
  • ስሜታዊ፣ መንፈሳዊና አካላዊ በሆነ ሁኔታ ሰዎች እንዲረዳዱ በመካከላቸው ያለው ጥብቅ ግንኙነትም ማሰሪያ ሊባል ይችላል። ይህ በጋብቻ መተሳሰርንም ይመለከታል።
  • ለምሳሌ ባልና ሚስት እርስ በርስ፣ “ተሳስረዋል” ወይም ተጣምረዋል። ይህ እግዚአብሔር እንዲላቀቅ የማይፈልገው ትስስር ወይም ጥምረት ነው።
  • አንድ ሰው በመሐላ “ይታሰራል”፤ ይህም ማለት የገባውን ቃል፣ “የመፈጸም ግዴታ” አለበት ማለት ነው፥

እንደ ገና መወለድ፣ ከእግዚአብሔር መወለድ፣ አዲስ ልደት

ኢየሱስ፣ “እንደ ገና መወለድ” በሚለው ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው እግዚአብሔር አንድን መንፈሳዊ ሙት የሆነ ሰው መንፈሳዊ ሕያው እንዲሆን እንደሚለውጠው ለማመልከት ነበር። “ከእግዚአብሔር መወለድ” ወይም፣ “ከመንፈስ መወለድ” የተሰኙትም ቃሎች አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት የተሰጠውን ሰው ያመለክታሉ።

  • ሰዎች ሁሉ መንፈሳዊ ሙታን ሆነው ተወልደዋል፤ ክርስቶስ እንደ አዳኝ ሲቀበሉ ግን፣ “አዲስ ልደት” ይሰጣቸዋል።
  • አዲስ መንፈሳዊ ልደት በሚሆነበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ አዲሱ አማኝ ውስጥ ለመኖር ይመጣል፤ በሕይወቱ መልካም መንፈሳዊ ፍሬ እንዲያፈራ ኃይል ይሰጠዋል።
  • አንድ ሰው እንደ ገና እንዲወለድና የእግዚአብሔር ልጅ ማድረግ የእግዚአብሔር ሥራ ነው።

ወንድም

ብዙውን ጊዜ ወንድም የሚባለው ቢያንስ ከወላጆች ከአንዱ የተወለደ ወንድ ልጅ ነው።

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን “ወንድም” የሚለው ቃል የአንድ ጎሳ፣ ነገድ አባሎችን ወይም ሰዎችን የመሳሰሉ ዘመዳሞችን የሚያመለክት አጠቃላይ መጠሪያ ነበር።
  • በአዲስ ኪዳን ዘመን ሐዋርያት ወንዶችንም ሆነ ሴቶች አማኞችን ጨምሮ ክርስቲያን ወገኖችን “ወንድም” በማለት ይጠሩ ነበር፤ በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ እግዚአብሔር አባታቸው የሆነ የአንድ መንፈሳዊ ቤተ ሰብ አባሎች ናቸው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ሐዋርያት በተለይ ሴት ስለሆነች ክርስቲያን ሲናገሩ ወይም ወንዶችም ሆነ ሴቶች መካተታቸውን አጽንዖት ለመስጠት ጥቂት ቦታ ላይ፣ “እኅት” በሚል ቃል ተጠቅመዋል። ለምሳሌ ያዕቆብ፣ “ምግብና ልብስ የሌለው ወንድም ወይም እኅት” ሲል እየተናገረ ያለው ስለ አማኞች ሁሉ መሆኑን አጽንዖት ሰጥቷል።

መጥራት፣ ጥሪ፣ ተጠራ፣ መጣራት

“መጥራት” እና “መጣራት” የተሰኙ ቃሎች ቅርብ ላልነበረ ሰው ጮኽ ብሎ አንዳች ነገር መናገር ማለት ነው። ሌሎች ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሏቸው።

  • አንድን ሰው “መጣራት” ሩቅ ላለ ሰው ጮኽ ብሎ መናገር ማለት ሲሆን፣ ርዳታ መጠየቅ፣ በተለይም የእግዚአብሔርን ርዳታ መጠየቅ ማለትም ይሆናል።
  • ብዙውን ጊዜ መጽሕፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መጥራት” ሲባል፣ “ና ማለት” ወይም፣ “እንዲመጣ ማዘዝ” ወይም፣ “እንዲመጣ መጠየቅ” ማለት ነው።
  • ሕዝቡ እንዲሆኑ ወደ እርሱ እንዲመጡ እግዚአብሔር ሰዎችን ይጣራል። ይህ ለእነርሱ፣ “ጥሪ” ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መጠራት” የሚለው ቃል የእርሱ ልጆች እንዲሆኑ፣ በኢየሱስ በኩል የሚገኘውን የመዳን መልእክት የሚናገሩ አገልጋዮቹ እንዲሆኑ እግዚአብሔር ሰዎችን መሾሙን ወይም መምረጡን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
  • ይህ ቃል ለአንድ ሰው ስም ማውጣትን በተመለከተም ጥቅም ላይ ይውላል። “ዮሐንስ ተባለ” ሲባል፣ “ዮሐንስ ተብሎ ተጠራ” ወይም “የእርሱ ስም ዮሐንስ ሆነ” ማለት ነው።
  • “በአንድ ሰው ስም መጠራት” ማለት ለአንድ ሰው የሌላው ሰው ስም ተሰጠው ማለት ነው። እግዚአብሔር ሕዝቡን በራሱ ስም እንደ ጠራ ይናገራል።
  • “በስሜ ጠርቻችኋለሁ” የተሰኘው የተለየ ሐረግ እግዚአብሔር ሰውን በግል በስሙ ያውቀዋል በተለየ ሁኔታም መርጦታል ማለት ነው።

መቶ አለቃ

መቶ አለቃ ከእርሱ ሥር 100 ወታደሮች የነበሩት የሮም ሰራዊት ባለ ሥልጣን ነበር።

  • ይህን፣ “የመቶ ሰዎች መሪ” ወይም፣ “የወታደሮች መሪ” ወይም፣ “መቶ ሰዎች ላይ ኃላፊነት ያለው ባለ ሥልጣን” በማለት መተርጎም ይቻላል።
  • አንድ ሮማዊ ባለ ሥልጣን ወደ ኢየሱስ መጥቶ አገልጋዩን እንዲፈውስለት ለመነው።

ልጆች፣ ልጅ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ልጅ” የሚለው ቃል ሕፃንን ጨምሮ በአጠቃላይ በዕድሜ ወጣት የሆነውን ያመለክታል። “ልጆች” የብዙ ቊጥር ሲሆን፣ ጥቂት ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።

  • አንዳንዴ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ደቀ መዛሙርት ወይም ተከታዮች፣ “ልጆች” በመባል ተጠርተዋል።
  • የአንድን ሰው ዘሮች ለማመልከት፣ “ልጆች” የተሰኘው ቃል ጥቅም ላይ ይውላል።
  • “የ. . .ልጆች” የሚለው ሐረግ የአንድን ነገር ባሕርይ መያዝ ያመለክታል። የሚከተሉት ለዚህ ምሳሌ ይሆናሉ፤
  • የብርሃን ልጆች
  • የመታዘዝ ልጆች
  • የዲያብሎስ ልጆች

ይህ አባባል መንፈሳዊ ልጆች የሆኑ ሰዎችንም ያመለክታል። ለምሳሌ፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” ሲባል በኢየሱስ በማመን የእግዚአብሔር የሆኑ ሰዎችን ያመለክታል።


ክርስቶስ፣ መሲሕ

“መሲሕ” ወይም፣ “ክርስቶስ” የሚለው ቃል፣ “የተቀባ” ማለት ሲሆን፣ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስን ነው የሚያመለክተው።

  • በሕዝቡ ላይ እንደ ንጉሥ እንዲገዛና ከኃጢአትና ከሞት እንዲያድናቸው እግዚአብሔር የሾመውን የእግዚአብሔር ልጅ ለማመልከት አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “መሲሕ” እና “ክርስቶስ” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ ውለዋል፥
  • የብሉይ ኪዳን ነቢያት እርሱ ወደዚህ ምድር ከመምጣቱ በመቶ በሚቆጠሩ ዓመታት በፊት ስለ መሲሑ ትንቢት ጽፈዋል።
  • የሚመጣውን መሲሕ ለማመልከት፣ “የተቀባ” የሚል ትርጕም ያለው ቃል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ተጠቅሷል።
  • ኢየሱስ ከእነዚህ ትንቢቶች ብዙዎችን ፈጸም፤ እርሱ መሲሕ መሆኑን የሚያረጋግጡ ተአምራትንም አደረገ፤ የተቀሩት ትንቢቶች የሚፈጸሙት እርሱ እንደ ገና ሲመለስ ነው።
  • “እርሱ ክርስቶስ” እና፣ “ክርስቶስ ኢየሱስ” ከተሰኙት ቃሎች መመልከት እንደሚቻለው፣ “ክርስቶስ” የሚለው እንደ መጠሪያ ጥቅም ላይ ውሏል።
  • “ኢየሱስ ክርስቶስ” እንደ ተሰኘው፣ “ክርስቶስ” የእርሱም አንድ አካል ሆኗል።

ክርስቲያን

ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከሄደ ጥቂት ጊዜ በኋላ ስዎች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም አወጡ፤ ክርስቲያን የክርቶስ ተከታይ ማለት ነው።

  • የኢየሱስ ተከታዮች ለመጀመሪያ ጊዜ፣ “ክርስቲያኖች” የተባሉት በአንጾኪያ ከተማ ነበር።
  • ክርስቲያን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን የሚያምንና ከኃጢአት እንደሚያድነው በእርሱ የሚተማመን ሰው ነው።
  • በዘመናችን በእውነት የኢየሱስ ተከታይ ባይሆን እንኳ በክርስቲያን ሃይማኖት ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው ክርስቲያን ተብሎ ይጠራል። መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ክርስቲያን” የሚለው እንዲህ ዓይነቱን አይደለም።
  • መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ክርስቲያን” ሲል ሁሌም የሚያመለክተው በእውነት በኢየሱስ የሚያምን ሰውን በመሆኑ፣ ክርስቲያን፣ “አማኝ” በመባልም ይታወቃል።

ቤተ ክርስቲያን

በአዲስ ኪዳን መሠረት ቤተ ክርስቲያን የሚባለው ለመጸለይና የእግዚአብሔር ቃል ሲሰበክ ለመስማት ዘወትር የሚሰበሰቡ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች ስብስብ ነው። “ቤተ ክርስቲያን” ብዙውን ጊዜ፣ ክርስቲያኖችን ሁሉ ያመለክታል።

  • ቃል በቃል የሚያመለክተው ለተለየ ዓላማ በአንድነት የሚሰበሰቡ፣ “ተጠርተው የወጡ” ሰዎችን ጉባኤ ወይም ስብስብን ነው።
  • ቃሉ በክርስቶስ አካል ውስጥ በየትኛውም ቦታ ያሉ አማኞችን ሁሉ ለማመልከት ጥቅም ላይ ሲውል ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ለመለየት አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕሞች በእንግሊዝኛው ቃል መጀመሪያ ላይ ያለውን ፊደል በትልቁ ይጽፋሉ።
  • ብዙውን ጊዜ በአንድ ከተማ ውስጥያሉ አማኞች የሚሰበሰቡት በግለ ሰብ ቤት ውስጥ ነበር። እነዚህ ቤተ ክርስቲያኖች የነበሩበት ከተማ ስም ይሰጣቸው ነበር። ለምሳሌ፣ “የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን” እንደሚለው።

መገረዝ፣ ግዝረት

“መግረዝ” ከወንድ ወይም ወንድ ከሆነ ትንሽ ልጅ ብልት ትርፍ የሆነውን ቆዳ መቊረጥ ማለት ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የግርዘት ሥርዓት ሊኖርም ይችላል።

  • ከእነርሱ ጋር ያደረገው ኪዳን ምልክት እንዶን ቤተ ሰብ ውስጥ ያለ ማንኛውንም ወንድና አገልጋይ እንዲገረዝ እግዚአብሔር አብርሃምን አዝዞት ነበር።
  • ቤተ ሰባቸው ውስጥ የሚወለድ ማንኛውንም ወንድ እንዲገርዙ እግዚአብሔር የአብርሃም ዘሮችንም አዝዞአቸዋል።
  • “የልብ መገረዝ” የሚለው ሐረግ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ከሰው፣ ኃጢአት “መቆረጥን” ወይም፣ “መወገድን” ያመለክታል።
  • በመንፈሳዊ ይዘቱ፣ “የተገረዙ” ማለት በኢየሱስ ክርስቶስ ደም እግዚአብሔር ከኃጢአት ያነጻቸውንና የእርሱ ሕዝብ የሆኑትን ሰዎች ያመለክታል።
  • “ያልተገረዙ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የብልት ሥጋቸው ያልተገረዘ ሰዎችን ነው። ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ በመንፈሳዊ ደረጃ ያልተገረዙትን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት የሌላቸውን ያመለክታል።

ንጽሕ፣ ማንጻት

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ንጹሕ” ምንም ቆሻሻ ወይም እድፍ የሌለበት ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ቅዱስ” እና “ከኃጢአት የነጻ” የሚሉትን ለማመልከት በምሳሌያዊ አነጋገር ጥቅም ላይ ይውላል።

  • “ማንጻት” አንድን ነገር ንጹሕ የማድረግ ሂደት ነው። “ማጠብ” ወይም “ማጽዳት” ተብሎ መተርጎምም ይችላል።
  • በብሉይ ኪዳን ዘመን የትኛው እንስሳ በሥርዓቱ መሠረት “ንጹሕ” የትኛው፣ “ርኵስ” እንደሆነ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ነግሮአቸዋል። ለመብልም ሆነ ለመሥዋዕት የተፈቀዱት ንጹሕ የሆኑ እንስሳት ብቻ ነበሩ። በዚህ ዐውድ መሠረት፣ “ንጹሕ” የተባለው መሥዋዕት እንዲሆን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ እንስሳ ማለት ነው።
  • የቆዳ በሽታ ያለበት ሰው በሽታው ተላላፊ እንዳይሆን ቆዳው እስኪፈወስ ድረስ፣ እንደ ርኵስ ይቆጠር ነበር። ሰውየው እንደገና “ንጹሕ” እንዲባል ከተፈለገ ከቆዳ በሽታ ለመንጻት ሊታዘዛቸው የመገቡ መመሪያዎች ነበሩ።
  • አንዳንዴ፣ “ንጽሕ” የሚለው ቃል ግበረ ገባዊ ንጽሕናን ለማመልከት በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

ማዘዝ፣ ትእዛዝ

ማዘዝ ማለት አንዳች ነገርን እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ለሰዎች መናገር ማለት ነው። ትእዛዝ የሚባለው እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ለሰዎች የተሰጠው መመሪያ ነው።

  • ምንም እንኳ እነዚህ ቃሎች በመሠረቱ ተመሳሳይ ቢሆኑም፣ ብዙውን ጊዜ “ትእዛዝ” የሚለው ቃል የበለጠ መድበኛና ቋሚ የሆኑ የእግዚአብሔርን ትእዛዞች ያመለክታል፤ ለምሳሌ “አሥሩ ትእዛዞች።”
  • አንድ ትእዛዝ አዎንታዊ (ለምሳሌ፣ “ወዳጆችን አክብር”) ወይም አሉታዊ፣ (ለምሳሌ፣ “አትስረቅ”) ሊሆን ይችላል።

ርኅራኄ፣ ርኅሩኅ

“ርኅራኄ” ለሰዎች ማሰብ፣ አተለይም መከራ ለደረሰባቸው ሰዎች እነርሱ ቦታ ሆኖ ስሜታቸውን መጋራትን ያመለክታል። “ርኅሩኅ” ሰው ለሌሎች ሰዎች ያስባል እነርሱንም ይረዳል።

  • ብዙውን ጊዜ፣ “ርኅራኄ” የሚለው ቃል ችግር ውስጥ ላሉ ሰዎች ጥንቃቄ ማድረግንና እነርሱን ለመርዳት አንዳች ነገር ማድረግንም ይጨምራል።
  • እግዚአብሔር ርኅሩኅ መሆኑን ያም ማለት እርሱ ፍቅርንና ምሕረትን የተሞላ እንደ ሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
  • ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ፣ “ርኅራኄን ልበሱ” በማለት ይመክራቸዋል። ለሰዎች የሚያስቡና የሚጠነቀቁ እንዲሆኑና ችግር ውስጥ ያሉትን ለመርዳት ንቁዎች እንዲሆኑ ያስስባቸዋል።

መኮነን፣ ኵነኔ

“መኮነን” እና “ኵነኔ” አንዳች በደል ከመፈጸሙ የተነሣ ሌላው ላይ መፍረድን ያመለክታል።

  • “መኮነን” ካደረገው ጥፋት የተነጃ ያንን ሰው መቅጣትንም ይጨምራል።
  • አንዳንዴ፣ “መኮነን” የሚለው በሐሰት ሰውን መክሰስ ወይም ያልተመጣጠነ ፍርድ መስጠት ማለት ሊሆን ይችላል።
  • “ኵነኔ” ሰውን የመኮነን ወይም የመክሰስ ተግባር ነው።

መመስከር፣ ምስክርነት

መመስከር አንድ ነገር እውነት መሆኑን መቀበል ወይም መናገር ማለት ነው። “ምስክርነት” አንድ ነገር እውነት መሆኑን በቃል ወይም በጽሑፍ በዚያም መስማማት ማለት ነው።

  • “መመስከር”እግዚአብሔርን በተመለከተ በድፍረት እውነቱን መናገርን ያመለክታል። ኃጢአት መሥራታችንን መቀበልንም ያመለክታል።
  • ሰዎች ኃጢአት መሥራታቸውን ሲናዘዙ፣ እግዚአብሔር ይቅር እንደሚላቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
  • አማኞች እርስ በርሳቸው ኃጢአታቸውን ሲናዘዙ መንፈሳዊ ፈውስ እንደሚኖር ሐዋርያው ያዕቆብ በመልእክቱ ጽፎአል።
  • አንድ ቀን ኢየሱስ ጌታ መሆኑን ሰዎች ሁሉ እንደሚመሰክሩ ወይም እንደሚናገሩ ሐዋርያው ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ ሰዎች ጽፎአል።
  • ኢየሱስ ጌታ መሆኑን ካመኑና እግዚአብሔርንም ከሙታን እንዳስነሣው ሰዎች ከመሰከሩ እንደሚድኑ ጳውሎስ ይናገራል።

ኅሊና

ኅሊና አንድ ሰው ኃጢአት እያደረገ መሆኑን እግዚአብሔር ለእርሱ የሚያሳውቅበት የሰውየው አስተሳሰብ አንድ ክፍል ነው።

  • ትክክል የሆነውንና ስሕተት የሆነውን ለይተው ማወቅ እንዲረዳቸው እግዚአብሔር ለሰዎች ኅሊና ሰጥቷል።
  • ለእግዚአብሔር የሚታዘዝ ሰው፣ “ንጹሕ” ወይም፣ “ያልቆሸሸ” ኅሊና አለው ይባላል።
  • አንድ ሰው፣ “ንጹሕ ኅሊና” አለው ከተባለ በውስጡ ምንም የተደበቀ ኃጢአት የለም ማለት ነው።
  • ሰዎች ኅሊናን ችላ ካሉና ኃጢአት ሲያደርጉ በደለኝነት የማይሰማቸው ከሆነ፣ ኃጢአትን በተመለከተ ኅሊናቸው ንቁ አይደለም ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን በጋለ ብረት የመተኮስን ያህል፣ “የደነዘዙ” ኅሊና ይለዋል። እንዲህ ያለው ኅሊና፣ “የሞተ” ወይም፣ “የተበከለ” ሊባል ይችላል።
  • ይህን ቃል፣ “ውስጣዊ ግብረ ገብ መሪ”፣ “ግብረ ገባዊ አስተሳሰብ” ማለት ይቻላል።

መለየት

መለየት አንድን ነገር ወይም ሰው እግዚአብሔርን እንዲያገለግል መመደብ ማለት ነው። በዚህ መልኩ የተለየ ሰው ወይም እቃ ለእግዚአብሔር እንደ ተቀደሰና እንደ ተለየ ይቆጠራል።

  • የዚህ ቃል ትርጕም፣ “መቀደስ” ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ቢሆንም ሥርዓት ባለው መልኩ አንድን ሰው ለእግዚአብሔር አገልግሎት መለየት የሚለውንም ይጨምራል።
  • ለእግዚአብሔር የተለየ ነገሮች የመሥዋዕት እንስሳትን፣ የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበት መሠዊያንና መገናኛው ድንኳንን ወይም ቤተ መቅደሱንም ይጨምራሉ።
  • ለእግዚአብሔር የተለዩ ሰዎች ካህናትን፣ የእስራኤል ሕዝብንና ያደጉ ወንድ ልጆችን ይጨምራል።
  • እንደነጹና በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙ ሰዎችን ወይም ነገሮችን ለእግዚአብሔር አገልግሎት ዝግጁ ማድረግን ከሆነ፣ “መለየት” የሚለው ቃል አንዳንዴ፣ “ማንጻት” ከተሰኘው ጋር ተመሳሳይ ትርጕም ይኖረዋል።

የማእዘን ድንጋይ

“የማእዘን ድንጋይ” የሚለው ሐረግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ተጠርቦ የሕንጻው መሠረት አንድ ጥግ ላይ የሚቀመጥ ትልቅ ድንጋይ ነው።

  • ሌሎች ድንጋዮች ሁሉ የሚለኩትና የሚቀመጡት ከማእዘን ድንጋይ መሠረት ነው።
  • የማእዘን ድንጋይ ሕንፃው በሙሉ ጥንካሬና ዘላቂነት እንዲኖረው በጣም አስፈላጊ ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ “የማእዘን ድንጋይ” ሲባል አማኞች ደግሞ ሕያዋን ድንጋዮች ተብለዋል።
  • የማእዘን ድንጋይ ሕንፃውን ደግፎ እንደሚይዝና የሕንፃውን ትክክለኛነት እንደሚወሰን ሁሉ አማኞች የተመሠረቱትና የተደገፉት ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነው።

ኪዳን

ኪዳን አንዱ ወይም ሁለቱም የሚፈጽሙት በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ መደበኛ አሳሪ ስምምነት ነው።

  • ስምምነቱ በሁለት ግለ ሰቦች፣ ሕዝቦች፣ ወይም በእግዚአብሔርና በሕዝብ መካከል ሊደረግ
  • ሰዎች እርስ በርስ ኪዳን ካደረጉ አንድ ነገር ለማድረግ ቃል ይገባሉ፤ ያንንም ማድረግ አለባቸው።
  • በሰዎች መካከል ለሚደረግ ኪዳን ምሳሌ የሚሆኑን የጋብቻ ኪዳን፣ የሥራ ስምምነትና በአገሮች መካከል የሚደረጉ ውሎች ናቸው ።
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር በርካታ ኪዳኖች አድርጎ ነበር።
  • በአንዳንድ ኪዳኖች ውስጥ የእርሱን ድርሻ ለመፈጸም እግዚአብሔር ቃል የገባው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነበር። ለምሳሌ ዓለምን ሁሉ በማያዳርስ ጎርፍ ከእንግዲህ ምድርን እንደማያጠፋ እግዚአብሔር ቃል ከሰው ልጅ ጋር ኪዳን ያደረገው ሰው ማሟላት የነበረበት ምንም ቅድመ ሁኔታ ሳይኖር ነው።
  • በሌሎች ኪዳኖች የእርሱን ድርሻ እንደሚፈጽም እግዚአብሔር ቃል የገባው ሰዎች ከታዘዙትና የኪዳኑን የእነርሱን ድርሻ ከፈጸሙ ብቻ ነበር።

ለኪዳኑ ታማኝ፣ ለኪዳኑ እውነተኛ

ይህ አገላለጽ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለሕዝቡ የሰጠውን ተስፋ ለመፈጸም ታማኝ መሆኑን ነው።

  • “ኪዳን” በተሰኘ ውል ያለው ስምምነት መሠረት እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን እግዚአብሔር ተስፋ ሰጠ።
  • ያህዌ፣ “ለኪዳኑ ታማኝ” ወይም፣ “ለኪዳኑ እውነተኛ” መሆኑ የሚያመለክተው እርሱ ለሕዝቡ የገባውን ቃል የሚጠብቅ መሆኑን ነው።
  • የኪዳኑን ተስፋ ለመጠበቅ እግዚአብሔር ታማኝ መሆኑ እርሱ ለሕዝቡ ያለው ተስፋ መገለጫ ነው።
  • “እውነተኛ” የሚለው የሰጠውን ተስፋ ለመፈጸም ታማኝና መሆኑን የሚያመለክት ሌላ ቃል ነው።

መስቀል

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን መስቀል አንድ ቀጥ ብሎ የወጣ እንጨት ሲሆን ጫፉ አካባቢ አንድ ሌላ ግንድ ይጋደምበት ነበር።

  • በሮም መንግሥታት ዘመን አንድ ሮማዊ ባለ ሥልጣን መስቀል ላይ በመቸንከር ወይም መስቀል ላይ በማሰርና እዚያ እንዲሞቱ በማድረግ ወንጀለኞችን ይቀጣ ነበር።
  • ኢየሱስ ባልፈጸመው ወንጀል በሐሰት ተከሰሰ፤ ሮማውያንም መስቀል ላይ ገደሉት።

መስቀል (ሰውን)

“መስቀል” ማለት አንድን ሰው መስቀል ላይ ማሰርና በታላቅ ሕመምና ስቃይ እስኪሞት ድረስ እዚያው መተው ማለት ነው።

  • የሚሰቀለው ሰው መስቀሉ ላይ ይታሰር ወይም ይቸነከር ነበር። በዚህ መልኩ የሚሰቀሉ ሰዎች በከባድ ደም መፍሰስ ወይም በመታረን ይሞቱ ነበር።
  • አደገኛ ወንጀለኞችን ወይም በሮም መንግሥት ላይ ያመፁ ሰዎችን ለመግደል ሮማውያን በእንደዚህ ዐይነቱ ቅጣት ይጠቀሙ ነበር።
  • የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ኢየሱስን እንዲሰቅሉ ወታደሮቹ እንዲያዝ ሮማውያን ባለ ሥልጣን ጠየቁ። ወታደሮቹ ኢየሱስን መስቀል ላይ ቸነከሩ። እኢያ ላይ ስድስት ሰዓት ያህል ተሰቃይቶ ሞተ።

መርገም፣ የተረገመ

“መርገም” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ላይ መጥፎ ነገር እንዲደርስበት ማድረግ ነው።

  • አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ላይ ጉዳት እንዲደርስ መናገር መርገም ነው።
  • ሰውን መርገም እዚያ ሰው ላይ መጥፎ ነገር እንዲደርስበት የመፈለግ መገለጫ ሊሆን ይችላል።
  • ቅጣትን አንድ ሰው ሌላው ላይ የሚያደርሰው ሌላ አሉታዊ ነገርን ሊያመለክትም ይችላል።

የጽዮን ሴት ልጅ

የጽዮን ሴት ልጅ የእስራኤልን ሕዝብ የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው። ብዙውን ጊዜ ትንቢት ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “ጽዮን” የኢየሩሳሌም ከተማ ሌላ ስም ነበር።
  • “ጽዮን” እና፣ “ኢየሩሳሌም” እስራኤልን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላሉ።
  • “ሴት ልጅ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ውድ ምሆንን ወይም ፍቅርን የሚያመለክት ሐረግ ነው። እግዚአብሔር ለሕዝቡ ላለው ትዕግሥትና ጥንቃቄ ተለዋጭ ዘይቤ ነው።

የጌታ ቀን፣ ይያህዌ ቀን

“የያህዌ ቀን” የተሰኘው የብሉይ ኪዳን አገላለጽ ከኀጢአታቸው የተነሣ እግዚአብሔር ሕዝቡን የሚቀጣበትን የተለየ ቀን ወይም ቀኖች ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል።

  • “የጌታ ቀን” የሚለው የአዲስ ኪዳን አገላለጽ ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው በመጨረሻው ቀን ጌታ ኢየሱስ በሰዎች ለመፍረድ ተመልሶ የሚመጣበትን ቀን ነው።
  • ይህ ወደ ፊት የሚመጣው የመጨረሻ ፍርድና ትንሣኤ አንዳንድ ጊዜ፣ “የመጨረሻው ቀን” ተብሎ ይጠራል። ይህ ጊዜ የሚጀምረው በኀጢአተኞች ለመፍረድና ለዘላለም መንግሥቱን ለመምሥረት ጌታ ኢየሱስ ሲመታ ነው።
  • እነዚህ ሐረጎች ውስጥ፣ “ቀን” የሚለው ቃል አንዳንዴ ቃል በቃል “ጊዜን” ወይም ከቀን የረዘመ “ወቅትን” ሊያመለክት ይችላል።
  • የቅጣቱ ቀን አንዳንዴ፣ “የእግዚአብሔር ቍጣ መፍሰስ” ተብሎ ይጠራል።

ዲያቆን

ዲያቆን ምግብን ወይም ገንዘብን በመሳሰሉ ተግባራዊ ነገሮች አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉትን በመርዳት የሚያገለግል ሰው ነው።

  • “ዲያቆን” የሚለው ቃል በቀጥታ የተወሰደው “ባርያ” ወይም “አገልጋይ” የሚል ትርጕም ካለው ግሪክ ቃል ነው።
  • የጥንት ክርስቲያኖች ከነበሩበት ዘመን ጀምሮ ዲያቆን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁነኛ ድርሻ ያለው የአገልግሎት ዘርፍ ነው።
  • ለምሳሌ ከአዲስ ኪዳን እንደምንመለከተው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ላሉ መበለቶችና ድኾች ገንዘብና ምግብ በአግባቡ መዳረሱን የሚያጣሩ ዲያቆናት ነበሩ።
  • “ዲያቆን” የተሰኘው ቃል፣ “የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ” ወይም፣ “የቤተ ክርስቲያን ሠራተኛ” ተብሎ ሊተረጎም ወይም የአጥቢያው ክርስቲያን ማኅበረ ሰብን የሚጠቅም ተግባር እንዲፈጽም በሥርዐት መሾምን በሚያሳይ ሌላ ሐረግ ወይም ቃል መጠቀም ይችላል።

ጋኔን፣ ክፉ መንፈስ፣ ርኵሳን መናፍስት

እነዚህ ሁሉ የሚያመለክቱት አጋንንትን ሲሆን፣ አጋንንት የእግዚአብሔርን ፈቀድ የሚቀወሙ መንፈሳዊ ፍጥረቶች ናቸው።

  • እርሱን እንዲያገለግሉ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጠረ። ዲያብሎስ በእግዚአብሔር ላይ ሲያምጽ ከመላእክቱም ጥቂቶቹ በማመጻቸው ከሰማይ ተጣሉ። አጋንንትና ክፉ መናፍስት፣ “እነዚህ የተጣሉ” መላእክት እንደ ሆኑ ይታሰባል።
  • እነዚህ አጋንንት አንዳንዴ፣ “ርኵሳን መናፍስት” ተብለው ይጠራሉ። “ርኵስ” “ንጹሕ ያልሆነ” ወይም፣ “ክፉ” ወይም፣ “ቅዱስ ያልሆነ” ማለት ነው።
  • አጋንንት የሚያገለግሉት ዲያብሎስን ስለ ሆነ ክፉ ነገር ያደርጋሉ። አንዳንድ ጊዜ እነርሱ ውስጥ በመግባት ሰዎችን ይቆጣጠራሉ።
  • አጋንንት ከሰው የበለጠ ብርቱ ቢሆኑም፣ የእግዚአብሔርን ያህል ግን ብርቱ አይደሉም።

አጋንንት ያደሩበት

አጋንንት ያደሩበት ሰው የሚያደርገውንና የሚያስበውን የሚቆጣጠሩ አጋንንት ወይም ክፉ መናፍሳት ውስጥ ይኖራሉ።

  • አጋንንት ያደሩበት ሰው ብዙ ጊዜ ራሱን ወይም ሌሎችን ይጎዳል፤ እንደዚያ የሚያስደርጉት ውስጡ ያሉት አጋንንት ናቸው።
  • ከውስጣቸው አጋንንቱ እንዲወጡ በማዘዝ ኢየሱስ አጋንንት ያደሩባቸው ሰዎችን ነጻ አውጥቶአል። ብዙ ጊዜ ይህ፣ “አጋንንትን ማስወጣት” የሚባለው ነው።

ደቀ መዝሙር

“ደቀ መዝሙር” በቃልም ሆነ በሕይወት ምሳሌነት ከመምህሩ ለመማር ሲል ብዙ ጊዜውን ከመምህሩ ጋር የሚያሳልፍ ሰው ነው።

  • ትምህርቱን በመስማትና ለእርሱ በመታዘዝ በየሄደበት ሁሉ ኢየሱስን የሚከተሉ ሰዎች፣ “ደቀ መዛሙርት” ይባላሉ።
  • መጥምቁ ዮሐንስም የራሱ ደቀ መዛሙርት ነበሩት።
  • ኢየሱስ በዚህ ምድር ባገለገለበት ዘመን እርሱን የተከተለና ትምህርቶቹን ያደመጡ ብዙ ደቀ መዛሙርት ነበሩት።
  • የቅርብ ተከታዮቹ እንዲሆኑ ኢየሱስ አሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት መረጠ፤ እነዚህም የእርሱ “ሐዋርያት” የተባሉት ናቸው።
  • አሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት፣ “ደቀ መዛሙርት” ወይም፣ “አሥራ ሁለቱ” በሚል ስያሜ መጠራታቸው ቀጥሎአል።
  • ወደ ሰማይ ከመሄዱ ጥቂት ቀደም ሲል የእርሱ ደቀ መዛሙርት እንዲሆኑ ሌሎች ሰዎችን እንዲያስተምሩ ኢየሱስ ደቀ መዝሙርቱን አዝዞአል።
  • በኢየሱስ የሚያምንና ለእርሱ ትምህርት የሚታዘዝ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ይባላል።

ሥርዓት፥ ራስን መግዛት ወይም ራስን በሥርዓት መምራት

“ሥርዓት” ለተወሰኑ ግብረ ገባዊ መመሪያዎች እንዲታዘዙ ሰዎችን መሠልጠንን ነው የሚያመለክተው።

  • ግብረ ገባዊ መመሪያዎችንና አቅጣጫዎችን በመስጠትና እንዲታዘዙ በማስተማር ወላጆች ልጆቻቸውን ሥርዓት ያስይዛሉ።
  • በተመሳሳይ መንገድ ጤናማ መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖራቸውና እንደ ደስታ፣ ትዕግሥትን የመሳሰሉ ፍሬዎች እንዲያፈሩ እግዚአብሔርም ልጆቹን ሥርዓት ያስይዛል።
  • ሥርዓት ሲባል እግዚአብሔርን እንዴት ደስ ማሰኘት እንደሚቻል መመሪያን እንደሚያመለክት ሁሉ፣ ከእርሱ ፈቀድ ውጪ የሆኑትን መቅጣትንም ያካትታል።

መለኮት

መለኮት የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር የሆነ ማንኛውንም ነገር ይመለከታል። ይህ ቃል ጥቅም ላይ ከሚውልባቸው መንገዶች ጥቂቶቹ “መለኮታዊ ሥልጣን”፣ “መለኮታዊ ፍርድ”፣ “መለኮታዊ ባሕርይ”፣ “መለኮታዊ ኃይል” እና፣ “መለኮታዊ ክብር የተሰኙት ናቸው።


ግዛት

ግዛት ሰዎችን፣ እንስሳትንና መሬትን የመቆጣጠር፣ የመግዛት ኃይልና ሥልጣንን ያመለክታል።

  • ነቢይ፣ ካህንና ንጉሥ በመሆኑ ኢየሱስ ክርስቶስ ምድርን ሁሉ እንደሚገዛ ተነግሮአል።
  • በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ላይ ሞት የሰይጣን ግዛት ለዘላለም ተሸንፎአል።
  • በፍጥረት ጊዜ ሰው የባሕር ዓሦችን፣ በአየር የሚበሩ ወፎችንና ምድር ላይ የሚኖሩ ፍጥረቶችን ሁሉ እንዲገዛ እግዚአብሔር ተናገረ።

የተመረጠ፣ የተመረጠ ሕዝብ፣ የተመረጠው፣ ምርጦች

“የተመረጠ” ወይም፣ “ምርጦች” የሚለው ቃል በቃል፣ “የተመረጡት” ወይም፣ “የተመረጠ ሕዝብ” ማለት ሲሆን አባባሉ የእርሱ ሕዝብ እንደሆኑ እግዚአብሔር የመደባቸውን ወይም የመረጣቸውን ያመልክታል። “የተመረጡ” ወይም፣ “በእግዚአብሔር የተመረጠው፣ የተመረጠ መሲሕ የሆነው የኢየሱስ መጠሪያ ነው።

  • እግዚአብሔር እንዲቀደሱ፣ መልካም መንፈሳዊ ፍሬ እንዲያፈሩ እግዚአብሔር ሰዎችን መረጠ። “የተመረጠ” የሚለው ቃል የሕዝቡ መሪ እንዲሆኑ እግዚአብሔር የመደባቸውን ሙሴንና ንጉሥ ዳዊትን የመሳሰሉ ሰዎች ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል። እንደ እግዚአብሔር የተመረጠ ሕዝብ የእስራኤልን ሕዝብም ያመለክታል።
  • “ምርጦች” የተሰኘው ጥንታዊ ሐረግ ቃል በቃል፣ “የተመረጡት” ወይም፣ “የተመረጠ ሕዝብ” ማለት ነው።

ኤፉድ

ኤፉድ እስራኤላውያን ካህናት ይለብሱት የነበረ መጎናጸፊያ ዐይነት ጨርቅ ነው። ትከሻ ላይ የሚገናኙ የፊትና የኋላ የሚባሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት፤ ከዚያም በጨርቅ መታጠቂያ ወገብ ላይ ይታሰር ነበር።

  • አንዱ አይነት ኤፉድ ከተራ ተልባ እግር የሚሠራ ሲሆን፣ የሚለብሱትም ተራ ካህናት ነበሩ።
  • ሊቀ ካህኑ የሚለብሰው ኤፉድ በወርቅ ያጌጠና በሰማያዊ፣ ሐምራዊና ቀይ ጥልፍ የተሠራ ነበር።
  • የሊቀ ካህኑ ደረት ልብስ ከኤፉዱ ፉት ለፊት አካል ጋር ይያያዛል፣ ከደረት ልብሱ በስተጀርባ አንድን ጉዳይ አመልክቶ የእርሱ ፈቃድ ምን እንደሆነ የሚጠይቅባቸው የከበሩ ድንጋዮች ኡሪምና ቱሚም ይቀመጣሉ።
  • መሳፍንቱ ጌዴዎን በስሕተት ከወርቅ የሠራውን ኤፉድ እስራኤላውያን እንደ ጣዖት ሲያመልኩት ነበር።

ዘላለም፣ ዘላለማዊ

“ዘላለም” እና “ዘላለማዊ” በጣም ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆን፣ የሚያመለክቱት ሁሌም የሚኖር ወይም ማለቂያ ማብቂያ የሌለውን ነገር ወይም ሁኔታ ነው።

  • “ዘላለም” ጅማሬም ሆነ ፍጻሜ የሌለውን ሁኔታ ያመለክታል። ማለቂያ፣ ማብቂያ የሌለው ሕይወትንም ያመለክታል።
  • ከዚህ የአሁን ሕይወት በኋላ የሰው ልጆች በመንግሥተ ሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር ወይም ከእግዚአብሔር ተለይተው በገሃነም ዘላለምን ያሳልፋሉ።
  • ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም በመንግሥተ ሰማይ መኖርን ለማመልከት አዲስ ኪዳን ውስጥ “ዘላለማዊ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።
  • “ከዘላለም እስከ ዘላለም” የሚለው ሐረግ ማለቂያ የሌለውን ጊዜ የሚያመለክት ሲሆን፣ ዘላለም ወይም የዘላለም ሕይወት ምን ማለት መሆኑን ይገልጻል።

ጃንደረባ

ብዙ ጊዜ፣ “ጃንደረባ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተኮላሸ ወንድን ነው በኋላ ግን ቃሉ አካላዊ ጉድለት ባይኖርባቸውም በአጠቃላይ ማንኛውንም የመንግሥት ባለሥልጣን የሚያመለክት ሆነ።

  • ብልታቸው በመጎዳቱ ወይም የግብረሥጋ ግንኙነት ማድረግ ባለመቻሉ፣ አንዳንዶች ጃንደረባ ሆነው እንደሚወለዱ ኢየሱስ ተናግሯል። አንዳንዶች ደግሞ በድንግልና እንደጃንደረባ መኖርን መርጠዋል።
  • በጥንት ዘመን ጃንደረቦች ብዙ ጊዜ የነገሥታቱን ሴቶች እንዲጠብቁ ቤተመንግሥት ውስጥ ያገለግሉ ነበር (ከነአስቴር ታሪክ መመልከት ይቻላል)
  • አንዳንድ ጃንደረቦች ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣኖች ነበሩ፤ ይህን በአዲስ ኪዳን ከተጠቀሰው ፊልጶስ ወንጌል ከሰበከለት ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ማየት ይቻላል።

ወንጌላዊ

“ወንጌላዊ” የኢየሱስ ክርስቶስን የምሥራች(ወንጌል) ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው።

  • የ “ወንጌላዊ” ቃል በቃል ትርጉም፣ “የኢየሱስ ክርስቶስን የምሥራች የሚሰብክ ሰው ማለት ነው።”
  • በኢየሱስና መስቀል ላይ በከፈለው የኀጢአት መሥዋዕት በማመን የእግዚአብሔር መንግሥት አካል እንደሚሆኑ ለሰዎች የምሥራቹን እንዲናገሩ ኢየሱስ አሥራ ሁለቱን ሐዋርያት ላከ።
  • ክርስቲያኖች ሁሉ ይህን የምሥራች እንዲያካፍሉ ተነግሯቸዋል።
  • አንዳንድ ክርስቲያኖች ውጤታማ በሆነ ሁኔታ ወንጌልን ለሌሎች የማካፈል ልዩ መንፈሳዊ ስጦታ ታድለዋል። እንዲህ ያሉ ሰዎች ወንጌል የማዳረስ ስጦታ አላቸው፤ “ወንጌላዊ” ተብለውም ይጠራሉ።

ክፉ፣ ዐመጽ(ዐመጸኛ)፣ ዐመጻ

“ክፉ” እና “ዐመጸኛ” የተሰኙት ቃሎች ሁለቱም የእግዚአብሔርን ቅዱስ ባሕርይና ፈቃድ የሚቃወም ማንኛውንም ነገር ያመለክታሉ።

  • “ክፉ” የሚለው ቃል የሰውን ፀባይ የሚያመለክት ሲሆን፣ “ዐመጸኛ” የሚለው ደግሞ የሰውን ባሕርይ ሊያመለክት ይችላል። ይሁን እንጂ፣ የሁለቱም ትርጉም ተመሳሳይ ነው።
  • “ዐመጻ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች ዐመጽ ሲያደርጉ የሚኖረውን ሁኔታ ነው።
  • ሰዎች ሌሎችን በመግደል፣ በመስረቅ፣ ስም በማጥፋት ወይም በሚፈጽሙት የጭካኔ ተግባር የክፋትን ወይም የዐመጻን ውጤት በግልጽ ማየት ይቻላል።

ከፍ ማድረግ፣ ከፍታ

ከፍ ማድረግ በከፍተኛ ደረጃ ማመስገንና ማክበር ማለት ነው። ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ማድረስንም ያመለክታል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ብዙውን ጊዜ እግዚአብሔርን ከፍ ለማድረግ ነው።
  • አንድ ሰው ራሱን ከፍ ካደረግ፣ ስለራሱ በትዕቢትና በእብሪት እያሰበ ነው ማለት ነው።

ማበረታታት

“ማበረታታት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች ትክክልና እውነት የሆነውን ነገር እንዲያደርጉ ማደፋፈርን ነው።

  • የማበረታታቱ ዓላማ ሰዎች ከኀጢአት እንዲርቁና የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዲያደርጉ መምከር ነው።
  • ክርስቲያኖች እርስ በርስ እንዲበረታቱና፣ ክፉ ቃል እንዳይመለለሱ አዲስ ኪዳን ያስተምራል።

እምነት

በአጠቃላይ ደረጃ “እምነት” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር፣ በሰው ወይም፣ በነገሮች መተማመንን፣ መደገፍን፣ ወይም፣ መመካትን ነው።

  • “ማመን” ማለት የምናምነው ሰው የሚናገረውና የሚያደርገው ሁሉ እውነትና አስተማማኝ መሆኑን በሙሉ ልብ መቀበል ማለት ነው።
  • “በኢየሱስ ማመን” ኢየሱስን በተመለከተ እግዚአብሔር የሚያስተምረውን ሁሉ ማመን ማለት ነው። በተለይም በኢየሱስና ሰዎችን ከኅጢአታቸው እንደሚያነጻቸው ከኅጢአታቸው የተነሳ ከሚጠብቃቸው ቅጣት እንደሚያድናቸው ማመን ማለት ነው።
  • አንድ ሰው በእውነት በኢየሱስ ካመነ መንፈስ ቅዱስ እርሱ ውስጥ ስለሚኖር መልካም መንፈሳዊ ፍሬ ወይም የሕይወት ለውጥ ይኖረዋል።
  • አንዳንድ፣ “እምነት” “የእምነት እውነት” በሚለው በተገለጸው መሠረት፣ በአጠቃላይ ስለ ኢየሱስ የተሰጡ ትምህርቶችን ሁሉ ያመለክታል።
  • “እምነትን መጠበቅ” ወይም፣ “እምነትን መተው” በሚለው ዐውድ ውስጥ “እውነት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስን በተመለከተ የተሰጡ ትምህርቶችን ሁሉ ማመንን ነው።

ታማኝ፣ ታማኝነት

ለእግዚአብሔር፣ “ታማኝ” መሆን ዘወትር በእርሱ ትምህርት መኖር ማለት ነው። ለእርሱ በመታዘዝ እውነተኛነትን ማሳየት ማለት ነው ታማኝ ሆኖ የመገኘት ሁኔታ፣ “ታማኝነት” ይባላል።

  • ታማኝ የሆነ ሰው ሁሌም ቃሉን እንደሚጠብቅና ለሌሎች ያለበትን ኅላፊነት ሁሌም እንደሚወጣ እምነት ሊጣልበት ይችላል።
  • ታማኝ ሰው ረጅምና አስቸጋሪ ቢሆንበት እንኳ በጀመረው ሥራ ይተጋል።
  • ለእግዚአብሔር ታማኝ መሆን ዘወትር እግዚአብሔር እንድናደርግ የፈለገውን በማድረግ መጽናት ነው።

እምነት የለሽ እምነት ወይም የሚተማመንበት የሌለው ማለት ነው።

እምነት የለሽ፣ እምነት የለሽነት

  • ቃሉ ጥቅም ላይ የዋለው በእግዚአብሔር የማያምኑና ይህንንም በክፉ አኗኗራቸው ያሚያሳዩ ሰዎችን ለማመልከት ነው።
  • ነብዩ ኤርምያስ እምነት የለሽ በመሆናቸውና ለእግዚአብሔር ባለመታዘዛቸው እስራኤልን ይወቅሳል።
  • ጣዖቶችን አመለኩ፤ እግዚአብሔርን የማያመልኩ ወይም ለእግዚአብሔር የማይታዘዙ ሰዎችን መጥፎ ባሕል ተከተሉ።

ሐሰተኛ አምላክ፣ ባዕድ አምላክ፣ ጣዖት

ሐሰተኛ አምላክ በአንዱ እውነተኛ አምላክ ቦታ ሰዎች የሚያመልኩት ነገር ነው። ወንድ ጣዖት እንዳለ ሁሉ ሴት ጥዖትም አለች።

  • ሐሰተኛ አማልክት ሕልውና የላቸውም፤ እውነተኛ አምላክ ያህዌ ብቻ ነው።
  • አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በተለያዩ ነገሮች ሐሰተኛ አማልክቶቻቸውን የሚወክልላቸው ምስል ይሠራሉ።
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው የእግዚአብሔር ሕዝብ ሐሰተኛ አማልክት ለማምለክ በተደጋጋሚ ለእርሱ ከመታዘዝ ወደኋላ ሄደው እንደነበር እናያለን።
  • የሚያመልኳቸው ሐሰተኛ አማልክትና ጣዖቶች ኅይል እንዳላቸው እንዲያምኑ ብዙውን ጊዜ አጋንንት ሰዎችን ያሳስታሉ።
  • በኣል፣ ዳጎንና ሞሎክ መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ሰዎች ያመልኳቸው ከነበሩ ብዙ ሐሰተኛ አማልክት መከከል ሦስቱ ናቸው።
  • አሼራና አርጤምስ(ዳያና) የጥንት ሰዎች ያመልኳቸው ከነበሩ ሴት አማልክት ሁለቱ ነበሩ።

ሞገስ፣ ሞገስ ያለው፣ አድልዎ (ከሌሎች የተለየ ሞገስ የሚደረግለት)

ሞገስ እርሱን በተመለከተ ጥሩ አመለካከት ያለንን ሰው ለመጥቀም የሚደረግ ነገርን ያመለክታለ። “ሞገስ ያለው” ነገር ቀና ተቀባይነት ያለው ወይም ጠቃሚ ነው።

  • “አድልዎ” ለአንዱ ሞገስ ማሳየት ለሌላው ግን ሞገስ መንፈግ ነው። አንዳንዴ ሰዎች ሀብታም ወይ ታዋቂ በመሆናቸው ብቻ ከሌላው የተለየ ሞገስ (አድልዎ) ይደረግላቸዋል።
  • ኢየሱስ፣ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት፣ “ሞገስ በማግኘት አደገ።” ይህም ፀባይና ባሕርዩ በእነርሱ ዘንድ ተቀባይነት ነበረው ማለት ነው።
  • “ሞገስ አገኘ” የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር በሌሎች ዘንድ መወደድን ተቀባይነት ማግኘትን ያመልክታል።
  • አንድ ንጉሥ ለሰው ሞገስ አደረገ ማለት ያ ሰው ያቀረበው ልመና በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አገኘ ማለት ነው።

ፍርሃት፣ ፈራ፣ የያህዌ ፍርሃት

“ፍርሃት” እና፣ “ፈራ” የሚሉት በእርሱ ወይም በሌሎች ላይ ጉዳት ይመጣል ብሎ ሲያስብ የሚኖረው ደስ የማይል ስሜት ነው።

  • “ፍርሃት” ሥልጣን ላለው ሰው ጥልቅ አክብሮት መገለጫ ሊሆንም ይችላል።
  • “የያህዌ ፍርሃት” (ወይም በተለመደው መልኩ፣ “የእግዚአብሔር ፍርሃት” እና፣ “የጌታ ፍርሃት”) ከልብ እግዚአብሔርን ማክበርንና ያንን በመታዘዝ ማሳየትን ያመለክታል። ይህ ዐይነቱ ፍርሃት እግዚአብሔር ቅዱስና ኀጢአትን የሚጠላ መሆኑን ከመገንዘብ የሚመጣ ነው።
  • ያህዌን የሚፈራ ሰው ጠቢብ (አስተዋይ) እንደሚሆን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።

ኅብረት

አጠቃላይ በሆነ ደረጃ፣ “ኅብረት” ተመሳሳይ ፍላጎትና ልምምድ ያላቸው የአንድ ማኅበር አባሎች መካከል የሚደረግ የወዳጅነት ግንኙነትን ያመለክታል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ኅብረት” በክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች አድነትን ነው ምንጊዜም የሚያመለክተው።
  • ክርስቲያናዊ ኅብረት ከክርስቶስና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ባላቸው ግንኙነት አመካይነት አማኞች እርስበርስ ያላቸውን ግንኙነት የሚገልጹበት መንገድ ነው።
  • የጥንት ክርስቲያኖች ኅብረታቸውን የሚገልጹት የእግዚአብሔርን ቃል ትምህርት በመካፈል፣ በአንድነት በመጸለይ ያላቸውን ሁሉ በመካፈልና አብረው በመመገብ ነበር።
  • ክርስቲያኖች በኢየሱስ፣ በሰዎችና በእግዚአብሔር መካከል የነበረውን መለያየት ባስወገደበት የመስቃል ላይ መሥዋዕታዊ ሞቱ በማመናቸው ከእግዚአብሔርም ጋር ኅብረት አላቸው።

በመንፈስ መሞላት

“በመንፈስ ቅዱስ መሞላት” የሚለው አገላለጽ የእግዚአብሔር ፈቃድ ማድረግ እንዲችል መንፈስ ቅዱስ ለሰው የሚሰጠውን ኅይል የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው።

  • “መሞላት” የሚለው ፈሊጣዊ ቃል በዙውን ጊዜ “በቁጥጥር ሥር መሆን” ማለት ነው።
  • የመንፈስ ቅዱስን ምሪት ሲከተሉና እግዚአሔር የሚፈልገውን ለማድረግ እንዲረዳቸው ሙሉ በሙሉ በእርሱ ሲተማመኑ ሰዎች፣ “በመንፈስ ይሞላሉ”።

ሥጋ

መጽሐፍ ቅዱስ ሥጋ ሲል ቃል በቃል የሰውን ወይም የእንስሳን ለስላሳውን የአካል ክፍል ያመለክታል።

  • የሰው ልጆችን ወይም ሕያዋን ፍጥረታትን ሁሉ ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ሥጋ” የሚለውን በምሳሌያዊ አነጋገር ይጠቀምበታል።
  • አዲስ ኪዳን፣ “ሥጋ” ኅጢአተኛውን የሰዎች ባሕርይ ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።
  • “የሥጋ ቁራጭ፣ የአጥንት ፍላጭ” የሚለው ፈሊጣዊ ቋንቋ በሥጋ የምንዛመደውን ሰው ማለት አባትን፣ እናትን፣ ልጆችን፣ የልጅ ልጆችን፣ እኅት፣ ወንድሞችንና ሌሎችን የቅርብ ዘመዶችን ያመለክታል።
  • “ሥጋና ደም” የአንድ ሰው የቀደሙ አባቶችንና እናቶችንም ያመለክታል።

ሞኝ፣ ሞኝነት፣ ከንቱነት

“ሞኝ” የሚባለው ብዙውን ጊዜ የተሳሳተ ምርጫ የሚያደርግ በተለይም አለመታዘዝን የሚመርጥ ሰው ነው። “ሞኝነት” ማስተዋል የሌለው ሰው ወይም ፀባይ የሚገለጥበት መንገድ ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ፣ “ሞኝ” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር የማያምንና ለእርሱ የማይታዘዝ ሰውን ነው። ብዙውን ጊዜ ቃሉ ጥቅም ላይ የሚውለው በእግዚአብሔር ከሚያምንናን ለእርሱ ከሚታዘዝ ሰው አንጻር ነው።
  • መዝሙሮቹ ውስጥ ዳዊት በእግዚአብሔር የማያምንና በእግዚአብሔር ፍጥረቶች ውስጥ ያሉትን ማስረጃዎች ችላ የሚልን ሰው ሞኝ በማለት ይጠራዋል።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለው መጽሐፍ ምሳሌ ሞኝ ሰው ምን ማለት እንደ ሆነ ብዙ መገለጫዎች ያቀርባል።
  • “ከንቱነት” ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ በመሆኑ ማስተዋል የሌለበት ድርጊት ያመለክታል።

ይቅር ማለት ይቅርታ

አንድን ሰው ይቅር ማለት ከዚህ ቀደም ባደረገው መጥፎ ነገር ቂም አለመያ ማለት ነው። “ይቅርታ” ሌላውን ይቅር የማለት ተግባር ነው።

  • ብዙውን ጊዜ አንድን ሰው ይቅር ማለት በፈጸመው ጥፋት እርሱን አለመቅጣት ማለት ነው።
  • ቃሉ “ዕዳ መሰረዙን” በሚያመለክት መልኩ፣ “መሰረዝ” የሚል ትርጕም ባለው መልኩ ምሳሌያዊ አነጋገርም ይሆናል።
  • ሰዎች ኀጢአታቸውን ሲናዘዙ ከኢየሱስ መስቀል ላይ መሥዋዕታዊ ሞት የተነሣ እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል።
  • እርሱ ይቅር እንዳላቸው እነርሱም ሌሎችን ይቅር ማለት እንዳለባቸው ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን አስተማረ።

መርሳት፣ ተረሳ

“መርሳት” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር ጨርሶ መተው ማለት ነው። “የተረሳ” በሌላው ወገን ጨርሶ የተተወ ግምት ውስጥ የማይገባ ሰው ነው።

  • ሰዎች እግዚአብሔርን “ረሱ” ከተባለ ለእርሱ ታማኝ አይደሉም፤ ለእርሱ አይታዘዙም ማለት ነው።
  • እግዚአብሔር ሰዎችን “ረሳ” ከተባለ እርሱ አይረዳቸውም፤ እንደ ገና ወደ እርሱ እንዲመለሱ የተለያየ መከራና ችግር እንዲደርስባቸው ይተዋቸዋል ማለት ነው።
  • መዘንጋት ወይም የእግዚአብሔርን ትምህርት አለመከተል ማለትም ነው።
  • “መርሳት” የሚለው ቃል፣ “ረስታችኋል” ወይም “ተረስታችኋል” በሚል የኀላፊ ጊዜ ጥቅም ላይ ይውላል።

መፈጸም

“መፈጸም” አንዳች የሚጠበቅ ነገርን ፈጽሞ ወይም አከናውኖ መገኘት ማለት ነው።

  • ትንቢት ሲፈጸም፣ በትንቢቱ የተነገረውን እግዚአብሔር እንዲፈጸም አደረገ ይባላል።
  • አንድ ሰው የገባውን ቃል ሲጠብቅ፣ ሰውየው አደርጋለሁ ያለውን ፈጽሟል ማለት ነው።
  • ኀላፊነትን መወጣት የተሰጠውን ወይም የተጠየቀውን ተግባር መፈጸም ማለት ነው።

አሕዛብ

አሕዛብ የያዕቆብ ወይም የአሥራ ሁለቱ የእርሱ ልጆች ዘር ያልሆነ ሰው ነው። ስለሆነም አሕዛብ አይሁድ አይድለም ማለት ነው።

  • ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ አሕዛብ አልፎ አልፎ፣ “ያልተገረዙ” ተብለው ይጠራሉ፤ ምክንያቱም እስራኤላውያን እንደሚያደርጉት አብዛኞቹ ወንዶች ልጆቻቸውን ስለማይገርዙ ነው።
  • ያ እርሱ የተለየ ሕዝብ እንደሆኑ እግዚአብሔር አይሁድን በመምረጡ፣ አሕዛብ ባዕዳንና የእግዚአብሔር ሕዝብ መሆን እንደማይችሉ አሰቡ።
  • በታሪክ ውስጥ በተለያየ ጊዜ አይሁድም እስራኤላውያን ወይም ዕብራውያን ተብለው ተጠርተዋል። ሌሎች ግን አሕዛብ ተብለው የሚጠሩት።
  • አሕዛብ የሚለውን፣ “አይሁድ ያልሆነ” ወይም፣ “እስራኤላዊ ያልሆነ” (ብሉይ ኪዳን) ብሎ መተርጎም ይቻላል።
  • በባሕላቸው መሠረት አይሁድ ከአሕዛብ ጋር አይበሉም ነበር፤ ይህም በጥንት ቤተ ክርስቲያን ችግር ሆኖ ነበር።

ስጦታ

“ስጦታ” የሚለው ለሌላው ወገን የተሰጠ ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ስጦታ የሚሰጠው በምላሹ ምንም ነገር ባለ መጠበቅ ነው።

  • ለድኾች የሚሰጥ ገንዘብ፣ ምግብ፣ ልብስና ማንኛውም ነገር “ስጦታ” ይባላል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ መባ ወይም መሥዋዕትም፣ “ስጦታ” ይባላል።
  • የድነት ስጦታ በኢየሱስ በማመን በኩል እግዚአብሔር የሰጥን ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “ስጦታ” የሚለው ቃል ሌሎችን ለማገልገል እግዚአብሔር ለክርስቲያኖች ሁሉ ይሚሰጠውን የተለያዩ መንፈሳዊ ችሎታዎችን ያመለክታል።

ክብር፣ የከበረ

በአጠቃላይ “ክብር” ማለት ምስጋና፣ ውበትና የላቀ ታላቅነት ማለት ነው። ክብር ያለው ነገር “የከበረ” ይባላል።

  • አንዳንዴ “ክብር” ታልቅ ዋጋ እና አስፈላጊነት ያለውን ነገር ያመለክታል። በሌላ ዐውድ ደግሞ ውበትን፣ ድምቀትን ወይም ፍርድን ያመለክታል።
  • ለምሳሌ፣ “የእረኞች ክብር” የሚለው ሐረግ በጎቻቸው የሚግጡት ሳር በብዛት ያለበትን ለምለም የግጦሽ ቦታ ያመለክታል።
  • በተለይ ደግሞ ክብር በአጽናፈ ዓለም ውስጥ ካለ ማንኛውም ሰውና ማንኛውም ነገር እጅግ የበለጠ ክቡር የሆነው እግዚአብሔርን ያመለክታል። ባሕርዩ ሁሉ ክብሩንና ውበቱን ይገልጻል።
  • “መክበር” ማለት በአንድ ነገር መጓደድ ወይም መመካትን ያመለክታል።

እግዚአብሔር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር አጽናፈ ዓለሙን ከምንም ያስገኘው ዘላለማዊ ፈጣሪን ያመለክታል። እግዚአብሔር አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በሚባሉ ሦስት አካሎች ተገልጧል። የእግዚአብሔር ተፀውዖ (መጠሪያ) ስም፣ “ያህዌ” ነው።

  • እግዚአብሔር ሁሌም ነበረ፤ ምንም ነገር ከመሆኑ በፊት ነበረ፤ ለዘላለምም ይኖራል።
  • አጽናፈ ዓለሙ ውስጥ ባለ ማንኛውም ነገር ሥልጣን ያለው እውነተኛ አምላክ እርሱ ብቻ ነው።
  • እግዚአብሔር ፍጹም ጻድቅ፣ እጅግ ጠበኛ፣ ቅዱስ፥ ኀጢአት የሌለበት፣ መልካም መሐሪና አፍቃሪ ነው።
  • እርሱ ኪዳን አክባሪ አምላክ ነው፤ እርሱ ተስፋ ቃሉን የሚፈጽም ነው።
  • ሰዎች የተፈጠሩት እርሱን ለማምለክ ነው፤ ማምለክ ያለባቸው እርሱን ብቻ ነው።
  • ስሙ፣ “ያህዌ” መሆኑን እግዚአብሔር ተናግሮአል፤ ይህም “እርሱ ነው” ወይም፣ “እኔ ነኝ” ወይም፣ “ሁሌም የምኖር” ማለት ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ሕላዌ ስለሌላቸውና ሰዎች በስሕተት ስለሚያመልኳቸው ስለ ሐሰተኛ አማልክትም ይናገራል።

አምላካዊ፣ አምላካዊነት

“አምላካዊ” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን በሚያስከብርና የእግዚአብሔርን ማንነት በሚያሳይ መንገድ የሚኖር ሰውን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል። የእግዚአብሔርን ፈቃድ በማድረግ እርሱን የማያከብር ሰው ባሕርይ አምላካዊነት ይባላል።

  • አምላካዊ ባሕርይ ያለው ሰው ፍቅርን፣ ደስታን፣ ሰላምን፣ ትዕግሥትን፣ ቸርነትንና ራስን መግዛትን የመሳሰሉ የመንፈስ ፍሬ በሕይወቱ ይታያሉ።
  • የአምላካዊነት ባሕርይ ማለትም፣ እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ መኖር፣ መንፈስ ቅዱስ ውስጡ ለመሆኑና ለእርሱም እየተገዛ መሆኑን የሚያሳይ ፍሬ ወይም ውጫዊ ማስረጃ ነው።

እግዚአብሔር አብ፣ ሰማያዊ አባት፣ አባት

“እግዚአብሔር አብ” እና፣ “ሰማያዊ አባት” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት አንዱን እውነተኛ አምላክ ያህዌን ነው። ይህ ቃል በተለይም ኢየሱስ ሲጠቀምበት “አባት” ተብሎም ተጠርቷል።

  • እግዚአብሔር - እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተብሎ ተጠርቷል። እያንዳንዱ አካል ፍጹም አምላክ ነው፤ ይሁን እንጂ ያለው አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ይህ ሰዎች ሙሉ በሙሉ መረዳት የማይችሉት ምስጢር ነው።
  • እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር አልድን (ኢየሱስን) ወደ ዓለም ላከ እርሱም መንፈስ ቅዱስን ለሕዝቡ ላከ።
  • በእግዚአብሔር ወልድ የሚያምን ሁሉ የእግዚአብሔር አብ ልጅ ይሆናል፤ መንፈስ ቅዱስ በዚያ ሰው ውስጥ ለመኖር ይመጣል። ይህ የሰው ልጅ ሙሉ በሙሉ መረዳት የማይችለው ምስጢር ነው።

መልካም፣ መልካምነት

“መልካም” የሚለው ቃል እንደ ምንባቡ ዐውድ ሁኔታ የተለያዩ ትርጕሞች ይኖሩታል። እነዚህን የተለያዩ ቃሎች ለመተርጎም የተለያዩ ቋንቋዎች የተለያዩ ትርጕሞች ያቀርባሉ።

  • አጠቃላይ በሆነ መልኩ ከእግዚአብሔር ባሕርይ፣ ዓላማና ፈቃድ ጋር የሚስማማ ነገር መልካም ነው።
  • “መልካም” ነገር ደስ የሚያሰኝ፣ የላቀ ብልጫ ያለው፣ ሰዎችን የሚረዳ፣ ምቹ፣ ጠቃሚ ወይም ከግብረ ገብ አንጻር ትክክል ሊሆን ይችላል።
  • “መልካም” መሬት፣ “ለም” ወይም፣ “ፍሬያማ” ተብሎ ይጠራል።
  • “መልካም” ሰብል፣ ብዛት ያለው ሰብል ይባላል።
  • እንደ “መልካም ገበሬ” ሁሉ አንድ ሰው በሥራውና በሙያው ጠንቃቃና የተዋጣለት ከሆነ፣ “መልካም” ይባላል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የ”መልካም” አጠቃላይ ትርጕም “ከክፉ” ጋር በንጽጽR ነው የሚቀርበው።
  • “መልካምነት” የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ የሚያማለክተው ግብረ ገባዊ ጥራትን ወይም በሐሳብና በተግባር ጻድቅ ሆኖ መገኘትን ነው።
  • የእግዚአብሔር መልካምነት መልካምና ጠቃሚ ነገሮችን ለሰዎች በመስጠት እነርሱን መባረኩን ያመለክታል። ግብረ ገባዊ ፍጽምናውንም ሊያመለክት ይችላል።

የምሥራች፣ ወንጌል

ቃል በቃል የምሥራች ማለት ሲሆን፣ ሰዎችን የሚጠቅምና ደስ የሚያሰኛቸውን መልእክት ያመለክታል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ይህ ቃል የሚያመለክተው በኢየሱስ መስቀል ላይ መሥዋዕት መሆን አማካይነት እግዚአብሔር ለሰዎች ያለውን ድነት ነው።
  • በአብዛኞቹ የአማርኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች “የምሥራች” የሚለው ቃል፣ “ወንጌል” ተብሎ ተተርጉሞአል። ለምስሌ፣ “የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል” እና፣ “የመንግሥቱ ወንጌል” ከተሰኙት ሐረጎች መመልከት ይቻላል።

ጸጋ፣ ባለጸጋ

“ጸጋ” የሚለው ቃል ምንም ሳይለፋና ሳይደክም አንድን ሰው መርዳትን ወይም መባረክን ያመለክታል። “ባለ ጸጋ” ሌሎችን ጸጋ የሚያሳይን ሰው ይመለከታል።

  • እግዚአብሔር ለኀጢአተኛ የሰው ልጆች ያለው ጸጋ በነጻ የሚሰጥ ስጦታ ነው።
  • ጸጋ በደልና የሚጎዳ ነገር የፈጸመውን ሰው ይቅር ማለትንና ለእርሱ ደግ መሆንንም ያመለክታል።
  • “ጸጋ ማግኘት” ከእግዚአብሔር ረድኤትና ምሕረትን መቀበልን የሚያመለክት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አንድን ሰው አስመልክቶ እግዚአብሔር ደስ ተሰኝቶ እነርሱን መርዳቱን የሚያመለክት ትርጕምንም ይጨምራል።

የበደል መሥዋዕት

“በደል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኀጢአት ማድረግን ወይም ወንጀል መፈጸምን ነው።

  • “መበደል” ግብረ ገባዊ ያልሆነ ነገር ማድረግ ማለትም በእግዚአብሔር ላይ ማመፅ ማለት ነው።
  • “የበደል” ተቃራኒ፣ “ንጹሕነት” ነው።

ሐዴስ፣ ሲኦል

ሞትንና ሰዎች ሲሞቱ የሚሄዱበትን ቦታ ለማመልከትት “ሐዴስ” እና “ሲኦል” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ ውለዋል። የሁለቱም ትርጕም ተመሳሳይ ነው።

  • የሙታን ስፍራን በአጠቃላይ ለማመልከት ብዙውን ጊዜ ብሉይ ኪዳን ውስጥ “ሲኦል” የተሰኘው የዕብራይስጥ ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ በእግዚአብሔር ላይ ያመፁ ነፍሳትን ቦታ ለማመልከት “ሐዴስ” የተሰኘው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል። እነዚህ ነፍሳት ወደ ሐዴስ እንደሚወርዱ ተነግሯል። አንዳንዴ ይህ በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች ወደሚኖሩበት ወደ ሰማይ፣ “መውጣት” ጋር በንጽጽር ይቀመጣል።
  • የዮሐንስ ራእይ ውስጥ፣ “ሐዴስ” የሚለው ቃል፣ “ሞት” ከተሰኘው ቃል ጋር በአንድነት ቀርቧል። መጨረሻው ዘመን ላይ ሞትና ሐዴስ ወደ እሳቱ ባሕር ይጣላሉ፤ እርሱም ገሃነም ነው።

ልብ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልብ የሰውን ሐሳብ፣ ስሜት፣ ፍላጎት ወም ፈቃድ ለማመልከት ብዙውን ጊዜ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

  • “ልበ ጠንካራ” መሆን ሰውየው በግትርነት ለእግዚአብሔር መታዘዝ አለመፈለጉን የሚያሳይ የተለመደ አገላለጽ ነው።
  • “በፍጹም ልቤ” ወይም፣ “በሙሉ ልቤ” የተሰኙት አገላለጾች ምንም ወደ ኋላ ሳይባል፣ በሙሉ መሰጠትና ፈቃደኛነት አንድን ነገር ማድረግን ያመለክታሉ።
  • “በልብህ ያዘው” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ለአንድ ሰው የተለየ ከበሬታ መስጠት ማለት ነው።
  • “ልበ ሰባራ” የሚለው ሐረግ ከፍ ያለ ሐዘንን ያመለክታል። የሰውየው ስሜት በከፍተኛ ደረጃ ተጎድቷል ማለት ነው።

ሰማይ፣ ሰማያት፣ ሰማያዊ

“ሰማይ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል የእግዚአብሔር መኖሪያን ያመለክታል።

  • “ሰማያት” የሚለው ቃል ፀሐይ፣ ጨረቃንና ከዋክብትን ጨምሮ ከምድር በላይ የምንመለከተውን ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ምድር ላይ ሆነን በቀጥታ የማናያቸውን በሩቅ ያሉ ፕላኔቶችን ጨምሮ የሰማይ አካላትን ሁሉ ያጠቃልላል።
  • “ሰማይ” ደመናና የምንተነፍሰው አየር ያለበትን ከምድር በላይ ያለውን የተንጣለለ ሰማያዊ ቦታ ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብት፣ “በላይ በሰማይ” መሆናቸው ይነገራል።
  • በአንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ዐውዶች መሠረት “ሰማይ” እንዲሁ ከምድር በላይ የተንጣለለው ሰማያዊ ቦታ ወይም የእግዚአብሔርን መኖሪያ ያመለክታል።
  • “ሰማይ” በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ የሚውለው እግዚአብሔርን ለማመልከት ነው። ለምሳሌ ማቴዎስ ስለ “መንግሥተ ሰማይ” ሲናገር ስለ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት” መናገሩ ነው።

ዕብራዊ

“ዕብራውያን” በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ሐረግ በኩል የተገኙ የአብርሃም ዘሮች ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ዕብራዊ” ተብሎ የተጠራ የመጀመሪያ ሰው አብርሃም ነበር። “ዕብራውያን” በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ሐረግ በኩል የአብርሃም ዘር የሆኑ ሕዝብ ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ዕብራው” ተብሎ የተጠራ የመጀመሪያ ሰው አብርሃም ነው።

  • “ዕብራዊ” የሚለው ቃል ዕብራውያን የሚናገሩትንም ቋንቋ ያመለክታል። መጀመሪያ ላይ ብሉይ ኪዳን የተጻፈው በዕብራይስ ቋንቋ ነበር።
  • ዕብራውያን፣ “የአይሁድ ሕዝብ” ወይም እስራኤላውያን ተብለውም ይጠራሉ። እነዚህ ቃሎች ስለ አንድ ሕዝብ የሚያመለክቱ እንደ መሆናቸው መጠን ሦስቱንም ቃሎች የመጀመሪያው ቅጂ ላይ በተጻፉበት ቅጂ መሠረት ማስቀመጡ ተገቢ ነው።

ገሃነም፣ የእሳት ባሕር

ገሃነም በእርሱ ላይ የሚያምፁትንና በኢየሱስ መሥዋዕትነት በኩል እነርሱን የማድኑን ዕቅድ ችላ የሚሉትን የሚቀጣበት የመጨረሻው የስቃይ ቦታ ነው። “የእሳት ባሕር” ተብሎም ይጠራል።

  • ገሃነም የእሳትና የጽኑ ስቃይ ቦታ መሆኑ ተነግሯል።
  • ሰይጣንና እርሱን የሚከተሉ ርኵሳን መናፍስት ለዘላለም ቅጣት ወደ ገሃነም ይጣላሉ።
  • ኢየሱ ለኀጢአታቸው መሥዋዕት መሆኑን የማያምኑና እርሱ እንደሚያድናቸው የማይተማመኑ ሰዎች ለዘላለም በገሃነም ይቀጣሉ።

ሊቀ ካህን

“ሊቀ ካህን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተቀሩት እስራኤላውያን ካህናት መሪ በመሆን ለአንድ ዓመት እንዲያገለግል የተሾመ የተለየ ካህንን ያመለክታል።

  • ሊቀ ካህን የተለየ ኀላፊነቶች ነበር። በዓመት አንድ ጊዜ የሆነውን መሥዋዕት ለማቅረብ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን እንዲገባ የሚፈቀድለት እርሱ ብቻ ነበር።
  • እስራኤላውያን ብዙ ካህናት ቢኖሯቸውም ለአንድ ዘመን አንድ ሊቀ ካህን ብቻ ነበራቸው።
  • ኢየሱስ በተያዘ ጊዜ የነበረው ሊቀ ካህን ቀያፋ ነበር። የቀያፋ ሚስት አባት የነበረው የቀድሞው ሊቀ ካህንና ምናልባትም ከዚያ በኋላም በሕዝቡ ላይ ኀይልና ሥልጣን የነበረው ሐና አልፎ ይጠቀሳል።

ቅዱስ፣ ቅድስና

“ቅዱስ” እና “ቅድስና” ኀጥእ ከሆነውና ፍጽምና ከሌለው ማንኛውም ነገር ፍጹም ልዩ የሚያደርገውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ ያመለክታል።

  • ፍጹም ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሰዎችንም ሆነ ነገሮችን ቅዱስ ያደርጋል።
  • ቅዱስ ሰው የእግዚአብሔር ይሆናል፤ እግዚአብሔርን ለማገልገልና ለእርሱ ክብር ለማምጣት ዓላማ ተለይቷል።
  • እግዚአብሔር ቅዱስ መሆኑን የተናገረለት ነገር ማለት ለእርሱ መሥዋዕት እንዲቀርብበት መሠዊያ ለእርሱ ክብርና አገልግሎት ተለይቶአል።
  • እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ እርሱ ካላቀረባቸው በቀር ሰዎች ወደ እርሱ መቅረብ አይችሉም፤ ምክንያቱም ሰዎች ኀጢአተኞችና ፍጽምና የጎደላቸው ናቸው።
  • በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር ለእርሱ ልዩ አገልግሎት ካህናትን ቅዱስ አድርጎ ይለይ ነበር። ወደ እርሱ መቅረብ እንዲችሉ አስፈላጊውን ሥርዐት በመፈጸም ከኀጢአት ነጽተዋል።
  • የእርሱ የሆኑትን ወይም ቤተ መቅደሱን የመሰሉ እርሱ ራሱን የገለጠበትን ቤተ መቅደሱን እንደመዳሰሉት አንዳንድ ቦታዎችንና ነገሮችን እግዚአብሔር ቅዱስ አድርጎ ለይቶአል።

ቅዱስ

“ቅዱሱ” የሚለው መጠሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሌም የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ይህ መጠሪያ ብዙውን ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለው፣ “የእስራኤል ቅዱስ” በተሰኘው ሐረግ ውስጥ ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስም፣ “ቅዱሱ” ተብሎ ተጠርቷል።
  • “ቅዱሱ” የሚለው ቃል አንዳንዴ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መልአክን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል።

ቅድስት፣ ቅድስተ ቅዱሳን

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ቅድስት” እና፣ “ቅድስተ ቅዱሳን” የተሰኙ ቃሎች መገናኛው ድንኳን ወይም ቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩ ሁለት ክፍሎች ያመለክታሉ። አንዳንዴ፣ “ቅድስት” ወይም፣ “ቅዱስ ቦታ” የሚለው በጠቅላላው ለእግዚአብሔር የለለየ ማንኛውንም ቦታ ያመለክታል።

  • ቅድስት” እና “ቅድስተ ቅዱሳን” በአጥር በተከለለ መገናኛ ድንኳን ወይም ቤተ መቅደስ አደባባይ የተከበበ ቦታ ነበር የሚገኙት። ቅድስተ ቅዱሳን መግቢያ ላይ በጣም ወፍራምና ከባድ መጋረጃ ነበር።
  • እስራኤላውያንን ሁሉ ከሚወክለው ከላቀ ካህኑ ጋር ለመገናኘት እግዚአብሔር ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ይመጣ ነበር።
  • ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ እንዲገባ የሚፈቀደው ለሊቀ ካህኑ ብቻ ነበር። ወፍራምና ከባድ መጋረጃ ማንም ወደዚያ እንዳይገባ ያግዳል።
  • “ቅድስት” ወይም፣ “ቅድስት ቦታ” የመጀመሪያው ክፍል ሲሆን ውስጡ ሁለት ነገሮች ነበሩ፤ የዕጣን መሠዊያና የተቀደሰው እንጀራ ያለበት መንበር።
  • “ቅድስተ ቅዱሳን” ሁለተኛው ክፍል ሲሆን በጣም ወደ ውስጥ ሲገባ የሚገኘው ነው፤ የቃል ኪዳኑ ታቦት እዚህ ውስጥ ነበር።
  • አንዳንዴ፣ “ቅድስት” ወይም፣ “ቅዱስ ቦታ” የሚለው በአጠቃላይ የቤተ መቅደሱን ሕንፃ ወይም መገናኛ ድንኳኑን ያመለክታል።

መንፈስ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ፣ የጌታ መንፈስ

እነዚህ ሦስት ቃሎች የሚያመለክቱት እርሱ ራሱ እግዚአብሔር የሆነው መንፈስ ቅዱስን ነው። እውነተኛው አንድ አምላክ አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ የሚባሉ አካላት አሉት።

  • መንፈስ ቅዱስ አንዳንዴ፣ “መንፈስ” እና “የያህዌ መንፈስ” እና፣ “የእውነት መንፈስ” ተብሏል።
  • መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር በመሆኑ ፍጹም ቅዱስ፣ እጅግ ንጹሕ፣ በባሕርዩና በሚያደርገው ነገር ሁሉ ፍጹም ጻድቅ ነው።
  • ከአብና ከወልድ ጋር መንፈስ ቅዱስ ዓለምን በመፍጠር ተሳታፊ ነበር።
  • እግዚአብሔር ወልድ ማለት ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከተመለሰ በኋላ ሕዝቡን እንዲመራቸው፣ እንዲያስተምራቸው፣ እንዲያጽናናቸውና የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ እንዲያስችላቸው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ላከ።
  • መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን መራው፤ በኢየሱስ የሚያምኑትንም ይመራቸዋል።

ክብር፣ ማክበር

“ክብር” የሚለው ቃል ለእግዚአብሔር ወይም ለሰው ልጅ የሚሰጥ የላቀ ቦታ፣ ግምት ወይም አክብሮታዊ ፍርሃት ነው።

  • ሌሎችን እንዲያከብሩ ለራሳቸው ግን ክብር መፈለግ እንደሌለባቸው እግዚአብሔር ለክርስቲያኖች ተናግሮአል።
  • ልጆች ወላጆቻቸውን እንዲያከብሩ ተነግሮአቸዋል፤ ይህም መታዘዝንም ይጨምራል።
  • በተለይ ስለ ኢየሱስ በሚነገርበት ጊዜ፣ “ክብርና ግርማ” በአንድነት ተያይዘው ይቀርባሉ። አንድን ነገር የሚያመለክቱ ሁለት የተለያዩ የአገላለጽ መንገዶችን የሚያመለክቱ ሊሆኑ ይችላሉ።
  • እግዚአብሔርን ማክበር ለእርሱ መታዘዝንና የእርሱን ታላቅነት በሚያሳይ መንገድ መኖርንም ያጠቃልላል፥

ተስፋ

ተስፋ አንድ መልካም ነገር ይሆናል ብሎ መጠበቅና የተሻለ ነገር እንደሚመጣ መጠባበቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “ተስፋ” እግዚአብሔር ለሕዝቡ ቃል የገባውን እንደሚቀበሉ እርግጠኛ ሆ መጠበቅን ነው የሚያመለክተው። ይሁን እንጂ፣ አንድን ነገር እርግጠኛ ሆኖ ወይም በልበ ሙሉነት መጠበቅን የሚያመለክት በመሆኑ ULB በተሰኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም አብዛኛውን ጊዜ፣ “እምነት” ወይም፣ “ድፍረት” ተብሎ ተተርጕሞአል።

  • አንድን ነገር፣ “ተስፋ ማድረግ” ያን ነገር ለማግኘት መፈለግ ወይም ያ ነገር እንዲሆን መመኘት ነው።
  • “ተስፋ ማጣት” መልካም ነገር ይሆናል ብሎ አለመጠባበቅ ማለት ነው።

የእግዚአብሔር ቤት፣ የያህዌ ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “የእግዚአብሔር ቤት” እና፣ “የያህዌ ቤት” የተሰኙት ሐረጎች የሚያመለክቱት እግዚአብሔር የሚመለክትበትን ቦታ ነው።

  • ይህ ሐረግ በተለይ የመገናኛውን ድንኳን ወይም ቤተ መቅደሱን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
  • አንዳንዴ፣ “የእግዚአብሔር ቤት” የእግዚአብሔርን ሕዝብ ያመለክታ።

ትሑት፣ ትሕትና

ትሑት ሰው ከሌሎች ሁሉ የበለጠ እንደ ሆነ አያስብም። ትዕቢተኛ ወይም እብሪተኛ አይደለም።

  • በእግዚአብሔር ፊት ትሑት መሆን ከእርሱ ታላቅነት፣ ጥበብና ፍጽምና አንጻር የራሳችንን ደካማነትና ጉድለት መረዳት ማለት ነው።
  • አንድ ሰው ራሱን ትሑት ሲያደርግ፣ ራሱን ዝቅተኛው አስፈላጊነት ደረጃ ላይ ያኖራል።
  • ትሕትና ከራስ አስቀድሞ ስለ ሌሎች ችግር ማሰብ ማለት ነው።
  • ትሕትና ባሉን ስጦታዎችና ችሎታዎች ስንጠቀም ልከኛ በሆነ ዝንብሌ ማገልገል ማለት ነው።
  • “ትሑት ሁን” የሚለው ሐረግ፣ “ትዕቢተኛ አትሁን” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።
  • “በእግዚአብሔር ፊት ትሑት ሁን” የሚለው፣ “የእርሱን ታላቅነት በመገንዘብ ፈቀድህን ለእርሱ አስገዛ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።

ግብዝ፣ ግብዝነት

“ግብዝ” የሚለው ልቡ ክፉና ጠማማ ሆኖ በሰዎች ፊት ግን መልካም ሰው መስሎ ለመታየት የሚሞክር ሰው ነው። “ግብዝነት” መልካምና እውነተኛ መስሎ ለመታየት አንድ ሰው የሚያደርገው ነው።

  • ግብዝ ሰው ሰዎች ጥሩ ሰው ነው ብለው እንዲያስቡ መልካም ነገር ሲያደርግ የሚታይ ነው።
  • ብዙውን ጊዜ ግብዞች እነርሱ ራሳቸው የሚያደርጉትን ክፉ ነገር ሌሎች ሲያደርጉ ይነቅፋሉ።
  • አንዳንድ ልብሶችን መልበስን፣ አንዳንድ ምግቦችን መመገብን ወይም አለመመገብን የመሳሰሉ ሃይማኖታዊ ነገሮችን ቢያደርጉም ለሰዎች ግን መልካም ያልነበሩ ፈሪሳውያንን ኢየሱስ ግብዞች ብሏቸዋል።
  • ግብዝ ሰው የሌሎች ሰዎች ደካማነት ላይ ጣቱን ይጠቁማል፤ የራሱን ደካማነት ግን አይቀበልም።

የእግዚአብሔር አምሳል፣ ምስል

“አምሳያ” የሚለው ሌላውን የሚመስል፣ በጸባይም ሆነ በጥንተ ተፈጥሮው ሌላውን የመሰለ ማለት ነው። “የእግዚአብሔር አምሳል” የሚለው ሐረግ እንደ አውዱ ሁኔታ በተለያየ መንገድ ጥቅም ላይ ይውላል።

  • ጊዜ ሲጀመር እግዚአብሔር የሰው ልጆችን፣ “በራሱ አምሳል” ማለትም፣ “እርሱን አስመስሎ” ፈጠረ። ይህም ማለት የሰው ልጆች ምክንያታዊነትና ከሌሎች ጋር ተራክቦ የማድረግ ችሎታና ለዘላለም የሚኖር መንፈስ አላቸው ማለት ነው።
  • የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ፣ “የእግዚአብሔር ምሳሌ” መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል፤ ያም ማለት እርሱ ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። ከሰው ልጆች በተለየ መልኩ ኢየሱስ ፍጡር አይደለም። እስከዘላለም የእግዚአብሔር አብ ባሕርያት ስላሉት እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ሁሌም መለኮታዊ ባሕርያት አሉት።

መውረስ፣ ውርስ፣ መብት፣ ወራሽ

“መውረስ” እና፣ “ውርስ” ከእነርሱ ጋር ካለ የተለየ መቀራረብ የተነሣ ከወላጆቹ ወይም ከሌሎች ጠቃሚ ነገር መቀበል ማለት ነው። ያንን ውርስ የሚቀበል ወራሽ ይባላል።

  • በውርስ የሚገኙ ቁሳዊ ነገሮችን ገንዘብ፣ መሬት ወይ ሌሎች ንብረቶች ሊሆኑ ይችላሉ።
  • በኢየሱስ ለሚያምኑ ሁሉ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚሰጠው ማንኛውም መንፈሳዊ ውርስ በዚህ ሕይወትም ሆነ ከእርሱ ጋር ለዘላለም ሕይወት የሚጠቅሙ በረከቶችን ሁሉ ያካትታል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ የእርሱ ሕዝብ የእግዚአብሔር ርስት መሆናቸውንም ይናገራል፤ ይህም ማለት እነርሱ የእርሱ ናቸው፤ በእርሱ ዘንድ እጅግ የከበሩ ናቸው ማለት ነው።
  • “መብት” ከውርስ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ አንድ ሰው ከወላጆቹ ወይም ከእግዚአብሔር የሚያገናኛቸው ቁሳዊ ያልሆኑ በረከቶችንና ባሕርያትን ብቻ ያመለክታል።
  • ምድረ ከነዓንን እንደሚወርሱና ለዘላለም የእነርሱ እንደሚሆን ለአብርሃምና ለዘሮቹ እግዚአብሔር ቃል ገብቷል።
  • የእግዚአብሔር የሆኑ ሕዝቡ፣ “ምድሪቱን ስለሚወርሱበት ሁኔታ” የሚያመለክት ምሳሌያዊ ወይም መንፈሳዊ አነጋገርም አለ። ይህም ማለት በቁሳዊም ሆነ በመንፈሳዊ ደረጃ ይበለጽጋሉ፣ በእግዚአብሔር ይባረካሉ ማለት ነው።
  • በኢየሱስ የሚያምኑ፣ “የድነት ወራሾች” እና፣ “የዘላለም ሕይወት ወራሾች” እንደሚሆኑ በአዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ተስፋ ቃል ሰጥቷል። “የእግዚአብሔር መንግሥት ወራሾች” ተብሎም ተገልጿል። ይህ ለዘላለም የሚኖር መንፈሳዊ ርስት ነው።
  • እነዚህን ቃሎች በተመለከተ ሌሎች ምሳሌያዊ ትርጉሞችም ይኖራሉ፤
  • አስተዋዮች፣ “ክብር እንደሚወርሱ” እና፣ ጻድቃን፣ “ መልካም ነገሮችን እንደሚወርሱ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
  • “የተስፋው ወራሽ” ማለት እግዚአብሔር ለሕዝቡ እንደሚሰጥ ቃል የገባው መልካም ነገርን ሁሉ መቀበል ማለት ነው።
  • ሞኞችና የማይታዘዙ ሰዎች፣ “ነፋስን እንደሚወርሱ” ወይም፣ “ከንቱነትን እንደሚወርሱ” ለማመልከት ይህ ቃል አሉታዊ በሆነ መልኩም ጥቅም ላይ የዋለበት ሁኔታም አለ። ይህም ማለት ቅጣትንነ ከንቱ አኗኗርን ጭምሮ ኀጢአተኛ ተግባራቸው የሚያስከትለውን ሁሉ ይቀበላሉ ማለት ነው።

ርኩሰት

“ርኩሰት” የሚለው ቃል ትርጉም፣ “ኀጢአት” ከሚለው ጋር በጣም ተመሳሳይ ቢሆንም በተለይ፣ ሆን ተብሎ የሚፈጸም በደልን ወይም ታላቅ ዐመፃን ሊያመለክት ይችላል።

  • “ርኩሰት” ቃል በቃል ማጣመም ወይም ማበላሸት (ሕጉን) ማለት ነው። በከፍተኛ ደረጃ የሚፈጸም የፍትሕ መዛባትን ያመለክታል።
  • ርኩሰት ሆን ተብሎ ሌሎች ሰዎች ላይ የሚፈጸም ጎጂ ተግባር ሊባልም ይችላል።
  • ርኩሰት የሚለውን ቃል መግለጽ የሚችሉ ሌሎች መንገዶች፣ “ማጣመም” እና፣ “ብልሽት” የተሰኙ ሲሆኑ ሁለቱም አስከፊ ኀጢአት የመፈጸም ሁኔታን ያመለክታል።

ነጻ

“ነጻ” የሚለው ቃል ወንጀል ከመፈጸም ወይም ከሌሎች በደሎች ነጻ የሆነ ማለት ነው። በጠቅላላው በማንኛውም ክፉ ነገር አለመሳተፉን ያመለክታል።

  • በደል ፈጽመሃል ተብሎ የተከሰሰ ሰው ያን በደል አለመፈጸሙ ከተረጋገጠ ነጻ ይሆናል።
  • የደረሰባቸው በደል እንዲደርስባቸው ምክንያት የሚሆን ምንም በደል ያልፈጸሙ ሰዎችን ለማመልከት አንዳንዴ፣ “ነጻ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ይውላል፤ ለምሳሌ፤ የጠላት ወታደር ጥቃት ያደረሰባቸው፣ “ንጹህ ሰዎች” እንደ ምሳሌ ማቅረብ ይቻላል።

መማልጃ፣ ምልጃ

“መማለጃ” እና፣ “ምልጃ” በሌሎች ስፍራ ሆኖ ስለ እነርሱ መለመን ወይም መጸለይን ያመለክታል። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ስለሌሎች ከመጸለይ ጋር ነው።

  • “ለ----መማለድ” እና ለ---መጸለይ” የተሰኙ ገለጻዎች ሌሎች እንዲጠቀሙ እግዚአብሔርን መለመን ማለት ነው።
  • መንፈስ ቅዱስ ለእኛ እንደሚማልድ ወይም እንደሚጸልይ መጽሐር ቅዱስ ያስተምራል።
  • አንድ ሰው ሥልጣን ላይ ላሉ ሰዎች ሲማልድ እነርሱን በተመለከተ ለእግዚአብሔር ልመና ማቅረቡ ነው።

እስራኤል፣ እስራኤላውያን፣ የእስራኤል ሕዝብ

እስራኤል እግዚአብሔር ለያዕቆብ የሰጠው ስም ነው። እስራኤል፣ “ከእግዚአብሔር ጋር ታገለ” ማለት ነው።

  • የያዕቆብ ዘሮች የእስራኤል ሕዝብ፣ ወይም እስራኤላውያን በመባል ታውቀዋል።
  • እግዚአብሔር ከእስራኤል ሕዝብ ጋር ኪዳን አደረገ። እነርሱ የእርሱ የተመረጠ ሕዝብ ናቸው።
  • እስራኤል የሕዝባቸው ስም ነው።
  • የእስራኤል ሕዝብ ከአሥራ ሁለት ነገዶች የተገኘ ነው።
  • ንጉሥ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ የእስራኤል ሕዝብ ለሁለት መንግሥታት ተከፈለ፤ ደቡባዊው የይሁዳ መንግሥት ሲባል፣ ሰሜናዊው መንግሥት የእስራኤል መንግሥት ተባለ።

ቀናተኛ፣ ቅናት

“ቀናተኛ” እና “ቅናት” የተሰኙት ቃሎች አንድ ሰው የግል የማድረግ ጽኑ ፍላጎት ያመለክታሉ። አንድን ነገር ወይም ንብረት አጥብቆ የመያዝ ፍላጎትንም ያመለክታል።

  • ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሁለት አገላለጾች ጥቅም ላይ የሚውሉት ባል ሚስቱን ወይም ሚስት ባልዋን የግሏ ብቻ ለማድረግ የሚያሳዩት ጽኑ ፍላጎት ለማመልከት ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሲሆን ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሁለት አገላለጾች ጥቅም ላይ የሚውሉት የእርሱ ሕዝብ ንጽሕና ማንኛውንም ኀጢአት እንዳያደርጉ እግዚአብሔር ያለውን ጽኑ ፍላጎት ለማመልከት ነው።
  • እግዚአብሔርም ለስሙ፣ “ቀናተኛ” ነው፤ ስሙ እንዲከብርና እንዲፈራ ይፈልጋል።
  • ሌላው ቅናት አሉታዊ ሲሆን ከራስ ይልቅ ሌላው ሲስካለትና ተወዳጅ ሆኖ ሲገኝ በቁጣ የሚገለጠው ነው። ይህ፣ “ምቀኝነት” ከሚለው ጋር በጣም የተያያዘ ነው።

ኢየሱስ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ክርስቶስ ኢየሱስ

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ኢየሱስ ማለት፣ “ያህዌ ያድናል” ማለት ነው። “ክርስቶስ” “የተቀባው” የሚል ትርጉም ያለው ቃል ሲሆን፣ መሲህ የሚለው ሌላ ቃል ነው።

  • ብዙውን ጊዜ “ኢየሱስ ክርስቶስ” ወይም፣ “ክርስቶስ ኢየሱስ” በተሰኙት ሁለቱ ስሞች ይጣመራሉ። እነዚህ ስሞች የእግዚአብሔር ልጅ በኀጢአታቸው ምክንያት ሕዝቡን ከዘለዓለም ቅጣት ለማዳን የመጣ መሲህ መሆኑን አጽንዖት ይሰጣሉ።
  • ተአምራዊ በሆን መንገድ መንፈስ ቅዱስ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ልጅ ሰው ሆኖ እንዲወለድ አደረገ። እርሱ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው እንዲያድን የተመደበ በመሆኑ ኢየሱስ ብለው እንዲጠሩት መልአኩ ለምድራዊ ወላጆቹ ተናግሮ ነበር።
  • እርሱ እግዚአብሔር መሲህ ወይም ክርስቶስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ኢየሱስ ብዙ ተአምራት አድርጓል።

አይሁድ፣ አይሁዳዊ

አይሁድ በልጅ ልጁ በያዕቆብ በኩል የአብርሃም ዘር የሆኑ ሕዝብ ናቸው።

  • ሰዎች እስራኤላውያን አይሁድ በማለት መጥራት የጀመሩት ከባቢሎን ምርኮ ወደ ይሁዳ ምድር ከተመለሱ በኋላ ነበር።
  • “አይሁድ” የሚለው ቃል የመጣው ከ፣ “ይሁዳ” ነው። ወደ ባቢሎን የተወሰዱ እስራኤላውያን፣ ከደቡባዊው የይሁዳ መንግሥት የመጡ ነበሩ።
  • መሲሑ ኢየሱስ አይሁድ ነበር። ይሁን እንጂ፣ የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ኢየሱስን መቀበል አልፈለጉም፤ እንዲያውም እንዲገደል ጠየቁ።

ፈራጅ፣ ፍርድ

ብዙውን ጊዜ፣ “ፈራጅ” ወይም፣ “ፍርድ” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት ከግብረ ገብ አንጻር አንድ ነገር ትክክል መሆን አለመሆኑን በተመለከተ ውሳኔ መስጠት ነው።

  • “የእግዚአብሔር ፍርድ” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው እርሱ ኀጢአት በሚለው ሰው ወይም ነገር አስመልክቶ ፍርድ ለማሳለፍ የሚያደርገውን ውሳኔ ነው።
  • ሁሌም ቢሆን የእግዚአብሔር ፍርድ በኀጢአታቸው ሰዎችን መቅጣቱን ይጨምራል።
  • “መፍረድ” የሚለው ቃል፣ “መኮነን” ማለት ሊሆንም ይችላል። በዚህ መልኩ ማንም ላይ እንዳይፈርዱ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ተናግሯል።
  • ሌላው ትርጉም፣ በሰዎች መካከል በሚፈጠር ክርክር የትኛው ትክክል የትኛው ስሕተት እንደሆነ፣ “በሁለቱ መካከል መዳኘት” ማለት ነው።
  • በአንዳንድ ዐውዶች መሠረት የእግዚአብሔር፣ “ፍርድ” እርሱ ትክክልና እውነት ብሎ የወሰነው ማለት ነው። በዚህ መልኩ ሲቀርብ ከእርሱ ሕግ፣ ደንብ ወይ ሥርዓት ጋር አንድ ዐይነት ትርጉም ይኖረዋል።
  • “ፍርድ” ማስተዋል ያለበት ውሳኔ የማድረግ ችሎታን ያመለክታል። “ፍርድ” የሌለው ሰው ማስተዋል ያለበት ችሎታ የመወሰን ትበብ የሌለው ማለት ነው።

የፍርድ ቀን

“የፍርድ ቀን” እግዚአብሔር በማንኛውም ሰው ላይ የሚፈርድበት ወደፊት የሚመጣ ጊዜ ነው።

  • ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስን እግዚአብሔር በሰዎች ሁሉ ላይ ፈራጅ ወይም ዳኛ አድርጎታል።
  • በፍርድ ቃን ክርስቶስ እንደሥራቸው መጠን በሰዎች ላይ ይፈርዳል።

ትክክል፣ ፍትሕ፣ በፍትሕ

እነዚህ ቃሎች የሚያመለክቱት በእግዝአብሔር ቃል መሠረት ሰዎችን በአግባቡ መያዝን ወይም ማስተናገድን ነው። ትክክል የሆነውን የእግዚአብሔር መስፈርት የሚያንጸባርቁ የሰው ልጆች ሕጎችም ፍትሕ ይባላሉ።

  • “ፍትሕ ማድረግ” ለሌሎች ቀና የሆነውን ትክክል የሆነውን ነገር ማድረግ ማለት ነው። ከግብረ ገባዊ ይዘቱ አንጻር በእግዚአብሔር ፊት ቅንነትና ታማኝነት ያለበት ነገር ማድረግንም ይጨምራል።
  • “በፍትሕ” መፍረድ በእግዚአብሔር ሕግ መሠረት ትክክል፣ መልካምና አግባብ በሆነ ሁኔታ ሰዎችን ማስተናገድ ማለት ነው።
  • “ፍትሕ” ማግኘት በሕጉ መሠረት በአግባቡ መስተናገድ፣ ከሕጉ ከለላ ማግኘት ወይም ሕጉን በመተላለፍ መቀጣት ማለት ነው።
  • አንዳንዴ፣ “ትክክል” የሚለው ቃል ሰፋ ባለ መልኩ፣ “ጻድቅ” ወይም፣ “የእግዚአብሔርን ሕግ መከተል” የሚል ትርጉም ይኖረዋል።

የእግዚአብሔር መንግሥት፣ መንግሥተ ሰማይ

“የእግዚአብሔር መንግሥት” እና፣ “መንግሥተ ሰማይ” የሚሉት ሁለቱም የሚያመለክቱት በሕዝቡና በፍጥረት ሁሉ ላይ እግዚአብሔር ያለውን አገዛዝ ነው።

  • ስሙን በቀጥታ ላለ መጥራት ብዙ ጊዜ አይሁድ፣ “ሰማይ” የሚለውን ቃል የሚጠቀምበት እግዚአብሔርን ለማመልከት ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ከማቴዎስ ወንጌል እንደምንመለከተው “የእግዚአብሔር መንግሥትን” – “መንግሥተ ሰማይ” በማለት ጠርቶታል፤ ይህን ያደረገው እየጻፈ የነበረው በዋነኛነት ለአይሁድ ስለሆነ ይሆናል።
  • የእግዚአብሔር መንግሥት የቁሳዊው ዓለም ገዢ እንደ ሆነ ሁሉ በመንፈሳዊ ደረጃም እግዚአብሔር ሕዝቡን እየገዛ እንደ ሆነ ያመለክታል።
  • በጽድቅ እንዲገዛ እግዚአብሔር መሲሑን እንደሚልክ ብሉይ ኪዳን ይናገራል። የእግዚአብሔር ልጅ መሲሑ ኢየሱስ በእግዚአብሔር መንግሥት ለዘላለም ይገዛል።

የአይሁድ ንጉሥ

  • የአይሁድ ንጉሥ” የተሰኘው የኢየሱስ የመሲሑ መጠሪያ ነው።
  • ይህ ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው፣ “የአይሁድ ንጉሥ” የሆነውን ሕፃን ለመፈለግ ሰብዓ ሰገል ወደ ቤተ ልሔም የመጡ ጊዜ ነበር።
  • ከእርሷ የሚወለደው ልጅ የንጉሥ ዳዊት ዘር እንደሆነና ለመንግሥቱም ፍጻሜ እንደሌለው መልአኩ ለማርያም ነግራት ነበር።
  • ኢየሱስ ከመሰቀሉ በፊት የሮም ወታደሮች እያፌዙ፣ “የአይሁድ ንጉሥ” በማለት ጠርተውታል። ይህ መጠሪያ እንጨት ላይ ተጽፎ ኢየሱስ የተሰቀለበት መስቀል ጫፍ ላይ እንዲሆን ተደርጎ ነበር።
  • ኢየሱስ በእውነት የአይሁድ ንጉሥ ነው፤ እርሱ በፍጥረት ሁሉ ላይ ንጉሥ ነው።

በግ፣ የእግዚአብሔር በግ

በግ ጥቅጥቅ ያሉ ለሱፍ መሥሪያ የሚያገለግሉ ጠጉሮች ያሉት ባለ አራት እግር እንስሳ ሲሆን፣ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይቀርባል። እርሱ ለሕዝቡ ኃጢአት መሥዋዕት ሆኖ በመሞቱ ኢየሱስ፣ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሏል።

  • በግ በቀላሉ የሚባዝን እንስሳ በመሆኑ ጥበቃና ክትትል ያስፈልገዋል። እግዚአብሔር የሰው ልጆችን በበጎች መስሎአቸዋል።
  • ንጹሕና ጉድለት የሌለባቸው በጎችን ለእርሱ መሥዋዕት እንዲያቀርቡ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ተናግሮአል።
  • ኢየሱስ ለሕዝቡ ኀጢአት ዕዳ ለመክፈል መሥዋዕት የሚሆን፣ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሏል። እርሱ ምንም ኀጢአት የሌለበት በመሆኑ ፍጹምና ንጹሕ መሥዋዕት ነው።

ዋይታ፣ ሰቆቃ

“ዋይታ” እና፣ “ሰቆቃ” የተሰኙት ቃሎች የከባድ ለቅሶ፣ ሕዘን ወይም ትኬ መገለጫዎች ናቸው።

  • አንዳንድ ይህ በኀጢአት በጣም መፀፀትን ወይም ጥፋት ለደረሰባቸው ሰዎች መራራትን ይጨምራል።
  • ሰቆቃ በሕመም ማቃሰትን፣ ማልቀስን ወይም እንጉርጉሮን ሊያካትትት ይችላል።

የመጨረሻ ቀን፣ የመጨረሻዎቹ ቀኖች፣ የኋለኞቹ ቀኖች

“የመጨረሻ ቀን” ወይም፣ “የመጨረሻዎቹ ቀኖች” በአጠቃላይ የሚያመለክቱት በአጠቃላይ ኢየሱስ ወደሚመለስበት ጊዜ የሚያደርሱ ወቅቶች ናቸው።

  • ለዚህ ጊዜ ርዝመት አይታወቅም።
  • “የመጨረሻው ቀን” - መጨረሻ ላይ የሚሆነው የትንሣኤና የፍርድ ጊዜ ነው።
  • “በመጨረሻው ቀን” ከሞት እንደሚያስነሣቸው ኢየሱስ ለተከታዮቹ ተናግሯል።

ሕግ፣ የሙሴ ሕግ፣ የእግዚአብሔር ሕግ፣ የያህዌ ሕግ

እነዚህ ቃሎች ሁሉ እስራኤላውያን እንደታዘዟቸው እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠውን ትእዝዞችና ትምህሮች የሚያመልክቱ ናቸው። “ሕጉ” እና፣ “የእግዚአብሔር ሕግ” የተሰኙት በአጠቃላይ እግዚአብሔር ሕዝቡ እንዲታዘዙ የሚፈልጋቸው ማንኛውንም ነገር ያመለክታሉ።

  • እንደ ዐውዱ ሁኔታ፣ “ሕጉ”
  • እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን በድንጋይ ጽላትች ላይ ያጻፋቸው አሥሩን ትእዛዞችን.
  • ለሙሴ የተሰጡትን ሕጎች ሁሉ፣
  • የመጀመሪያዎቹን አምስት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “ቅዱሳት መጻሕፍት” የተባሉትን መላው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን፥
  • የእግዚአብሔርን ትምህርትና ፈቃድ ሁሉ ሊያመለክት ይችላል።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “ሕግና ነቢያት” የተሰኘው ሐረግ ጥቅም ላይ የዋለው የዕብራውያን ቅዱሳት መጻሕፍትን ወይም ብሉይ ኪዳንን ለማመልከት ነው።

ሕይወት፣ ሕያው፣ ሕይወት

እነዚህ ቃሎች ሁሉ የሚመለከቱት በሕይወት መሆንን፣ አለመሞትን ነው። መንፈሳዊ ሕያውነትን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላሉ። “ሥጋዊ ሕይወት” እና፣ “መንፈሳዊ ሕይወት” ሁለቱም ሕይወት ቢሆኑም፣ አንዱ ጊዜያዊ ሌላው ግን ዘላለማዊ ነው።


ጌታ፣ አዛዥ፣ አለቃ

“ጌታ” የሚለው ቃል ሰዎች ላይ ባለቤትነት ወይም ሥልጣን ያለውን ሰው ያመለክታል።

  • አንዳንዴ ቃሉ ኢየሱስን ወይም ባሪያ አሳዳሪ ሰውን ለማመልከት ሲፈልግ፣ “አዛዥ” ተብሎ ይተረጎማል።
  • ከፍ ያለ የሥልጣን ደረጃ ያለውን ሰው በጨዋነት በሚጠራበት ዐውስ ውስጥ አንዳንድ ትርጕሞች “አለቃ” በሚል ተርጉመውታል።

የጌታ እራት

“የጌታ እራት” የሚለውን ቃል ሐዋርያው ጳውሎስ የተጠቀመበት በአይሁድ መሪዎች በተያዘበት ሌሊት ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የበላውን የፋሲካ ምግም ለማመልከት ነበር።

  • ምግቡን እየበሉ ሳሉ ኢየሱስ የፋሲካውን እንጀራ ቆራርሶ በቅርሱ የሚገረፍና የሚገደል የእርሱ አካል እንደ ሆነ ተናገረ።
  • ጽዋው ውስጥ የነበረውንም ወይን እርሱ ለኀጢአት መሥዋዕት ለመሆን ሲሞት የሚፈስሰው የእርሱ ደም እንደ ሆነ ተናገረ።
  • በአንድነት ሆነው ተከታዮቹ ይህን ምግብ በበሉ ጊዜ ሁሉ ሞትና ትንሣኤውን እንዲያስታውሱ ኢየሱስ አዘዘ።
  • ለቆሮንቶስ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ ሐዋርያው ጳውሎስም የጌታ እራት በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች ዘወትር ሊያደርጉት እንደሚገባ በተጨማሪ አጠናከረ።
  • በዚህ ዘመን ያሉ አንዳንድ ቤተ ክርስቲያኖች የጌታን እራት ብዙ ጊዜ፣ “ኅብረት” በማለት ይጠሩታል። “የመጨረሻው እራት” የሚለው ሐረግም አንዳንዴ ጥቅም ላይ ይውላል።

ጌታ ያህዌ፣ ያህዌ አምላክ

እንዱ እውነተኛ አምላክን በተመለከተ እነዚህ ቃሎች ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሰዋል።

  • “ጌታ” የሚለው ስም መጠሪያ ሲሆን፣ “ያህዌ” ግን የእግዚአብሔር የተፀውዖ ስስም ነው።
  • “ያህዌ” የተሰኘው የእግዚአብሔር የተፀውዖ ስም፣ “ያህዌ አምላክ” ለማለት “አምላክ” ከሚለው ጋር ብዙ ጊዜ ይያያዛል።

ፍቅር

አንድን ሰው መውደድ ለዚያ ሰው ማሰብና መጠንቀቅ እንዲሁም ለእርሱ የሚጠቅመውን ነገር ማድረግ ነው። “ፍቅር” የተለያዩ ትርጕሞች አሉት፤ አንዳንድ ቋንቋዎች በተለያዩ ቃሎች ይገልጹታል። 1. ከእግዚአብሔር የሚመጣው ፍቅር ምንም እንኳ ራስን የሚጠቅም ባይሆንም ሌሎችን መጥቀም ላይ ያተኩራል። ምንም ያድርጉ ምን ይህ ፍቅር ለሌሎች ያስባል፣ ለሌሎች ይጠነቃቃል። እግዚአብሔር ራሱ ፍቅር ነው፤ የእውነተኛ ፍቅር ምንጭም እርሱ ነው።

  • እኛን ከኀጢአትና ከሞት ለማዳን ሕይወቱን መሥዋዕት በማድረግ ኢየሱስ ያሳየው ይህ ዐይነቱን ፍቅር ነበር። መሥዋዕት እስከ መሆን ድረስ ሌሎቹን መውደድ እንዳለባቸው ለተከታዮቹ አስተምሯል።
  • በዚህ ዐይነቱ ፍቅር ሰዎች ሌሎቹን ሲወዱ የሌሎችን ማደግና መሻሻልንም መወደዳቸውን የሚያሳይ ተግባርም ያደራሉ። ሌሎችን ይቅር የሚል ልብም ይኖራቸዋል።
  1. ሌላው የአዲስ ኪዳን ቃል የወንድማማችነት ፍቅርን ወይም ጓደኛን ወይም ቤተ ሰብን ማፍቀርን የሚመለከተው ነው።
  • ይህ ቃል የሚያመለክተው በጓደኛሞች ወይም በዘመዳሞች መካከል ያለውን ተፈጥሮአዊና ሰብዓዊ ፍቅርን ነው።
  • “በግብዣም በከበሬታ ቦታ መቀመጥ ያፈቅራሉ (ይወዳሉ)” በሚለው ዐውድ ውስጥም ጥቅም ላይ ውሏል። ይህም ማለት ያንን የማድረግ ከፍ ያለ ፍላጎት ወይም ምኞት አላቸው ማለት ነው።
  1. “ፍቅር” የሚለው ቃል በወንድና በሴት መካከል ያለውን መሳሳብና ማደድንም ያመለክታል። 4. “ያዕቆብን ወደድሁ (አፈቀርሁ) ኤሳውን ግን ጠላሁ” በሚለው አነጋገር ውስጥ፣ “ወደድሁ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብ ከእርሱ ጋር የኪዳን ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር መምረጡን ነው። ስለዚህ እዚህ ላይ ይህ ቃል፣ “መረጥሁ” ተብሎ መተርጎም ይችላል ማለት ነው። ምንም እንኳ ኤሳውም በእግዚአብሔር ቢበክም፣ ከእርሱ ጋር ኪዳን የማድረግን መብት አላገኘም። “ጠላሁ” የሚለውም ቃል፣ “አልፈለግሁትም” ወይም፣ “አልመረጥሁም” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።

ግርማ

ብዙውን ጊዜ “ግርማ” ከንጉሥ ክብር ጋር በተያያዘ መልኩ ትልቅነትንና ውበትን ነው የሚያመለክተው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ግርማ” በተደጋጋሚ የማመለክተው በአጽናፈ ዓለሙ እጅግ የላቀ ንጉሥ የሆነው የእግዚአብሔርን ታላቅነት ለማመልከት ነው።
  • “ግርማዊ ሆይ” አንድ ንጉሥ የሚጠራበት መንገድ ነው።

መና

መና ከግብፅ ከወቱ በኋላ እስራኤል በምድረ በዳ ይንከራተቱ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሰጣቸው እንጀራ የመሰለ ስስ ምግብ ነበር።

  • መና በየጥዋቱ መሬት ላይ ካለው ጤዛ ነጭ ቅርፊት ይገኝ ነበር። ከሰንበት በቀር እስራኤላውያን በየዕለቱ ይሰበስቡት ነበር፤ ምን ጊዜም ሰውን ሁሉ ለመመገብ ይበቃ ነበር።
  • ከሰንበት በፊት በነበረው ቀን ሁለት ዕጥፍ መና መሰብሰብ እንዳለባቸው እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሮ ነበር፤ እንዲህ የሚያደርጉት በሰንበት ቀን መሰብሰብ ስለማይገባ ነበር።
  • “መና” ማለት፣ “ይህ ምንድን ነው?” ማለት ነው።

ምሕረት፣ መሐሪ

“ምሕረት” እና፣ “መሐሪ” የተሰኙት ቃሎች ችግር ውስጥ በተለይም እጅግ በተዋረደ ዝቅረኛ ደረጃ ያሉ ሰዎችን መርዳትን ያመለክታሉ።

  • ባደረጉት ጥፋት መሠረት ሰዎችን አለመቅጣትም፣ “ምሕረት” ማድረግ ነው።
  • ንግሥን የመሰለ አንድ ብርቱ ሰው ሰዎችን ከመበደል ይልቅ መልካም ካደረገላቸው ያ ሰው፣ “መሐሪ” ይባላል።
  • የበደለንን ሰው ይቅር ማለትም መሐሪነት ነው።
  • ችግር ውስጥ ያሉ ሰዎችን ስንረዳ ምሕረት ማሳየታችን ነው።
  • እግዚአብሔር እኛን ምሮናል፤ እኛም ሌሎችን እንድንምር ይፈልጋል።

አገልጋይ፣ አገልግሎት

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “አገልጋይ” እና፣ “አገልግሎት” የተሰኙት ቃሎች እግዚአብሔርን በተመለከተ ሰዎችን በማስተማር፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታቸውም በማሰብ ሌሎችን መርዳት ማለት ነው። በዚህ መልኩ ሰዎችን የሚረዳ ሰው አገልጋይ ይባላል።

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን ለእርሱ መሥዋዕት በማቅረብ ካህናት ቤተ መቅደስ ውስጥ እግዚአብሔርን ያገለግሉ ነበር።
  • አገልግሎታቸው የቤተ መቅደሱን ሥራ ማከናወንና ስለ ሌሎች ወደ እርሱ መጸለይህንም ያካትታል።
  • በአዲስ ኪዳን፣ የውንጌል፣ “አገልጋይ” በኢየሱስ በማመን የሚገኘው የመዳንን ቃል ለሰዎች የሚያስተምር ሰው ነው። አንዳንዴ አገልጋይ፣ “ባርያ” ተብሎም ይጠራል።
  • ሰዎችን የማገልገሉ ሥራ ስለ እግዚአብሔር ለሰዎች በማስተማር በመንፈሳዊ ሕይወታቸው መርዳትም ያካትታል።
  • ለሕመምተኞች ጥንቃቄ በማድረግና ለድኾች ምግብ በመስጠት ቁሳዊ በሆነ መንገድ ሰዎችን ማገልገልንም ያመለክታል።

ተአምር፣ ድንቅ፣ ምልክት

“ተአምር”እግዚአብሔር ራሱ ካላደረገው በቀር ጨርሶ ሊሆን የማይችል አስደናቂ ነገር ነው።

  • ኢየሱስ ያደረጋቸው ተአምራት፣ ባሕርን ጸጥ ማሰኘትናን የዕውሩን ዐይን መክፈትንም ያካትታሉ።
  • ሰዎችን በመደነቅና በመገረም ስለሚሙ “ተአምራት” አንዳንዴ፣ “ድንቆች” ተብለው ይጠራሉ።
  • “ድንቅ” የሚለው ቃል አጠቃላይ በሆነ ሁኔታ የእግዚአብሔር ኀይልን መገለጥ ለምሳሌ፣ ሰማይና ምድርን በመፍጠር የተገለጠው ኀይሉን ያመለክታል።
  • የእግዚአብሔርን ኀያልነትና አጽናፈ ዓለሙ ላይ ያለውን ፍጹም ሥልጣን የሚያሳዩ ወይም ማስረጃ የሚሆኑ ከመሆናቸው የተነሣ ተአምራት፣ “ምልክቶች” ተብለውም ይጠራሉ።
  • የእስራኤልን ከግብፅ መውጣት፣ የዳንኤልን ከአንበሶች አፍ መዳን እንደ መሳሰሉት ነገሮች አንዳንድ ትአምራት የእግዚአብሔር ማዳን ሥራዎች ናቸው።
  • በኖኅ ዘመን በምድር ሁሉ ላይ የጥፋት ውሃ ማምጣቱን፣ በሙሴ ዘመን በግብፅ ምድር መቅሠፍት ማምጣቱን የመሳሰሉ ሌሎች ድንቆች የእግዚአብሔር ፍርድ ሥራዎች ናቸው።
  • አብዛኞቹ የእግዚአብሔር ተአምራት በሽተኞችን መፈሰስ ወይም የሞቱ ሰዎችን ማስነሣት ናቸው።
  • ሰዎችን ሲፈውስ፣ ባሕርን ጸጥ ሲያደርግ፣ በባሕር ሲራመድ፣ የሞቱ ሰዎችን ሲያስነሣ የእግዚአብሔር ኀይል በኢየሱስ አማካይነት ተገልጧ። አንዚህ ሁሉ ተአምራት ናቸው።
  • የፈውስ ተአምራትንና በእግዚአብሔር ኀይል ብቻ የሚቻሉ ነገሮችን እንዲያደርጉ ለነቢያትና ለሐዋርያት ተአምራት የማድረግ ችሎታን ሰጥቷቸው ነበር።

ልዑል እግዚአብሔር

“ልዑል እግዚአብሔር” ከእግዚአብሔር መጠሪያዎች አንዱ ሲሆን፣ የእርሱን ታላቅነትና ሥልጣን ያመለክታል።

  • የዚህ ቃል ትርጕም፣ “ሉዓላዊ” ወይም፣ “እጅግ የላቀ” ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ነው።
  • እዚህ ላይ፣ ልዑል (ከፍ ያለ) የሚለው የሚያመለክተው ቁሳው ከፍታ ወይም ርቀትን ሳይሆን፣ ታላቅነትን ነው።

ከርቤ

ከርቤ ከተለየ ዐይነት ዛፍ ሙጫ የሚዘጋጅ ቅመም ነው።

  • የሞተ ሰው አካልን ለቀብር ለማዘጋጀት ከሬ እንደ ዕጣን፣ ሽቱና ጣፋጭ መዓዛ ያለው ቅመም ያገለግል ነበር።
  • ከርቤ ጠቢባኑ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ ካቀረቡለት ስጦታዎች አንዱ ነበር።
  • ኢየሱስ በተሰቀለ ጊዜ ስቃዩን ለማስታገሥ ከወይን ጋር የተቀላቀለ ከርቤ እንዲጠጣ ሰጥተውት ነበር።

ስም

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስም በተለያዩ ምሳሌያዊ አነጋገርና ጥቅም ላይ ውሏል።

  • በአንዳንድ ዐውዶች፣ “ስም” የሰውን ዝና ሊያመለክት ይችላል፤ ለምሳሌ፣ “ስማችንን እናስጠራው” እንደሚለው።
  • “ስም” የአንድ ነገር መታሰቢያን ሊያመለክትም ይችላል፤ ለምሳሌ፣ “የጣዖቶችን ስም ማጥፋት” ሲል ከእንግዲህ ማንም እንዳያስታውሳቸው ወይም እንዳያመልካቸው እንዚያን ጣዖቶች መደምሰስ ማለት ነው።
  • “በእግዚአብሔር ስም መናገር” እርሱን በመወከል በእርሱ ኀይልና ሥልጣን መናገር ማለት ነው።
  • የአንድ ሰው፣ “ስም” የሰውየውን ሙሉ ማንነት ሊያመለክት ይችላል፤ ለምሳሌ፣ “እንድንበት ዘንድ ለሰዎች የተሰጠ ከዚህ ስም በስተቀር ሌላ ስም ከሰማይ በታች የለምና” እንደሚለው።

ናዝራዊ፣ የናዝራዊ ስእለት

ናዝራዊ የሚባለው ናዝርውያን የሚሳሉትን ስእለት የተሳለ ሰው ነው።

  • የናዝራዊ እስለት ከማንኛውም ከወይን የተሠራ መጠጥም ሆነ ምግብ መታቀብን፣ በስምምነት እስከ ተወሰነ ቀን ድረስ ማለት ሳምንቶች ወይም ወሮች ሊሆኑ ይችላሉ ጠጕርን አለመስተካከልን ይጨምራል። ወደ ሞተ ሰው አካል እንዳይቀርብም ይከለከላል።
  • የተወሰነው ጊዜ ሲያበቃና ስእለቱም ሲፈጸም ናዝራዊው ወደ ካህን ሄዶ ቁርባን ያቀርባል። ጠጕሩን መቆረጥና ማቃጠልን ያካትትም ይሆናል። ሌሎች ገደቦች ሁሉ ይነሣሉ።
  • የናዝራዊ ስእለትን በተመለከተ ሳምሶን በጣም የታወቀ የብሉይ ኪዳን ሰው ነው።
  • መጥምቁ ዮሐንስም በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የናዝራዊ ስእለት የነበረበት ሰው ሳይሆን አይቀርም።
  • ሐዋርያው ጳውሎስም አንድ ወቅት ላይ ይህን ስእለት ሳያደርግ አልቀረም።

ምሳሌ

ምሳሌ ግብረ ገባዊ ወይም ሃይማኖታዊ ትምህርት ለማስተማር የሚቀርብ አጭር ታሪክ ነው።

  • ደቀ መዛሙርቱን ለማስተማር ኢየሱስ ምሳሌዎች አቅርቦ ነበር።

ፋሲካ (ማለፍ)

ፋሲክ እግዚአብሔር አባቶቻቸው እስራኤላውያንን እንዴት ከግብፅ ባርነት እንዳዳናቸው ለማሰብ አይሁድ በየዓመቱ የሚያከብሩት ሃይማኖታዊ በዓል ስም ነው።

  • የዚህ በዓል ስም የመጣው፣ የግብፃውያንን የመጀመሪያ ወንድ ልጅ ሲገድል እግዚአብሔር የእስራኤላውያንን ቤት፣ “አለፈ” ልጆቻቸውንም አልገደልም ከሚለው ታሪክ ነው።
  • የፋሲካ አከባበር ምንም ጉድለት የሌለበት በግ በማረድ፣ ሥጋውን ጠብሶ ልዩ ዓይነት ምግብ ማዘጋጀትንና እርሾ የሌለበት እንጀራ መብላትንም ይጨምራል። ይህ ምግብ ከግብፅ ከመውጣታቸው በፊት በነበረው ሌሊት እስራኤላውያን ተመግበውት ስለ ነበረው ምግብ ያስታውሳቸዋል።
  • እግዚአብሔር ቤቶቻቸውን “እንዳለፈና” በእንዴት ዓይነት ሁኔታ ከግብፅ ባርነት እንዳዳናቸው እንዲያስታውሱ በየዓመቱ ፋሲካን እንዲያከብሩ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሮአል።

ፓስተር

“ፓስተር” የሚለው ቃል በቃል፣ “እረኛ” ከሚለው ጋር አንድ ነው። የአማኞች ስብስብ መንፈሳዊ መሪ ለሆነ ሰው የሚሰጥ ስም ነው።

  • በእንግሊዝኛው መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ፓስተር” የሚለው ቃል በኤፌሶን መልእክት አንድ ጊዜ ብቻ ሲጠቀስ፣ በሌሎች ክፍሎች ግን፣ “እረኛ” ተብሎ ተተርጕሞአል።
  • በሌሎች ቋንቋዎች “ፓስተር” የሚለው ቃል፣ “እረኛ” ከሚለው ቃል ጋር አንድ ነው።
  • ኢየሱስ፣ “መልካም እረኛ” እንደ ሆነ ሲናገር የተጠቀመው በዚሁ ቃል ነው።

ጴንጠቆስጤ (በዓለ ሃምሳ)፣ የሳምንቶች በዓል

በዓለ ሃምሳ ከፋሲካ ሃምሳ ቀን በኋላ የሚከበረው የአይሁድ በዓል ግሪክኛ ስም ነው።

  • የጴንጠቆስጤ ቀን የሳምንቶች በዓል የመጀመሪያው ቀን ነበር።
  • የሳምንቶች በዓል የሚከበረው የመከር ጊዜ ማብቂያን ለማሰብ ነው። በሙሴ በኩል እግዚአብሔር ሕጉን ለእስራኤላውያን በመጀመሪያ መስጠቱ የሚታሰብበት ጊዜ ነው።
  • ኢየሱስ ከሞት ከተነሣና ወደ ሰማይ ከተመለሰ በኋላ እግዚአብሔር በኢየሱስ ተከታዮች ላይ መንፈስ ቅዱስን ያፈሰሰው በዚህ ቀን በመሆኑ የጰንጠቆስጤ ቀን በአዲስ ኪዳን የተለየ ግምት ይሰጠዋል።

የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ ሕዝቤ

“የእግዚአብሔር ሕዝብ” የተሰኘው ሐረግ ከእርሱ ጋር የተለየ ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር ከዓለም የጠራውን ሕዝብ ነው።

  • እግዚአብሔር፣ “ሕዝቤ” ሲል እርሱ ስለ መረጠውና ከእርሱ ጋር ግንኙነት ስላለው ሕዝብ መናገሩ ነው።
  • የእግዚአብሔር ሕዝብ በእርሱ ተመርጠዋል፤ እርሱን ደስ በሚያሰኝ መንገድ እንዲኖሩ ከዓለም ተለይተዋል። ልጆቼ በማለትም ይጠራቸዋል።
  • በብሉይ ኪዳን፣ “የእግዚአብሔር ሕዝብ” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር የተመረጡትንና እርሱን ለማገልገልና ለእርሱ ለመታዘዝ ከዓለም ሕዝብ መካከል ተለይተው የወቱትን የእስራኤል ሕዝብ ነው።
  • በአዲስ ኪዳን፣ “የእግዚአብሔር ሕዝብ” በተለየ ሁኔታ የሚያመለክተው በኢየሱ የሚያምኑትን ሁሉ ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያን ተብለውም ይጠራሉ። ይህም አይሁድንና አሕዛብንም ይጨምራል።

መጥፋት፣ ጥፋት፣ የሚጠፋ

“መጥፋት” የሚለው ቃል አብዛኛውን ጊዜ በአንድ ዓይነት ጥቃት ወይም አደጋ የተነሣ መሞት ወይም መደምሰስ ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለይ ለዘላለም በገሃነም መቀጣት የሚል ትርጕም አለው።

  • “የሚጠፋ” ሰዎች እንዲያድናቸው በኢየሱስ ማመን ባለመፈለጋቸው ለገሃነም የተወሰኑ ናቸው።
  • ዮሐንስ 3፡16፣ “መጥፋት” ለዘላለም በመንግሥተ ሰማይ አለመኖር መሆኑን ያስተምራል።

ፈሪሳዊ

ፈሪሳውያን ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ዘመን በጣም ታዋቂ የእስራኤል ሃይማኖት መሪዎች ነበር። አብዛኞቹ መካከለኛ ኑሮ ያላቸው ሠራተኞች ሲሆኑ፣ ጥቂቶቹም ካህናት ነበሩ።

  • ከአይሁድ መሪዎች ሁሉ ፈሪሳውያን፣ ለሙሴ ሕግና ለሌሎቹ የአይሁድ ሕጎችና ወጎች በመታዘዝ ረገድ ፈሪሳውያን በጣም ጠንካሮች ነበር።
  • የአይሁድ ሕዝብ በዙሪያው ከነበሩ አሕዛብ የተለየ ሆኖ እንዲዘልቅ በጣም ያስቡ ነበር። “ፈሪሳዊ” የሚለው ስም ራሱ፣ “መለየት” ከሚለው ቃል የመጣ ነበር።
  • ፈሪሳውያን ከሞት በኋላ ሕይወት መኖሩን ያምኑ ነበር፤ መላእክትና ሌሎች መንፈሳዊ ፍጥረቶች መኖራቸውንም ያምኑ ነበር።
  • የካህናት አለቆችን ጨምቶ ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን ኢየሱስንና የጥንት ክርስቲያኖችን አጥብቀው ይቃወሙ ነበር።

ኀይል፣ ኀይላት

“ኀይል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብዛኛውን ጊዜ በታላቅ ብርታት ነገሮችን ማድረግን ወይም ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ችሎታን ነው። “ኀይላት” የሚያመለክተው ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ታላቅ ችሎታ ያላቸው ሰዎችን ወይም መናፍስትን ነው።

  • “የእግዚአብሔር ኀይል” ማንኛውንም ነገር በተለይም ለሰዎች የማይቻሉ ነገሮችን ለማድረግ እግዚአብሔር ያለውን ችሎታ ያመለክታል።
  • እግዚአብሔር በፈጠረው ማንኛውም ነገር ላይ ፍጹም ኀይል አለው።
  • እርሱ የሚፈልገውን እንዲያደርጉ እግዚአብሔር ለእሕዝቡ ኀይል ይሰጣል፤ ስለዚህ በሽተኞችን ሲፈውሱ ወይም ሌሎች ተአምራት ሲያደርጉ ያንን ያደረጉት በእግዚአብሔር ለይል ነው ማለት ነው።
  • ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስም እግዚአብሔር በመሆናቸው ይኸው ኀይል አላቸው።

መጸለይ፣ ጸሎት

መጸለይ ለእግዚአብሔር መናገር ነው።

  • እነርሱን ወይም ሌሎችን እንዲረዳ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ይጸልያሉ።
  • ሰዎች በጸሎት እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፤ እርሱን ይወድሳሉ።
  • ጸሎት እርሱ ይቅር እንዲለን ኀጢአታችንን መናዘዝ ማለትም ነው።
  • ሰዎች ለጣዖቶቻቸው ሲናገሩ፣ ወደ እነርሱ “መጸለያቸው” ነው።

መወሰን፣ የተወሰነ

“መወሰን” እና፣ “የተወሰነ” የተሰኙት ቃሎች አንድ ነገር ከመሆኑ በፊት እንደዚያ እንዲሆን መቁረጥን ወይም ማቀድን ያመለክታሉ።

  • ብዙውን ጊዜ ቃሉ የዘላለምን ሕይወት እንዲያገኙ እግዚአብሔር ሕዝቡን መወሰኑን ያመለክታል።
  • አንዳንዴ፣ “ማቀድ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ይውላል፤ ያም አንድ ነገር ከመሆኑ በፊት አስቀድሞ መቁረጥን ነው የሚያመለክተው።

መንጠቅ፣ ንጥቂያ “መንጠቅ” የሚያመለክተው አንድን ነገር፣ ብዙውን ጊዜ ደግሞ ለምግብ የሚሆን እንስሳን ማደንን ነው።

  • ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ሲውል ጥቅሙን እንዲያጣ የተደረገውን፣ የእርሱ የሆነው አለአግባብ የተወሰደበትን ወይም በሌላ ኀያል በሆነ ሰው የሚጨቆን ሰውን ያመለክታል።
  • ሰዎች ላይ የሚፈጸም፣ “ንጥቂያ” እነርሱን በመጫን ወይም ከእነርሱ በመስረቅ የእነርሱን ጥቅም መውሰድ ማለት ነው።

ካህን፣ ክህነት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካህን ሕዝብን በመወከል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚያቀርብ ሰው ነው። “ክህነት” እንዲህ ላለው ሰው ተግባር የተሰጠ ስም ወይም ቦታ ነው።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ለእስራኤል ሕዝብ ካህናት እንዲሆኑ እግዚአብሔር አሮንና ልጆቹን መርጧል።
  • “ክህነት” በሌዋውያን ነገድ ውስጥ ከአባት ወደ ልጅ የሚተላለፍ መብትና ኀላፊነት ነበር።
  • የእስራኤል ካህናት ቤተ መቅደሱ ውስጥ ሌሎች ተግባሮችን መፈጸምን ጨምሮ የሕዝቡን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር የማቅረብ ኀላፊነት ነበራቸው።
  • ካህናት ለሕዝቡ ዘወትር ወደ እግዚአብሔር ይጸልዩና ሌሎች ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ይፈጽሙ ነበር።
  • ካህናት ወግ ባለው መልኩ ሕዝቡን ይባርካሉ፤ የእግዚአብሔርን ሕጎች ያስተምራሉ።
  • ኢየሱስ በዚህ ምድር ባገለገለበት ዘመን የካህናት አልቆችንና ሊቀ ካህኑን ጨምሮ የተለያዩ የካህናት ደረጃዎች ነበሩ።
  • ኢየሱስ በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ የሚማልድ፣ “ታላቅ ሊቀ ካህናችን” ነው። የመጨረሻው የኀጢአት መሥዋዕት ለመሆን ራሱን ሰጠ። ይህም ማለት ካህናት የሚያቀርቧቸው መሥዋዕቶች ከእንግዲህ አያስፈልጉም ማለት ነው።
  • በአዲስ ኪዳን መሠረት በኢየሱስ የሚያምን እያንዳንዱ አማኝ “ካህን” ነው፤ ለሱና ለሌሎች ለመማለድ በጸሎት በቀጥጣ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይችላል።
  • በጥንት ዘመን በአልን ለመሳሰሉ የሐሰት አማልክት መሥዋዕት የሚያቀርቡ አረማውያን ካህናትም ነበር።

ተስፋ ቃል

ተስፋ ቃል አንድን ነገር ለመስጠት ወይም ለማድረግ ቃል መግባት ማለት ነው። አንድ ሰው አንድ ነገር ለማድረግ ተስፋ ከሰጠ ያንን ለመፈጸም ይተጋል ማለት ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ስለ ገባው ብዙ ተስፋ ቃል አስፍሮአል።
  • ተስፋ ቃል ኪዳንን በመሳሰሉ ውል ያላቸው ስምምነቶች ሁነኛ ክፍል ነው።
  • ብዙ ጊዜ የተስፋ ቃል እውን እንደሚሆን መሐላም ይኖረዋል።

የተስፋ ምድር

“የተስፋ ምድር” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እንጂ በጠቅላላው መጽሐፍ ቅዱስ አይደለም። ለአብርሃምና ለዘሮቹ እንደሚሰጥ እግዚአብሔር ቃል የገባላት የምድረ ከነዓን አማራጭ ቃል ነው።

  • አብራም በዑር ከተማ በነበረ ጊዜ እንዲሄድና በከነዓን ምድር እንዲኖር እግዚአብሔር አዘዘው። እርሱና የእርሱ ዘሮች የሆኑት እስርኤላውያን ለብዙ ዓመታት እዚያ ኖሩ።
  • እዚያ ከደረሰው ድርቅ የተነሣ ራብ በሆነ ጊዜ እስራኤላውያን ወደ ግብፅ ሄዱ።
  • ክአራት መቶ ዓመት በዓላ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፅ ባርነት አውጥቶ እንደሚሰጣቸው እግዚአብሔር ወደ ገባላቸው ምድር ወደ ምድረ ከነዓን አመጣቸው።

ነቢይ፣ ትንቢት፣ ትንቢት ተናገረ፣ ተመልካች፣ ነቢዪት “ነቢይ” የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው። ይህን የምታደርግ ሴት ነቢዪት ትባላለች።

  • ነቢይ የሚለው የቀድሞ መጠሪያ፣ “ተመልካች” ሲሆን፣ “የሚያይ፣ የሚመለከት ሰው” ማለት ነው።
  • ይሁን እንጂ “ተመልካች” የሚለው ቃል አንዳንዴ ሟርተኛን ወይም ሐሰተኛ ነቢይንም ያመለክታል።
  • ምንጊዜም ነቢያት ሰዎች በኀጢአታቸው እንዲመለሱና ለእግዚአብሔር እንዲታዘዙ ያስጠነቅቃሉ።
  • “ትንቢት” ነቢዩ የሚናገረው መልእክት ነው። “ትንቢት መናገር” የእግዚአብሔርን መልእክት መናገር ማለት ነው።
  • ብዙውን ጊዜ የትንቢት መልእክት ወደ ፊት የሚሆነውን ያመለክታል።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያሉ ብዙ ትንቢቶች ተፈጽመዋል።
  • “ሐሰተኛ ነቢይ” በአልን ከመሳሰሉ ሐሰተኛ አማልክት ተቀብያለሁ የሚለውን መልእክት የሚናገር ወይም የእግዚአብሔር መልእክት እንደ ተቀበለ በውሸት የሚናገር ሰው ነው።

ነቢይ፣ ትንቢት፣ ትንቢት ተናገረ፣ ተመልካች፣ ነቢዪት

“ነቢይ” የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው። ይህን የምታደርግ ሴት ነቢዪት ትባላለች።

  • ነቢይ የሚለው የቀድሞ መጠሪያ፣ “ተመልካች” ሲሆን፣ “የሚያይ፣ የሚመለከት ሰው” ማለት ነው።
  • ይሁን እንጂ “ተመልካች” የሚለው ቃል አንዳንዴ ሟርተኛን ወይም ሐሰተኛ ነቢይንም ያመለክታል።
  • ምንጊዜም ነቢያት ሰዎች በኀጢአታቸው እንዲመለሱና ለእግዚአብሔር እንዲታዘዙ ያስጠነቅቃሉ።
  • “ትንቢት” ነቢዩ የሚናገረው መልእክት ነው። “ትንቢት መናገር” የእግዚአብሔርን መልእክት መናገር ማለት ነው።
  • ብዙውን ጊዜ የትንቢት መልእክት ወደ ፊት የሚሆነውን ያመለክታል።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያሉ ብዙ ትንቢቶች ተፈጽመዋል።
  • “ሐሰተኛ ነቢይ” በአልን ከመሳሰሉ ሐሰተኛ አማልክት ተቀብያለሁ የሚለውን መልእክት የሚናገር ወይም የእግዚአብሔር መልእክት እንደ ተቀበለ በውሸት የሚናገር ሰው ነው።

ማስተሰሪያ

“ማስተሰረያ” የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ፍትሕ ለማርካት ወይም ለመፈጸምና ቁጣውን ለማስታገሥ የሚቀርብ መሥዋዕት ነው።

  • በኢየሱስ ክርስቶስ ደም በኩል የቀረበው መሥዋዕት የሰውን ልጅ ኀጢአት ለማስተሰረይ የቀረበ ማስተሰሪያ ነው።
  • የኢየሱስ መስቀል ላይ ሞት ለሰው ልጅ ኀቲአት የእግዚአብሔር ማስተሰሪያ ነው። ይህም እግዚአብሔር ሰዎችን በምሕረት እንዲያይና ለእነርሱም የዘላለም ሕይወት ለመስጠት መንገድ ሆነ።

መዝሙር

ቅዱስ ዝማሬ፣ ብዙ ጊዜ በሙዚቃ የታጀበ ግጥም ወይም ቅኔ ማለት ነው። ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለው መጽሐፈ መዝሙር በእስራኤላውያን የተጻፉ የመዝሙሮች ስብስብ ይዟል።

  • ሙሴና ንጉሥ ዳዊት የእስራኤል ሕዝብ እግዚአብሔርን ሲያመልኩ የሚጠቀሙባቸው መዝሙሮች ጽፈዋል።
  • መዝሙራቶች እንደ ሐዘንና ጉዳት ሁሉ ደስታን፣ እምነትንና አክብሮትን ለመግለጥ ያገለግላሉ።
  • በአዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የአምልኮአቸው መገለጫ የሆኑ መዝሙሮች እንዲዘምሩ ተነግሮአቸዋል።

ንጹሕ፣ ማንጻት

“ንጹሕ” መሆን እንከን የሌለው ወይም እዚይ ኣመገኘት ያልነበረበት የተቀላቀለ ነገር የሌለው ማለት ነው። አንድን ነገር ማንጻት ማለት ንጹሕ ማድረግና የሚያቆሽሸውንና የሚበክለውን ማንኛውንም ነገር ማስወገድ ማለት ነው።

  • ከብሉይ ኪዳን ሕጎች አንጻር፣ “ማንጻት” በዋናነት ሕመምን፣ ከሰውነት የሚወጣ ፈሳሽን ወይም ልጅ መውለድን ከመሳሰሉ በሥርዓቱ ያረክሳሉ ከሚባሉ ነገሮች አንድ ነገር ወይም ሰው እንዲጠራ ማድረግ ማለት ነው።
  • ብሉይ ኪዳን ሰዎች እንዴት ከኀጢአት መንጻት እንደሚችሉ ይናገራል፤ ብዙውን ጊዜ ይህ የሚሆነው እንስሳን መሥውሳዕት በማድረግ ነበር። ይህም ለጊዜው ብቻ የሚያገለግል በመሆኑ መሥዋዕቱ በየጊዜው መደጋገም ነበረበት።
  • በአዲስ ኪዳን መሠረት መንጻት፣ የሚያመክተው ከኀጢአት መንጻትን ነው።
  • ሰዎች ሙሉ ብሙሉና ለዘለቄታው ከኀቲአት መንጻት የሚችሉት በኢየሱስና በእርሱ መሥዋዕትነት በመታመን ንስሐ በማድረግና የእግዚአብሔርን ይቅርታ በመቀበል ብቻ ነው።

ረቢ፣ ረቡኒ

ቃል በቃል፣ “ረቢ” – “ጌታዬ” ወይም፣ “መምህሬ” ማለት ነው።

  • የአይሁድ ሃይማኖት መምህር ይልቁንም፣ የእግዚአብሔር ሕግ መምህር የሆነ ሰው የሚጠራበት የክብር መጠሪያ ነበር።
  • መጥምቁ ዮሐንስንም ሆነ ኢየሱስን ደቀ መዛሙርቶቻቸው፣ “ረቢ” በማለት ይጠሯቸው ነበር።

ቤዛ

“ቤዛ” የሚለው ቃል በምርኮ የተያዘ ሰውን ለማስለቀቅ እንዲከፈል የተጠየቀ ገንዘብ ወይም ሌላ ነገር ያመለክታል።

  • “ቤዛ መሆን” በባርነት ወይም በእስር ያለ ሰውን ነጻ ለማድረግ መክፈል ወይም ራስን መሥዋዕት ማድረግ ማለት ነው። ይህም፣ መልሶ መግዛት” ማለት ሲሆን፣ “መዋጀት” ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ትርጕም አለው።
  • ኀጢአተኞችን ከኀጢአት ባርነት ነጻ ለማውጣት ቤዛ ለመሆን ኢየሱስ ራሱን ለሞት አሳልፎ ሰጠ። ለኀጢአታቸው ዋጋ በመክፈል እግዚአብሔር ሕዝቡን የመግዛቱ ተግባር በመጽሐፍ ቅዱስ “ቤዛነት” ይባላል።

ማስታረቅ፣ ዕርቅ

“ማስታረቅ” እና፣ “ዕርቅ” ቀድሞ እርስ በርስ ይጠላሉ በነበሩ ሰዎች መካከል፣ “ሰላም ማድረግ” ማለት ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ይህ ቃል በልጁ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ መሥዋዕት እግዚአብሔር ሰዎችን ከራሱ ጋር ማስታረቁን ያመለክታል።
  • በኀጢአት ምክንያት የሰው ልጆች ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ነበር። ከፍቅርና ርኅራኄው የተነሣ እግዚአብሔር በክርስቶስ በኩል ሰዎች ከእርሱ ጋር የሚታረቁበትን መንገድ አዘጋጀ።
  • የኢየሱስ መሥዋዕት ለኀጢአታችን የተከፈለ ዋጋ መሆኑን በማመን ሰዎች ይቅርታን አግኝተው ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ይኖራቸዋል።

መዋጀት

“መዋጀት” የሚለው ቃል በሌሎች ተወስዶ የነበረ ነገርን በመግዛት የራስ ማድረግ ማለት ነው።

  • ሰዎችን ወይም ነገሮችን እንዴት እንደሚዋጁ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ሕግ ሰጥቷል።
  • ለምሳሌ፣ ለእርሱ ዋጋ በመክፈል ባርያውን፣ “መዋጀት” ይቻላል። “ቤዛ” የሚለውም ቃል የሚያመለክተው ይህንኑ ነው።
  • የአንድ ሰው ርስት ከተሰጠ፣ ርስቱ ከቤተ ሰብ እንዳይወጣ የዚሃ ሰው ዘመድ፣ “ይዋጀዋል” ወይም፣ “እንደ ገና ይገዛዋል።”
  • እንዲህ ያሉት አሠራሮች የኀጢአት ባርያ የነበሩ ሰዎችን እግዚአብሔር በእንዴት ያለ ሁኔታ እንደ “ዋጀ” ያሳያሉ። መስቀል ላይ በሞተ ጊዜ ኢየሱስ የሰው ልጆችን ኀቲአት ዋጋ ከፈለ፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ሁሉ “ይዋጃቸዋል።” እግዚአብሔር የዋጃቸው ከኀጢአትና ከሚያስከትለው ቅጣት ነጻ ናቸው።

ትሩፍ፣ ትሩፋን

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ትሩፋን” ማለት፣ በጣም ብዙ ከሆነው ክፍል ወይም ወገን “የተረፉ” ወይም፣ “የቀሩ” ሰዎች ወይም ነገሮች ማለት ነው።

  • ብዙውን ጊዜ፣ “ትሩፋን” የሚያምለክተው ከአደገኛ ጥፋት የተረፉ ወይም በከፍተኛ ስደት ውስጥ እንኳ ለእግዚአብሔር ታማኝ የሆኑ ሰዎችን ነው።
  • ከውጪ ወራሪዎች ጥቃት ቢደርስባቸውም በሕይወት ኖረው ወደ ተስፋው ምድር የተመለሱትን አይሁድ ኢሳይያስ ትርፋን ይላቸዋል።
  • ጳውሎስ ጸጋውን ለመቀበል እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሰዎች፣ “ትሩፋን” ይላቸዋል።
  • “ትሩፋን” የሚለው ታማኝ ያልሆኑ ወይም በሕይወት ያልተረፉ ወይም ያልተመረጡ ሌሎች መኖራቸውን ያመለክታል።

ንስሐ መግባት፣ ንስሐ

“ንስሐ መግባት” እና፣ “ንስሐ” ከኀጢአት ወደ እግዚአብሔር መመለስን ያመለክታል።

  • ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ንስሐ መግባት” – “የአስተሳሰብ ለውጥ” ማለት ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ንስሐ ማድረግ” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ከኀጢአት መመለስን፣ ከሰብዓዊ አስተሳሰብና ሥራ ወደ እግዚአብሔር ሐሳብና ሥራ መመለስን ነው።
  • ሰዎች በኀጢአታቸው ከልባቸው ንስሐ ካደረጉ እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል፤ ለእርሱ መታዘዝ እንዲጀምሩም ይረዳቸዋል።

መመለስ፣ መታደስ

“መመለስ” እና፣ “መታደስ” አንድን ነገር ቀድሞ ወደ ነበረበት ቦታ፣ ወደ ተሻለ ሁኔታ መመለስ ማለት ነው።

  • አንድ የታመመ አካል፣ ከተመለሰ፣ ሕመሙ፣ “ድኗል” – “ተፈውሷል” ማለት ነው።
  • አንድ ደረጃ ላይ ተቋርጦ የነበረ ግንኙነት ወደ ነበረበት ቦታ ሲመለስ፣ “ዕርቅ” ሆኗል ማለት ነው። እግዚአብሔር ኀጢአተኞችን ይመልሳል፣ ወደ ራሱ መልሶ ያመጣቸዋል።
  • ሰዎች ወደ ትውልድ አገራቸው ከተመለሱ ተመልሰው መጥተዋል፣ ወደ አገራቸው፣ “ተመልሰዋል” ማለት ነው።

ትንሣኤ

“ትንሣኤ” ከሞት በኋላ ተመልሶ ወደ ሕይወት መምጣት ነው።

  • አንድን ሰው ማስነሣት ያንን ሰው እንደ ገና ወደ ሕይወት ማምጣት ማለት ነው። ያን የማድረግ ኀይል ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው።
  • ብዙውን ጊዜ፣ “ትንሣኤ” የሚያመለክተው ከሞት በኋላ ኢየሱስ ወደ ሕይወት መመለሱን ነው።
  • ኢየሱስ፣ “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ” ሲል፣ እርሱ የትንሣኤ ምንጭ መሆኑንና ሰዎችን መልሶ ወደ ሕይወት የሚያመጣ መሆኑን መናገሩ ነበር።

መግለጽ፣ መገለጽ (ራእይ)

“መግለጽ” አንድ ነገር እንዲታወቅ ማድረግ ማለት ነው “መገለጽ” እንዲታወቅ የተደረገ ነገር ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ አብዛኛውን ጊዜ “መገለጽ” የሚለው ጥቅም ላይ የዋለው እግዚአብሔር ራሱን ለሕዝቡ ማሳወቁን ለማመልከት ነው።
  • በፈጠረው ፍጥረት ሁሉና በቃልና በጽሑፍ በሰፈሩ መልእክቶች ከሰዎች ጋር ግንኙነት በማድረግ እግዚአብሔር ራሱን ገልጿል።
  • በሕልምና በራእይም እግዚአብሔር ራሱን ይገለጻል።
  • ወንጌልን የተቀበለው፣ “ከኢየሱስ ክርስቶስ ባገኘው መገለጥ” እንደ ነበር ጳውሎስ ሲናገር፣ ወንጌልን ግልጽ ያደረገለት ኢየሱስ ራሱ መሆኑን ማመልከቱ ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ የሚገኘው፣ “የዮሐንስ ራእይ” በመጨረሻው ዘመን ስለሚሆኑ ነገሮች እግዚአብሔር ስለ ሰጠው መገለጽ ይናገራል። ለሐዋርያው ዮሐንስ እነዚህን ነገሮች የገለጸው በራእይ ነበር።

ጻድቅ፣ ጽድቅ

“ጻድቅ” እና፣ “ጽድቅ” የእግዚአብሔር ፍጹም መልካምነት፣ ፍትሕ፣ ታማኝነትና ፍቅር ያመለክታል። እግዚአብሔር ጻድቅ ስለሆነ ኀጢአት ላይ መፍረድ አለበት።

  • አብዛኛውን ጊዜ ይህ ቃል ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና በግብረ ገባዊ ሕይወቱ መልካም የሆነ ሰውንም ሊያመለክት ይችላል። ይሁን እንጂ፣ ሰዎች ሁሉ ኀጢአት በማድረጋቸው፣ ከእግዚአብሔር በቀር ፍጹም ጻድቅ የሆነ ማንም የለም።
  • መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ጻድቃን” በማለት በሚጠራቸው ስሞች ዝርዝር ውስጥ ኖኅ፣ ኢዮብ፣ አብርሃም፣ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ይገኛሉ።
  • እርሱ እንዲያድናቸው ሰዎች በኢየሱስ ሲያምኑ፣ እግዚአብሔር ከኀጢአታቸው ያነጻቸዋል፤ ከኢየሱስ ጽድቅ የተነሣ እነርሱም ጻድቃን መሆናቸውንም ይናገርላቸዋል።

ቀኝ እጅ

“ቀኝ እጅ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር፣ በአንድ መሪ፣ ወይም ሥልጣን ባለው ሰው ቀኝ ያለውን የክብር ቦታ ያመለክታል።

  • ቀኝ እጅ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር፣ በአንድ መሪ፣ ወይም ሥልጣን ባለው ሰው ቀኝ ያለውን የክብር ቦታ ያመለክታል።
  • ቀኝ እጅ የኀይል፣ የሥልጣንና የብርታት ምሳሌ በመሆም ጥቅም ላይ ይውላል።
  • የአማኞች አካል ራስ እንደ መሆኑና ፍጥረትን ሁሉ የሚቆጣጠር እርሱ እንደ መሆኑ መጠን ኢየሱስ በእግዚአብሔር “ቀኝ እጅ” በኩል መቀመጡን መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል።
  • በረከት በሚቀበል ሰው ራስ ላይ ቀኝ እጅ ማድረግ ያ ሰው ያለውን ልዩ የክብር ቦታ ያመለክታል (ለምሳሌ እስራኤል የዮሴፍ ልጅ ኤፍሬምን ስባርክ እንደ ታየው)።
  • በአንድ ሰው “ቀኝ እጅ በኩል ማገልገል” አገልግሎቱ ለዚያ ሰው በጣም ጠቃሚና ተፈላጊ መሆኑን ያመለክታል።

ሰንበት

ሰንበት የሳምንቱ ሰባተኛ ቀን ነው፤ ይህ ቀን ምንም ሥራ የማይሠራበት የዕረፍት ቀን እንዲሆን እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዝዞ ነበር።

  • እግዚአብሔር ዓለምን የመፍጠር ሥራውን እንደጨረሰ በሰባተኛው ቀን ዐረፈ
  • በተመሳሳይ መንገድ ሰባተኛውን ቀን የዕረፍትና እርሱ የሚመለክበት የተለየ ቀን እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዘዘ
  • “ሰንበትን መቀደስ” በሁለት ድንጋይ ጽፎ እግዚአብሔር ለሙሴ ከሰጠው ዐሥሩ ትእዛዞች አንዱ ነው
  • በአይሁድ ቀን አቆጣጠር መሠረት ሰንበት አርብ ፀሐይ ሲጠልቅ ይጀምርና ቅዳሜ ፀሐይ ሲጠልቅ ያበቃል

ሰዱቃውያን

ሰዱቃውያን ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያላቸው የአይሁድ ካህናት ነበሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ባገለገለ ዘመን የነበረውን የሮም አገዛዝ ይደግፉ ነበር። በሙታን ትንሣኤ አያምኑም

  • ሰዱቃውያን እንደ የካህናት አለቆችና ሊቀ ካህናቱ ሀብታም የመሆንና ከፍ ያለ የመሪነት ቦታ የመያዝ ፍላጎት ነበራቸው
  • የሰዱቃውያን ተግባሮች የቤተ መቅደሱን ሕንፃ መንከባከብና መሥዋዕት ማቅረብንም ያካትታል
  • ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሰቀል በማድረግ ከፍ ያለ ድርሻ ነበራቸው
  • ራስ ወዳድና ግብዝ በመሆናቸው ኢየሱስ እነዚህ ሁለት የሃይማኖት ቡድኖችን ነቅፏል

ቅዱሳን

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ቅዱሳን” – “ቅዱስ የሆኑ ሰዎች” ማለት ሲሆን፣ በኢየሱስ ያመኑ ወገኖችን የመለክታል

  • ቆየት ብሎ በቤተክርስቲያን ታሪክ በመልካም ሥራቸው ለታወቁ ሰዎች፣ “ቅዱሳን” የሚል መጠሪያ ይሰጣቸው ጀመር፤ አዲስ ኪዳን ውስጥ ቃሉ ጥቅም ላይ የዋለው በዚህ መልኩ አይደለም
  • በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች ቅዱሳን የሆኑት እነርሱ ካደረጉት የተነሣ ሳይሆን፣ በኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ በማመናቸው ነው። ቅዱሳን ያደረጋቸው እርሱ ነው

መቀደ፣ ቅድስና

መቀደስ፣ ቅዱስ ይሆን ዘንድ አንድን ነገር መለየት ማለት ነው። ቅድስና ቅዱስ የመሆን ሂደት ነው

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን አንዳንድ ሰዎችና አንዳንድ ነገሮች ይቀደሱ ወይም ለእግዚአብሔር አገልግሎት ይለዩ ነበር
  • በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎችን እግዚአብሔር እንደሚቀድስ አዲስ ኪዳን ያስተምራል። ያም ማለት ቅዱስ ያደርጋቸዋል ለአገልግሎትም ይለያቸዋል ማለት ነው
  • በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች በሚያደርጉት ቅዱስ ለመሆን ራሳቸውን እንዲለዩ ታዝዘዋል

ቅዱስ ቦታ

“ቅዱስ ቦታ” ቃል በቃል እግዚአብሔር የሚቀደስበትና የሚመለክበት የተለይ ቦታ ማለት ነው። ከለላና ደኅንነት የሚገኝበትንም ቦታ ሊያመለክት ይችላል

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “ቅዱስ ቦታ” የሚለው ሐረግ አብዛኛውን ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው፣ “ቅድስት” እና፣ “ቅድስተ ቅዱሳን” ይገኙበት የነበረውን መገናኛ ድንኳን ወይም የቤተ መቅደሱን ሕንፃ ለማመልከት ነበር
  • ቅዱሱን ቦታ እግዚአብሔር በሕዝቡ በእስራኤል ማካከል የሚኖርበት ቦታ ብሎታል
  • ራሱንም፣ “ቅዱስ ቦታ” ወይም ሕዝቡ ከለላና ደኅንነት የሚያገኙበት ቦታ በማለት ጠርቷል

ሰይጣን፣ ዲያብሎስ፣ ክፉው

ዲያብሎስ እግዚአብሔር የፈጠረው መንፈሳዊ አካል ነበር፤ በእግዚአብሔር መማመፁ የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ። ዲያብሎስ፣ “ሰይጣን” እና፣ “ክፉው” ተብሎ ይጠራል

  • የእግዚአብሔርን ቦታ ለመውሰድና እንደ እግዚአብሔር መመለክ በመፈለጉ ዲያብሎስ እግዚአብሔርንና እርሱ የፈጠረውን ሁሉ ይጠላል
  • ሰይጣን በእግዚአብሔር እንዲያምፁ ሰዎችን ይፈታተናል
  • ሕዝቡን ከሰይጣን ቁጥጥር ለማዳን እግዚአብሔር ልጁ ኢየሱስን ላከ
  • “ሰይጣን” – “ጠላት” ወይም፣ “ባላጋራ” ማለት ነው
  • “ዲያብሎስ” – “ከሳሽ” ማለት ነው

ማዳን፣ ደኅንነት

“ማዳን” አንድን ሰው ከአንዳች መጥፎ ወይም ጎጂ ነገር መጠበቅ ማለት ነው “ደኅንነት” ከጉዳት ወይም ከአደጋ የተጠበቀ ማለት ነው

  • ቁሳዊ በሆነ ደረጃ ሰዎች ከጉዳት፣ ከአደጋ ወይም ከሞት መዳን ወይም ማምለጥ ይችላሉ
  • በመንፈሳዊ ደረጃ፣ አንድ ሰው፣ “ድኗል” ከተባለ በኢየሱስ መስቀል ላይ ሞት እግዚአብሔር ይቅር ብሎታል፤ በኅጢአቱ ገሃነም ውስጥ ከመቀጣት እንዲያመልጥ ረድቶታል ማለት ነው
  • ሰዎች ከአደጋ መዳን ወይም ማምለጥ ይችላሉ፤ በኅጢአታቸው ምክንያት ለዘላለም ከመቀጣት ሰዎችን የሚያድን ግን እግዚአብሔር ብቻ ነው

አዳኝ

“አዳኝ” የሚለው ቃል ሌሎችን የሚያድን ወይም የሚታደግ ሰውን ያመለክታል። ለሌሎች ብርታትን ወይም የሚያስፈልጋቸውን የሚሰጥ ሰውንም ያመለክታል

  • ብዙ ጊዜ ከጠላቶቻቸው ስላዳናቸው፣ ብርታትንና ለመኖር የሚያስፈልጋቸውን ስለሰጣቸው ብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር የእስራኤል አዳኝ ተብሏል
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “አዳኝ” የኢየሱስ ክርስቶስ መጠሪያ ነው፤ ምክንያቱም በኅጢአታቸው ምክንያት ለዘላላም ከመቀጣት ሰዎችን የሚያድን እርሱ በመሆኑ ነው። ከኅጢአታቸው ቁጥጥር ስር ከመሆንም ያድናቸዋል

ጸሐፍት፣ የአይሁድ ሕግ መምሕራን

ጸሐፍት መንግሥታዊ ወይም ሃይማኖታዊ ሰንዶችን በእጅ ጽሑፍ የማርቀቅ ወይም የመገልበጥ ኅላፊነት የነበረባቸው ባለ ሥልጣኖች ናቸው

  • የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በእጅ መጻፍና ለትውልድ ማቆየት የጸሐፍት ኅላፊነት ነበር
  • ጸሐፍት የእግዚአብሔርን ሕግ የሚመለከቱ አስተሳሰቦችንና ማብራርያዎችን ይጽፉ፣ ይጠብቁና ይተረጉሙ ነበር
  • አልፎ አልፎም ጸሐፍት ሁነኛ የመንግሥት ባለ ሥልጣኖችም ይሆናሉ
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም የሚታወቁ ጸሐፍት ባሮክና ዕዝራ ናቸው

መለየት

“መለየት” የሚለው ቃል አንድ ዓላማን ለመፈጸም ከአንድ ነገር ተለይቶ መውጣትን ያመለክታል

  • እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር አገልግሎት የተለዩ ነበሩ
  • መንፈስ ቅዱስ እርሱ ለሰጣቸው ሥራ በርናባስንና ጳውሎስን እንዲለዩለት በአንጾኪያ ለነበሩ ክርስቲያኖች ተናገረ
  • የእግዚአብሔርን ሥራ ለመሥራት የተለየ ሰው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም “ተለይቷል”
  • “ቅዱስ የሚለው ቃል አንዱ ትርጉም የእግዚአብሔር ለመሆንና ኅጢአተኛ ከሆነ ዓለማዊ ሕይወት የተለየ ማለት ነው
  • “መቀደስ” - አንድ ሰው ለእግዚአብሔር አገልግሎት መለየት ማለት ነው

ምልክት፥ ማረጋገጫ፣ ማሳሰቢያ

ምልክት የተለየ ትርጉም ያለው መልእክት የሚያስተላልፍ ዕቃ፣ ሁኔታ ወይም ድርጊት ሊሆን ይችላል

  • ምልክቶች ቃል ለተገባለት ነገር እንደ ማሳሰቢያ ያገለግላል
  • ሰማይ ላይ የምናየው ቀስተ ደመና ከእንግዲህ በምድር ሁሉ ላይ በሚሆን ጎርፍ ሕይወትን ሁሉ እንደማያጠፋ የሚያሳስብ ምልክት ነው
  • ከእነርሱ ጋር ያደረገው ኪዳን ምልክት እንዲሆን ልጆቻቸውን እንዲገርዙ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዘዘ
  • ምልክቶች አንድን ነገር ይገልጣሉ ወይም ያመለክታሉ
  • በቤተ ልሔም አዲስ የተወለደው መሲህ የትኛው ሕፃን መሆኑን ማወቅ እንዲችሉ መልአኩ ለእረኞቹ ምልክት ነገራቸው
  • ማሰር ያለባቸው እርሱን እንደሆነ ለአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ለማሳየት ምልክት እንዲሆን ይሁዳ ኢየሱስን ሳመ
  • ምልክቶች አንድ ነገር እውነት መሆኑን ሊያመለክቱ ይችላሉ
  • ነቢያትና ሐዋርያት የደረጓቸው ተአምራት የተናገሩት የእግዚአብሔርን መልእክት መሆኑን የሚያረጋግጡ ምልክቶች ነበሩ
  • ኢየሱስ ያደረጋቸው ተአምራት እርሱ በእውነት መሲሕ ለመሆኑ፣ ምልክቶች ናቸው

ኅጢአት፣ ኅጥእ፣ ኅጢአተኛ፣ ኅጢአት ማድረግ

“ኅጢአት” የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር የሚደረግ ተግባርን፣ ሐሳብንና ቃልን ያመለክታል። እግዚአብሔር ያዘዘውን አለማድረግም ኅጢአት ነው

  • ኅጢአት ሌሎች ሰዎች ባያውቁ እንኳ ማንኛውንም እና የምናደርገውን ለእግዚአብሔር የማይገዛና እርሱን ደስ የሚያሰኝ ነገር ሁሉ ይጨምራል
  • ለእግዚአብሔር ፈቃድ የማይገዛ ሐሳብና ተግባር ሁሉ፣ “ኅጢእ” ነው
  • አዳም ኅጢአት በመድረጉ የሰው ልጆች ሁሉ እነርሱን ከሚቆጣጠር ኅጥእ ዝንባሌ ጋር ተወልደዋል
  • “ኅጢአተኛ” ኅጢአት የሚያደርግ ሰው ነው፤ ሰዎች ሁሉ ኅጢአተኞች ናቸው
  • አንዳንዴ ፈሪሳዊያንን የመሳሰሉ የሃይማኖት ሰዎች ሕጉንና እነርሱ መጠበቅ አለባቸው የሚሉትን ነገር የማይጠብቁ ሰዎች ለማመልከት “ኅጢአተኛ” በተሰኘው ቃል ይጠቀማሉ
  • ከሌሎች የከፋ ኅጢአተኞች የሆኑ ሰዎችን ለማመልከት፣ “ኅጢአተኞች” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል። ለምሳሌ፣ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና አመንዝራዎች፣ በዚህ ቃል ተጠርተዋል

ልጅ፣ የ. . . ልጅ

“ልጅ” የሚለው ቃል ከወላጆቹ ጋር ካለው ግንኙነት አንፃር ትንሽ ልጅን ወይም ሰውን ያመለክታል። የአንድ ሰው ወንድ ወይም ሴት ልጅ ወይም እንደ ልጅ የተቀበለውን ሰው ያመለክታል

  • ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ልጅ” የሚለው ቃል የልጅ ልጅ ወይም የልጅ ልጅ ልጅ የሆነ ማንኛውንም ወንድ ያመለክታል
  • “ልጄ” የሚለው ቃል ሕፃን ልጅ ወይም ጎልማሳ በፍቅር የሚጠራበት ቃል ሊሆን ይችላል
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ በክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎችን ለማመልከት፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል
  • “የ. . . ልጅ” የሚለው ቃል፣ ብዙ ጊዜ “የእርሱ ባሕርይ ያለው” የሚል ትርጉም ያለው ምሳሌያዊ አነጋገር ነው። ለምሳሌ፣ “የብርሃን ልጆች” ፣ “የመታዘዝ ልጆች” ፣ “የሰላም ልጆች” እና፣ “የነጎድጓድ ልጆች” እንደተሰኙት
  • “የ. . . ልጅ” የዚያን ሰው አባት ለማመልከትም በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ውሏል። ይህ ሐረግ የትውልድ ቆጠራን አስመልክቶ በተለያየ ቦታ ጥቅም ላይ ውሏል
  • የአባቱን ስም ለማመልከት “የ. . . ልጅ” የሚለው ሐረግ ተደጋግሞ ጥቅም ላይ ከዋለ ተመሳሳይ ስም ያላቸውን ሰዎች ለመለየት ይጠቅማል። ለምሳሌ፣ 1ነገሥት 4 ላይ እንዳለው “የሳዶቅ ልጅ አዛርያስ” እና፣ “የናታን ልጅ አዛርያስ” ወይም 2ነገሥት 15 ላይ፣ “የአማስያ ልጅ አዛርያስ” የተባሉ ሦስት የተለያዩ ሰዎች አሉ

የእግዚአብሔር ልጅ፣ ልጁ፣ ልጅ(ወልድ)

“የእግዚአብሔር ልጅ” ሰው ሆኖ ወደ ዓለም የመጣውን ቃል ኢየሱስን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ፣ “ልጁ” ተብሎም ይጠራል

  • የእግዚአብሔር ልጅ የእግዚአብሔር ባሕርያት አሉት፤ እርሱ ፍጹም እግዚአብሔር ነው
  • እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሦስቱም በባሕርይ አንድ ናቸው
  • ከሰው ልጆች በተለየ መልኩ የእግዚአብሔር ልጅ ለዘላለም ነበር
  • በመጀመሪያ የእግዚአብሔር ልጅ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ዓለምን ፈጥሯል
  • ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ በመሆኑ፣ አባቱን ይወዳል፤ ለአባቱም ይታዘዛል፤ አባቱም ይወደዋል

የሰው ልጅ

የሰው ልጅ“የሰው ልጅ” የሚለው ሐረግ ብዙ ጊዜ ኢየሱስ ራሱን የሚጠራበት ስም ነበር። ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “የሰው ልጅ” ማንኛውም ሰው የሚታወቅበት ስም ነበር

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “የሰው ልጅ” የተሰኘው ሐረግ ብዙውን ጊዜ፣ “ሰው” ወይም “ሰብዓዊ ፍጡር” ለማለት ጥቅም ላይ ይውል ነበር
  • ከትንቢተ ሕዝቅኤል እንደምንመለከተው እግዚአብሔር ነቢዩን፣ “የሰው ልጅ” በማለት ጠርቶታል። ለምሳሌ፣ “የሰው ልጅ ሆይ ትንቢት ተናገር” እንደሚለው
  • “እኔ” ከማለት ይልቅ ኢየሱስ ራሱን በዚህ ቃል ይጠራ ነበር
  • ነቢዩ ዳንኤል በራእዩ፣ “የሰው ልጅ” ከደመና ጋር ሲመጣ አይቶ ነበር። ይህ የሚያመለክተው የመሲሑን መምጣት ነበር
  • ኢየሱስ ስለ ራሱ ሲናገር፣ አንድ ቀን “የሰው ልጅ” በደመና ተመልሶ ይመጣል አለ
  • ኢየሱስ በደመና እንደሚመጣ የሚናገሩት እነዚህ

ጥቅሶች እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታሉ


የእግዚአብሔር ልጆች

“የእግዚአብሔር ልጆች” በርካታ ትርጉሞች ያሉት ምሳሌያዊ አነጋገር ሊሆን ይችላል

  • አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” በኢየሱስ የሚያምኑትን ሁሉ የሚመለከት ሲሆን፣ ወንዶችንም ሆነ ሴቶችን ስለሚያጠቃልል፣ ብዙ ጊዜ፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” ተብሎ ተተርጉሞአል
  • ይህ ቃል አንድ ልጅ ልጅ መሆን ከሚያስገኘው መብት ሁሉ ጋር ተያይዞ በአባትና በልጅ መካከል መቀራረብ ከእግዚአብሔር ጋር መቀራረብን ያመለክታል
  • ዘፍጥረት 6 ላይ ያለውን፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” የሚለውን አንዳንዶች የወደቁ መላእክትን ማለትም ክፉ መናፍስትን ወይም አጋንንትን እንደሚያመለክት ተርጉመውታል። ሌሎች ደግሞ ኅይለኛ ፖለቲካዊ ሥልጣን የነበራቸው ገዦችን ወይም የሴት ዘሮችን እንደሚያመለክት ያስባሉ
  • “የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለው ብቸኛ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስን ከሚያመለክተው የተለየ ነው

ነፍስ

ነፍስ የሰው ውስጣዊ፣ የማይታይና ዘላለማዊ ክፍል ነው። የሰውን ቁሳዊ ያልሆነ ነገር ሁሉ ይጨምራል

  • “ነፍስ” እና፣ “መንፈስ” ሁለት የተለያዩ ነገሮች ሊሆኑ ይችላሉ፤ ወይም አንድን ነገር የሚያመለክቱ ሁለት የተለያዩ ቃሎች ሊሆኑ ይችላሉ
  • አንድ ሰው ሲሞት ነፍሱ ከሥጋው ይለያያል
  • አንዳንዴ፣ “ነፍስ” የሚለው ቃል የሰውን ሁለንተና ለማመልከት በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል። ለምሳሌ፣ “ኅጢአት የምታደርግ ነፍስ” ማለት፣ “ ኅጢአት የሚያደርግ ሰው” ማለት ነው፤ “ ነፍሴ ደከመች” - ማለት፣ “እኔን ደከመኝ” መለት ነው

መንፈስ፥ መንፈሳዊ

“መንፈስ” የሚለው ቃል የሰዎችን ቁሳዊ ያልሆነና የማይታይ ክፍል ያመለክታል። ሰው ሲሞት መንፈሱ ከአካሉ ይለያያል

  • “መንፈስ” ቁሳዊ አካል የሌለውን በተለይ መልካም ወይም ክፉ መናፍስትን ሊያመለክት ይችላል
  • የሰው መንፈስ እግዚአብሔርን የሚያውቅበትና በእርሱ የሚያምንመበት ክፍል ነው
  • በአጠቃላይ፣ “መንፈሳዊ” ቁሳዊ ያልሆነ ዓለም ማንኛውም ክፍል ነው
  • በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት፣ “መንፈሳዊ” ከእግዚአብሔር ጋር ሚያያዝ ማንኛውንም ነገር በተለይም፣ መንፈስ ቅዱስን ያመለክታል
  • ለምሳሌ፣ “መንፈሳዊ ምግብ” የሰውን መንፈስ የሚመግብ የእግዚአብሔር ትምህርት ሲያመለክት፣ “መንፈሳዊ ጥበብ” ከመንፈስ ቅዱስ ኅይል የሚገኝ ዕውቀትና መልካም አኗኗር ያመለክታል
  • እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ ቁሳዊ አካል የሌላቸው መንፈሳዊ ፍጡራንን የፈጠረም እርሱ ነው
  • በእግዚአብሔር ያመፁትንና ክፉ መናፍስት የሆኑትን ጨምሮ መላእክት መንፈሳዊ ፍጡራን ናቸው
  • “የ. . .መንፈስ” ከተባለ፣ “የጥበብ መንፈስን” ጨምሮ፣ “የ. . . መንፈስ” ባሕርይ ሲኖር ማለት ነው

ድንጋይ፣ በድንጋይ መውገር

ድንጋይ አነስ ያለ ዐለት ነው። በድንጋይ መውገር አንድን ሰው ለመግደል እርሱ ላይ ድንጋዮች መወርወር ማለት ነው

  • በጥንት ዘመን ወንጀለኞች በድንጋይ ይወገሩ ነበር፤ በዚህ ዘመን አንዳንድ አገሮችም እንደዚህ ያደርጋሉ
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዝሙትን ለመሳሰሉ እንዳንድ ኅጢአቶች ቅጣት እንዲሆን መሪዎች በደለኛውን በድንጋይ እንዲገድሉ ታዝዟል

ምኩራብ

ምኩራብ አይሁድ እግዚአብሔርን ለማምለክ የሚሰበሰቡበት ቦታ ነው። ከጥንት ዘመን ጀምሮ ምኩራቦች ለጸሎት፣ ቅዱሳት መጽሐፍትን ለማንበብና ለመማር አገልግሎት ላይ ውለው ነበር

  • አይሁድ ምኩራቦችን የሠሩት ብዙዎቹ ኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ በጣም ርቀው ይኖሩ ስለነበርና ዘወትር ወደዚያ ለመሄድ ባለመቻላቸው ነበር
  • ኢየሱስ ዘወትር በምኩራብ ያስተምር ነበር
  • “ምኩራብ” የሚለው ቃል እዚያ የሚሰበሰቡ ሰዎችንም ማመልከት ይችላል

መገናኛ ድንኳን

መገናኛ ድንኳን እስራኤላውያን 40 ዓመት በምድረ በዳ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሚያመልኩበት ድንኳን መሰል ነገር ነበር

  • ይህን ሁለት ክፍሎች የነበሩትን ዙሪያው ባለው አደባባይ የተከበበውን ትልቅ ድንኳን እንዴት መሥራት እንዳለባቸው እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ዝርዝር መምሪያዎች ሰጥቷቸዋል
  • እስራኤላውያን ወደ ሌላ ቦታ በተንቀሳቅሱ ጊዜ ሁሉ ካህናቱ የመገናኛውን ድንኳን በማፍረስ እስከ ቀጣዩ ሰፈር ድረስ ይሸከሙታል። ከዚያም አዲሱ ሰፈራቸው መካከል የተክሉታል
  • የመገናኛው ድንኳን ከጨርቅ፣ ከፍየል ጠጉርና ከእንስሳት ቆዳ የተሠሩ መጋረጃዎች በተሰቀሉበት የእንጨት ማዕቀፍ የተሠራ ነበር። ዙሪያው ያለው አደባባይም በሌሎች መጋረጃዎች የተከበበ ነበር
  • የመገናኛው ድንኳን ሁለቱ ክፍሎች ቅድስት (የዕጣኑ መሠዊያ ያለበት) እና ቅድስተ ቅዱሳን (የቃል ኪዳኑ ታቦት ያለበት) ናቸው
  • የመገናኛው ድንኳን አደባባይ ለመሥዋዕት የቀረቡ እንስሳት የሚቃጠሉበት መሠዊያና ለሃይማኖትዊ ሥርዓቱ የሚታጠቡበት ልዩ መታጠቢያ ክፍል ነበረው
  • በኢየሩሳሌም የነበረው የሰሎሞን ቤተ መቅደስ ከተሥራ በኋላ እስራኤላውያን መገናኛው ድንኳን ጥቅም ላይ መዋሉ ቀረ

ቤተ መቅደስ

ቤተ መቅደስ እስራኤል ለጸሎትና ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ የሚሰበሰቡበት ዙሪያውን በተከበበ አደባባይ ውስጥ ያለ ሕንፃ ነው። ቤተ መቅደስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ባለው የሞሪያ ተራራ ነበር።

  • አብዛኛውን ጊዜ፣ “ቤተ መቅደስ” የሚለው ቃል ዋናውን ሕንፃ የሚከብባትን አደባባዮች ጨምሮ መላውን ሕንፃ ያመለክታል። አንዳንዴ የሚያመለክተው ውስጡ የሚፈጸመውን አምልኮ ሳይሆን ሕንፃውን ብቻ ነው።
  • የቤተ መቅደስ ሕንፃ ቅድስትና ቅድስተ ቅዱሳን የሚባሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት።
  • ቤተ መቅደሱ የእርሱ ማደሪያ እንደ ሆነ እግዚአብሔር ተናግሯል።
  • መንፈስ ቅዱስ በውስጣቸው ከመኖሩ የተነሣ በክርስቶስ ያመኑ ሰዎች “የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ” ተብለው ተጠርተዋል።

መፈተን፣ ፈተና

መፈተን አንድ ሰው ተገቢ ያልሆነ ነገር እንዲያደርግ መሞከር ማለት ነው።

  • ፈተና የሚባለው አንድ ሰው ተገቢ ያልሆነ ነገር ለማድረግ እንዲፈልግ ማድረግ ነው።
  • ሰዎች በራሳቸው ኀጥእ ባሕርይና በሌሎች ይፈተናሉ።
  • ለእግዚአብሔር ባለ መታዘዝና መጥፎ ነገሮችን በማድረግ እግዚአብሔር ላይ ኀጢአት እንዲሠሩ ሰይጣንም ሰዎችን ይፈትናል።
  • ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው፤ ተገቢ ያልሆነ ነገር ሊያስደርገውም ሞከረ፤ ኢየሱስ ግን የሰይጣንን ፈተናዎች ሁሉ ተቋቋመ፤ ኀጢአትም አላደረገም።
  • “መፈተን” የሚለው ቃል እግዚአብሔር መፈተን ለማለትም ጥቅም ላይ ይውላል፤ ይህም አልታዘዝ ባዩን በመቅጣት ምላሽ እስኪሰጥ ድረስ በእግዚአብሔር ላይ በማመጽ መጽናት ማለት ነው። ይህ ሁኔታ እግዚአብሔርን መፈታተን ይባላል።

ፈተና

“ፈተና” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ብርታትና ድካም ለይቶ የሚያሳይ አስቸጋሪ ወይም አዳጋች ሁኔታ ያመለክታል።

  • የሰዎችን ኀጢአት ለመግለጥ አንዳንዴ እግዚአብሔር በሚመጡ ፈተናዎች ይጠቀማል። ፈተና ሰዎች ከኀጢአት እንዲመለሱና ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርቡ ይረዳል።
  • ምን ያህል ንጹሕ ወይም ጠንካራ መሆናቸውን ለመለየት ወርቅና ሌሎች የብረት ዐይነቶች በእሳት ይፈተናሉ። ይህ እግዚአብሔር ሕዝቡን ለመፈተን አዳጋችና አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እንደሚጠቀም የሚያመለክት ሥዕል ነው።
  • እግዚአብሔር ሰዎችን ይፈትናል፤ ይሁን እንጂ ኀጢአት እንዲያደርጉ ምክንያት የሚሆን ፈተና አያመጣባቸውም፤ ሰይጣን ሰዎችን የሚፈትነው ኀጢአት እንዲፈጽሙ ለማድረግ ነ።ው
  • “መፈተን” የአንድ ሰው ወይም ነገር ትክክለኛ ምንነት ይፋ እንዲወጣ መገዳደር” ማለት ነው።
  • እግዚአብሔርን መፈተን ባለ መታዘዝ መጽናት፣ ለምሕረቱ ዋጋ አለመስጠት ማለት ነው።
  • እግዚአብሔርን መፈተን እንደማይገባ ኢየሱስ ለሰይጣን ነግሮታል። እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ፣ ቅዱስና ከማንኛውም ነገር በላይ ነው።

ምስክር፣ መመስከር

“ምስክር” እና፣ “መመስከር” አንድን ነገር በተመለከተ የሚያውቁትን እውነት በግልጽና በሰው ሁሉ ፊት መናገር ማለት ነው።

  • ብዙውን ጊዜ አንድ ሰው፣ “የሚመሰክረው” በትክክል ስለሚያውቀውና በቀጥታ ስለ ተለማመደው ነገር ነው።
  • ሐሰት የሚናገር “ምስክር” የተፈጸመውን ነገር አስመልክቶ እውነቱን እየተናገረ አይደለም።
  • አንዳንዴ፣ “ምስክር” ነቢይ የተናገረውን ትንቢት ያመለክታል።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ ይህ ቃል የሚያመለክተው የኢየሱስ ተከታዮች ስለ እርሱ ሕይወት፣ ሞትና ትንሣኤ የሚናገሩትን ሁሉ ነው።

የአራተኛው ክፍል ገዥ

የአራተኛው ክፍል ገዥ የሚባለው የሮም መንግሥትን የተወሰነ ክፍል በመግዛት ላይ ያለ ባለ ሥልጣንን ነው። እያንዳንዱ የአራተኛው ክፍል ገዥ ከሮም ንጉሥ ሥልጣን ሥር ነበር።

  • “የአራተኛው ክፍል ገዥ” የሚያመለክተው እያንዳንዱ ባለ ሥልጣን ከአራት ክፍሎች አንዱን የሚገዛ መሆኑን ነው።
  • እያንዳንዱ ክፍል አንድ ወይም ገሊላ ወይም ሰማርያ የተሰኙ ብዙ አውራጃዎችን ይሸፍናል።
  • “የአራተኛው ክፍል ገዥ” የሚለው፣ “ገዥ” ወይም፣ “አስተዳዳሪ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።

አሥራ ሁለቱ፣ አሥራ አንዱ

“አሥራ ሁለቱ” የቅርብ ደቀ መዛሙርቱ ወይም ሐዋርያቱ እንደሆኑ ኢየሱስ የመረጣቸው አሥራ ሁለት ሰዎች ናቸው። ይሁዳ ራሱን ከገደለ በኋላ፣ “አሥራ አንዱ ቀሩ።

  • ኢየሱስ ሌሎች ብዙ ደቀ መዛሙርትም ነበሩት፤ “አሥራ ሁለቱ” ግን በሦስት ዓመት ተኩል አገልግሎቱ እስከ መጨረሻው የተከተሉት ናቸው።
  • የእነዚህ አሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት ስም ማቴዎስ 10፣ ማርቆስ 3 እና ሉቃስ 6 ላይ ተዘርዝሮአል።
  • ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከተመለሰ በኋላ “አሥራ አንዱ” የይሁዳን ቦታ እንዲይዝ ማትያስ የተባለ ደቀ መዝሙር መረጡ። ከዚያም እንደ ገና፣ “አሥራ ሁለቱ” ተባሉ።

መተላለፍ

“መተላለፍ” ትእዛዝን፣ ደንብን ወይም ሕግን ማፍረስ ማለት ነው።

  • በምሳሌያዊ መልኩ፣ “መተላለፍ” – “መስመር አልፎ መሄድ” ማለትም ለራሱ ለሰውዬውና ለሌሎችም ጥቅም ሲባል የተደረገውን ገደብ ወይም ክልል አልፎ መሄድን ያመለክታል።
  • “መተላለፍ”፣ “ኀጢአት”፣ “ርኵሰት” እና፣ “በደል” የተሰኙት ቃሎች በሙሉ ከእግዚአብሔር ፈቃድ የሚጻረር ነገር ማድረግና ትእዛዞችን ማፍረስ ማለት ናቸው።

መጣስ፣ መዳፈር

“መጣስ” ሕግ ማፍረስ ወይም የሌሎችን መብት መንካት ማለት ነው።

  • ግብረ ገባዊ ወይም ማኅበራዊ ሕግ አለማክበር ወይም ሌሎች ላይ ይተፈጸመ ኀጢአት ማለት ነው።
  • ይህ ቃል በተለይ ለእግዚአብሔር አለመታዘዝ ጋር ከተያያዘ፣ “ከኀጢአት” እና “ከመተላለፍ” ጋር ተመሳሳይ ትርጕም ይኖረዋል።
  • ኀጢአት ሁሉ እግዚአብሔርን መዳፈር ነው።

እውነት፣ እውነተኛ

“እውነት” የሚለው ቃል ይተረጋገጠ ፅንሰ ሐሳብን፣ በትክክል የተፈጸመ ሁኔታንና በእርግጥ የተነገረ ቃልን ያመለክታል።

  • እውነተኛ ነገሮች፣ እውን የሆኑ፣ ትክክለኛ፣ እርግጠኛ፣ ተገቢ፣ ሕጋዊና አግባብ የሆኑ ነገሮች ናቸው።
  • እምነትን፣ ሐቅን ወይም እውነት የሆነውን መረዳት እውነተኛ መሆን ነው።
  • አስተማማኝና እርግጠኛ በሆነ መልኩ መንቀሳቀስን የሚያመለክት ፅንሰ ሐሳብ እውነተኛነትን ያመለክታል።
  • ኢየሱስ በተናገረው ሁሉ የእግዚአብሔርን እውነት ገልጧል።
  • የእግዚአብሔር ቃል እውነት ነው። በትክክል የተፈጸመ ነገርን ይናገራል፤ ስለ እግዚአብሔርና እርሱ ስለ ፈጠራቸው ማንኛውም ነገሮች እውንቱን ያስተምራል።

መታመን፣ ታማኝ፣ ታማኝነት

“መታመን” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር እውነት ወይም እምነት ሊጣልበት የሚገባ መሆኑን ያመለክታል። “ታማኝ” ሰው ትክክልና እውነት የሆነ ነገር እንደሚያደርግና እንደሚናገር እምነት ይጣልበታል።

  • “መታመን” ከእምነት ጋር በጣም ይቀራረባል። አንድ ሰው ላይ ከተማመንን ቃል የገባውን እንደሚያደርግ እናምናለን።
  • አንድ ሰው ላይ መታመን እርሱ ላይ መደገፍ ማለት ነው።
  • በኢየሱስ፣ “መታመን” እርሱ እግዚአብሔር መሆኑንና ለኀጢአታችን ዋጋ ለመክፈል መስቀል ላይ መሞቱን፣ እርሱ እንደሚያድነን ማመን ማለት ነው።
  • “የታመነ ቃል” - እውነት መሆኑ የማይጠረጠር የታመነ ንግግር ማለት ነው።

ያልቦካ እንጀራ

“ያልቦካ እንጀራ” የሚያመለክተው ያለ እርሾ ወይም እንዲቦካ የሚያደርግ ሌላ ነገር ሳይገባበት የተጋገረ እንጀራን ነው። ያልቦካ ዳቦ ኩፍ አይልም፣ ስለዚህ ጠፍጣፋ ነው።

  • እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፅ ባርነት ባወጣ ጊዜ ያቦኩት ሊጥ ኩፍ እስኪል ድረስ ሳይጠብቁ በፍጥነት ግብፅን ለቅቀው እንዲወጡ ነግሮአቸው ነበር። ስለዚህ የበሉት እንጀራ ያልቦካ ነበር። ስለዚህም ይህን ጊዜ እንዲያስታውሳቸው በየዓመቱ የፋሲካን በዓል ሲያከብሩ ያልቦካ እንጀራ ይበሉ ነበር።
  • በአንዳንድ መልኩ፣ እርሾ የኀጢአት ምሳሌ በመሆኑ፣ “ያልቦካ እንጀራ” ኀጢአትን ማስወገድንና እግዚአብሔርን በሚያከብር መንገድ መኖርን ይወክላል።

ስእለት

ስእለት አንድ ሰው ለእግዚአብሔር የሚገባው ቃል ነው። እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ሁኔታ ለማክበር ወይም ም ያህል ለእርሱ የተሰጠ መሆኑን ለማሳየት አንድ ሰው አንድ ነገር እንደሚያደርግ ለእግዚአብሔር ቃል ይገባል።

  • አንድ ሰው ስእለት ካደረገ ያንን የመፈጸም ግዴታ አለበት።
  • ስእለቱን ካልፈጸመ እግዚአብሔር ያንን ሰው እንደሚቀጣ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
  • አንዳንዴ ሰው ባድረገው ስእለት መሠረት እንደጠበቀው ወይም የሚያስፈልገውን እንዲያሟላላት እግዚአብሔርን ይለምናል።
  • ይሁን እንጂ አንድ ሰው ስእለት በማድረግ የጠየቀውን ሁሉ እግዚአብሔር የማሟላት ግዴታ የለበትም።

የእግዚአብሔር ፈቃድ

“የእግዚአብሔር ፈቃድ” የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ፍላጎትና እቅድ ነው።

  • የእግዚአብሔር ፈቃድ በተለይ ከሰዎች ጋር ያለውን ግንኙነትና ሕዝቡ መስጠት ካለባቸው ምላሽ ጋር ይያያዛል።
  • ለተቀረው ፍጥረቱ ያለውን ፍላጎትና ዕቅዱንም ያመለክታል።
  • “መፍቀድ”፣ “መወሰን” ወይም “መፈለግ” ማለት ነው።

ጠቢባን

“ጢቢባን” የተሰኘው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የተለየ ዕውቀትና ችሎታ ያላችው ሰዎችን ለማመልከት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሰዎች በንጉሡ አደባባይ ነበር የሚገኙት።

  • አንዳንድ ጠቢባን ከዋክብትን በማጥናት ሰማይ ላይ ያሉ ከዋክብት አቀማመጥ ትርጕም ያለው መሆኑን አመልክተዋል።
  • ብዙውን ጊዜ ጠቢባን ሕልም ለመተርጎም ይጠሩ ነበር። ዳንኤል ከንጉሥ ናቡከደነፆር ጠቢባን አንዱ ነበር፤ እግዚአብሔር የንጉሡን ሕልም መተርጎም የሚችልበት ችሎታ ሰጠው።
  • በአንዳንድ የሜድትራንያን አገሮች ጠቢባን እንደ መደበኛ ምሁራን ነበር የሚታዩት።
  • አንዳንዴ ጠቢባን ጥንቆላንና በክፉ መናፍስት ኀይል የሚደረጉ ሌሎች ነገሮችን ይለማመዱ ነበር።
  • ከአዲስ ኪዳን እንደምንመለከተው ለኢየሱስ ለመስገድ ከምሥራቅ መጥተው የነበሩት ሰዎች፣ ሰብዓ ሰገል ወይም “ጠቢባን” ይባሉ ነበር። እነዚህ ሰዎች ከዋክብትን የሚያጠኑ ኮከብ ቆጣሪዎች ሊሆን እንደሚችል ይታሰባል። አንዳንዶች ዳንኤል ባቢሎን በነበረ ጊዜ ያስተማራቸው ጠቢባን ልጆች ሊሆኑ እንደሚችሉ ያስባሉ።

ወዮ

“ወዮ” ከፍ ያለ ጭንቀትና ሐዘንን ያመለክታል። ስለሚመጣው ከባድ ጥፋት ማስጠንቀቂያም ይሆናል።

  • “ለ. . . ወዮ” ማለት ለኀጢአታቸው ቅጣት እንዲሆን ሰዎች ላይ የሚወርድ ከባድ መከራን ያመለክታል።
  • በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ስለሚመጣው ከባድ ፍርድ አጽንዖት ለመስጠት፣ “ወዮ” የሚለው ቃል ተደጋግሞአል።
  • “ወዮልኝ” የሚል ሰው ከከባድ መከራ የተነሣ የደረሰበትን ሐዘን መግለጹ ነው።

የእግዚአብሔር ቃል፣ የያህዌ ቃል፣ የጌታ ቃል፣ ቅዱሳት መጻሕፍት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “የእግዚአብሔር ቃል” የሚባለው እግዚአብሔር ለሰዎች የተናገረው ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ይህም ንግግርና በጽሑፍ የሰፈረ መልእክትን ይጨምራል። ኢየሱስ ራሱ፣ “የእግዚአብሔር ቃል” ተብሏል።

  • “ቅዱሳት መጻሕፍት” – “ጽሑፎች” ማለት ነው። ቃሉ የሚገኘው አዲስ ኪዳን ውስጥብቻ ሲሆን፣ የሚያመለክተው የዕብራውያንን ቅዱሳት መጻሕፍት፣ “ብሉይ ኪዳንን” ነው። እነዚህ ጽሑፎች ወደ ፊት ከብዙ ዓመታት በኋላ የሚመጡ እንዲያነባቸው በጽሑፍ የሰፈሩ የእግዚአብሔር መልእክት ናቸው።
  • “የያህዌ ቃል” እና፣ “የጌታ ቃል” የተሰኙት ተያያዥ ገለጻዎች ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉ ነቢይ ወይም ሌላ ሰው የተሰጡ በውል የሚታወቁ የእግዚአብሔር መልእክቶችን ነው።
  • አንዳንዴ የእግዚአብሔር ቃል የሚለው እንዲሁ፣ “ቃል” ወይም፣ “ቃሌ” ወይም፣ “ቃልህ” ተብሎ ተጽፏል።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ፣ “ቃል” እና፣ “የእግዚአብሔር ቃል” ተብሏል። እነዚህ መጠሪያዎች እርሱ ራሱ እግዚአብሔር በመሆኑ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ማንነት መግለጡን ያመለክታሉ።

ሥራዎች፣ ተግባሮች፣ ሥራ፣ ተግባር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሥራዎች”፣ “ተግባሮች” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ የዋሉት እግዚአብሔር ወይም ሰዎች ያደረጉትን በአጠቃላይ ለማሳየት ነው።

  • “ሥራ” ሌሎችን ለማገልገል የተከናወነ ማንኛውንም ነገር ያመለክታል።
  • “የእግዚአብሔር ሥራዎች” እና፣ “የእጆቹ ሥራ” የተሰኙት ዓለምን መፍጠሩን፣ ኀጢአተኞችን ማዳኑን፣ ለፍጥረት ሁሉ የሚያስፈልገውን መስጠቱንና አጽናፈ ዓለሙን አጽንቶ መያዝን ጨምሮ እርሱ ያደረገውን ሁሉ የሚያካትት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው።
  • የሰው ሥራ ወይም ተግባር መልካም ወይም ክፉ ሊሆን ይችላል።
  • አማኞች መልካም ፍሬ እንዲያፈሩ መንፈስ ቅዱስ ያስችላቸዋል፤ ይህም፣ “መልካም ፍሬ” የሚባለው ነው።
  • ሰዎች የሚድኑት በመልካም ሥራቸው ሳይሆን፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ነው።
  • ሰው የሚሠራው ራሱን ለመርዳት ወይም እግዚአብሔርን ለማገልገል ሊሆን ይችላል። እግዚአብሔር አሁንም፣ “እየሠራ” መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል።

ዓለም፣ ዓለማዊ

ብዙውን ጊዜ፣ “ዓለም” የሚያመለክተው አጽናፈ ዓለሙ ውስጥ ሰዎች የሚኖሩበትን ማለትንን ማለትን ምድርን ነው። “ዓለማዊ” በዚህ ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ክፉ መንገድና አሠራር ያመለክታል።

  • በጣም አጠቃላይ በሆነ መልኩ፣ “ዓለም” የሚያመለክተው ሰማያትንና ምድርን እንዲሁም በውስጣቸው ያሉትን ነገሮች ሁሉ ነው።
  • አብዛኞቹ ዐውዶች ውስጥ፣ “ዓለም” ከተባለ፣ “በዓለም ያሉ ሰዎች” ማለት ነው።
  • አንዳንዴ ደግሞ በተዘዋዋሪ የሚያመለክተው በምድር የሚኖሩ መጥፎ ሰዎችን ወይም ለእግዚአብሔር የማይታዘዙ ሰዎችን ነው።
  • ሐዋርያትም፣ “ዓለም” የሚለውን ቃል የተጠቀመበት በዚህ ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ብልሹና ራስ ወዳድ ሕይወት ለማመልከት ነበር። ይህም የሰውን ጥረት መሠረት ያደረገውንና ራሱን እንደ ጻድቅ የሚቆጥር ሃይማኖታዊ ልምምዶችን ሁሉ ያካትታል።
  • እነዚህ ባሕርያት የሚታዩባቸው ሰዎችና ነገሮች፣ “ዓለማዊ” ይባላሉ።

ማምለክ፣ መስገድ

“ማምለክ፣ መስገድ” እግዚአብሔርን ማክበር፣ ማመስገንና ለእርሱ መታዘዝ ማለት ነው።

  • ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “በጣም ማጎንበስ” ወይም፣ በትሕትና እርሱን ለማክበር እፊቱ መደፋት ማለት ነው።
  • እርሱን በማመስገንና በመታዘዝ እርሱን ስናገለግልና ስናከብር እግዚአብሔርን ማክበራችን ነው።
  • እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ሲያመልኩ አብዛኛውን ጊዜ መሠዊያው ላይ መሥዋዕት ያቀርቡ ነበር።
  • አንዳንዶች ሐሰተኛ አማልክት ያመልካሉ።

የሚገባው፣ ዋጋ ያለው፣ የማይገባው፣ ዋጋ ቢስ

“የሚገባው” የሚለው ቃል ክብርና ምስጋና መቀበል ያለበትን ያመለክታል። “ዋጋ ያለው” ውድ ወይም ጠቃሚ ነገርን ያመለክታል። “ዋጋ ቢስ” ግን ለምንም የማይጠቅም ማለት ነው።

  • የሚገባው የሚለው ዋጋ ወይም ጥቅም ያለው ከሚለው ጋር ይያያዛል።
  • “የማይገባው” ምንም ዓይነት ትኵረት ሊሰጠው የማይበቃ ማለት ነው።
  • ራስን እንደ ዋጋ ቢስ መቁጠር ለራስ ዝቅ ያለ ግምት መስጠት፣ ክብርና ችሮታ ላደረገለት ብቁ እንዳልሆነ ሰው መቁጠር ማለት ነው።
  • “የማይገባው” እና፣ “ዋጋ ቢስ” የተሰኙት ቢቀራረቡም ልዩነት አላቸው። “የማይገባው”ምንም ዓይነት ክብርና ዕውቅና ሊሰጠው የማይገባ ማለት ነው። “ዋጋ ቢስ” ግን ዓላማም ሆነ ጠቀሜታ የሌለው ማለት ነው።

መዓት፣ ቁጣ

መዓት ለረጅም ጊዜ የሚቆይ በጣም ከባድ ቁጣ ነው። ብዙውን ጊዜ ኀጢአት ላይ የሚመጣውን የእግዚአብሔር ጻድቅ ፍርድና በእርሱ ላይ የሚያምፁ ሰዎችን ቅጣት ያመለክታል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “መዓት” ብዙውን ጊዜ እርሱ ላይ ኀጢአት በሚያደርጉት ሰዎች የሚመጣውን የእግዚአብሔር ቁጣ ያመለክታል።
  • የእግዚአብሔር “መዓት” ኀጢአት ላይ መፍረዱንና መቅጣቱንም ያመለክታል።
  • የእግዚአብሔር መዓት ከኀጢአታቸው በንስሐ ለማይመለሱ ሰዎች የሚገባ የጽድቅ ቅጣት ነው።

ያህዌ

“ያህዌ” የእግዚአብሔር የተፀውዖ ስም ሲሆን፣ በሚቃጠለው ቁጥቋጦ ውስጥ እግዚአብሔር ራሱን ለሙሴ የገለጠው በዚህ ስሙ ነበር።

  • “ያህዌ” የሚለው ቃል የመጣው፣ “መሆን” ወይም፣ “መገኘት፣ ሐልዎት” ከተሰኙ ሁለት ቃሎች ነው።
  • “ያህዌ” የሚለው ሌሎች አማራጭ ትርጕሞች፣ “እርሱ ነው” ወይም፣ “እኔ ነኝ” ወይም፣ “እንዲሆን የሚያደርግ” የተሰኙትንም ይጨምራል።
  • ይህ ስም እግዚአብሔር ሁሌም የነበረ፣ አሁንም ያለና ለዘላለም የሚኖር መሆኑን ያመለክታል። እርሱ ሁሌም በቦታው ያለ መሆኑንም ያመለክታል።
  • የአብዛኞቹ ዋና ዋና ቋንቋዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕሞች፣ “ያህዌ” በሚለው ቃል ፈንታ፣ “ጌታ” በሚለው ቃል ተጠቅመዋል። ለምሳሌ፣ “እኔ አምላካችሁ ያህዌ ነኝ” የሚለው ቃል በቃል አገላለጽ፣ “እኔ አምላካችሁ ጌታ እግዚአብሔር ነኝ” ተብሏል።
  • አንዳንድ ቤተ እምነቶች፣ “ያህዌ” ከማለት ይልቅ፣ “ጌታ” ማለትን አጥብቀው ይመርጣሉ።
  • ይሁን እንጂ፣ ULB እና UDB የተሰኘው ትርጕም፣ ቃል በቃል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ባለው መሠረት የእግዚአብሔርን የተፀውዖ ስም ሁሌም ያህዌ በማለት ተርጉመዋል።
  • “ያህዌ” የተባለው የተፀውዖ ስም አዲስ ኪዳን ውስጥ አይገኝም፤ ከዚያ ይልቅ ጥቅም ላይ የዋለው፣ “ጌታ” የተባለው ቃል ነው።

የሰራዊት ጌታ ያህዌ፣ የሰራዊት ጌታ፣ ሰራዊት

“የሰራዊት ጌታ ያህዌ” እና፣ “የሰራዊት ጌታ” የሚሉት ሐረጎች ለእርሱ በሚታዘዙ እጅግ ብዙ መላእክት ላይ እግዚአብሔር ያለውን ሥልጣን የሚገልጡ አባባሎች ናቸው።

  • “ሰራዊት” ወይም፣ “ሰራዊቶች” የሚሉት ቃሎች ወታደሮችን፣ ሕዝብንና ከዋክብትን የመሳሰሉ እጅግ ብዙ ቁጥር ያላቸው ነገሮችን ያመለክታሉ።
  • አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕሞ መላእክትን፣ ወታደሮችን ሕዝብንና ከዋክብትን ሰራዊት በማለት ይጠራሉ።
  • “የሰማይ ሰራዊት” ከዋክብትን፣ ፕላኔቶችንና ሌሎች የሰማይ አካላትን ያመለክታል።

ቅንዓት፣ ቀናተኛ (ቀናዒ)

“ቅንዓት” እና፣ “ቀናተኛ” የአንድ ሰው ወይም ሐሰብ ጠንካራ ደጋፊ መሆንን ያመለክታል።

  • ቅንዓት መልካም ዓላምን ለመፈጸም የሚኖር ጠንካራ ፍላጎትና ሥራንም ይጨምራል። በታማኝነት ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ሌሎችም ያኑ እንዲያደርጉ የሚያስተምር ሰውን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
  • ቀናዒነት አንድን ነገር ለማድረግ ከፍ ያለ ጥረት ማድረግንና በዚያ ጥረት መጽናትንም ያካትታል።
  • “የጌታ ቅንዓት” ወይም፣ “የያህዌ ቅንዓት” የምኪያመለክተው ሕዝቡን ለመባረክና ፍትሕ ሰፍኖ ለማየት የእግዚአብሔር የሚወሰደውን ጠንካራና ያልተቆጠበ ርምጃ ያመለክታል።

ጽዮን፣ የጽዮን ተራራ

መጀመሪያ ላይ፣ “ጽዮን” ወይም፣ “የጽዮን ተራራ” ተብሎ ይጠራ የነበረው ንጉሥ ዳዊት ከኢያቡሳውያን የያዝሰው ምሽግ ወይም መሸሸጊያ ቦታ ስም ነበር። የኢየሩሳሌም ከተማ በተመሠረተችባቸውና የዳዊት መኖሪያ ከሆነው ኮረብቶች አንዱ ላይ ነበር የሚገኘው።

  • የጽዮን ተራራና የሞርያም ተራራ ኢየሩሳሌም የምትገኝባቸው ሁለት ኮረብቶች ናቸው። የዳዊት ልጅ ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሠራው ሞርያም ተራራ ላይ ነበር፤ ከብዙ ዓመታት በፊት አብርሃም ልጁ ይስሐቅን ለመሥዋዕት ያቀረበውም እዚያው ነበር።
  • በኋላ ላይ፣ “ጽዮን” እና፣ “የጽዮን ተራራ” የእነዚህ ተራሮችና የኢየሩሳሌም ከተማ አጠቃላይ መጠሪያ ሆነ። በኢየሩሳሌም ያለው ቤተ መቅደስ መጠሪያም ሆነ።
  • ዳዊት ጽዮንን ወይም ኢየሩሳሌምን፣ “የዳዊት ከተማ” አላት። ይህ የዳዊት ከተማ ተብሎ ከሚጠራው ዳዊት ከተወለደበት ቤተ ልሔም ከተማ የተለየ ነው።
  • እስራኤልን ወይም የእግዚአብሔር መንፈሳዊ መንግሥትን ወይም ከእግዚአብሔር ዘንድ የምትመጣው አዲሲቱ ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን በምሳሌነት ለማመልከትም፣ “ጽዮን” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ይውላል።