Key Terms

ሁሉን ቻይ

“ሁሉን ቻይ” የሚለው ቃል በቃል “ኃይል ሁሉ የእርሱ የሆነ” ማለት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሉም የሚያመልክተው እግዚኣብሔርን ነው።


ለኪዳኑ ታማኝ፣ ለኪዳኑ እውነተኛ

ይህ አገላለጽ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለሕዝቡ የሰጠውን ተስፋ ለመፈጸም ታማኝ መሆኑን ነው።


ሊቀ ካህን

“ሊቀ ካህን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተቀሩት እስራኤላውያን ካህናት መሪ በመሆን ለአንድ ዓመት እንዲያገለግል የተሾመ የተለየ ካህንን ያመለክታል።


ልብ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልብ የሰውን ሐሳብ፣ ስሜት፣ ፍላጎት ወም ፈቃድ ለማመልከት ብዙውን ጊዜ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።


ልዑል እግዚአብሔር

“ልዑል እግዚአብሔር” ከእግዚአብሔር መጠሪያዎች አንዱ ሲሆን፣ የእርሱን ታላቅነትና ሥልጣን ያመለክታል።


ልጅ፣ የ. . . ልጅ

“ልጅ” የሚለው ቃል ከወላጆቹ ጋር ካለው ግንኙነት አንፃር ትንሽ ልጅን ወይም ሰውን ያመለክታል። የአንድ ሰው ወንድ ወይም ሴት ልጅ ወይም እንደ ልጅ የተቀበለውን ሰው ያመለክታል


ልጅነት/ልጅ አድርጎ መቀበል

“ልጅነት” የተሰኘው ቃል አንድን ሰው በተፈጥሮ ወላጆቹ ያልሆኑ ሰዎች ሕጋዊ ልጅ የማድረግ ሂደት ያመለክታል።


ልጆች፣ ልጅ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ልጅ” የሚለው ቃል ሕፃንን ጨምሮ በአጠቃላይ በዕድሜ ወጣት የሆነውን ያመለክታል። “ልጆች” የብዙ ቊጥር ሲሆን፣ ጥቂት ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።

ይህ አባባል መንፈሳዊ ልጆች የሆኑ ሰዎችንም ያመለክታል። ለምሳሌ፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” ሲባል በኢየሱስ በማመን የእግዚአብሔር የሆኑ ሰዎችን ያመለክታል።


ሐሰተኛ አምላክ፣ ባዕድ አምላክ፣ ጣዖት

ሐሰተኛ አምላክ በአንዱ እውነተኛ አምላክ ቦታ ሰዎች የሚያመልኩት ነገር ነው። ወንድ ጣዖት እንዳለ ሁሉ ሴት ጥዖትም አለች።


ሐዋርያ ፣ ሐዋርያነት

ሐዋርያት ስለ እግዚአበሔር ስለ መንግሥቱ ለሰዎች እንዲሰበኩ እየሱስ የላካቸው ሰዎች ነበሩ፤ሐዋርያነት የሚለው ቃል ሐዋርያነት ለመሆን የተመረጡ ሰወች የነበራቸውን ቦታና ስልጣን ያመለክታል።


ሐዴስ፣ ሲኦል

ሞትንና ሰዎች ሲሞቱ የሚሄዱበትን ቦታ ለማመልከትት “ሐዴስ” እና “ሲኦል” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ ውለዋል። የሁለቱም ትርጕም ተመሳሳይ ነው።


ሕይወት፣ ሕያው፣ ሕይወት

እነዚህ ቃሎች ሁሉ የሚመለከቱት በሕይወት መሆንን፣ አለመሞትን ነው። መንፈሳዊ ሕያውነትን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላሉ። “ሥጋዊ ሕይወት” እና፣ “መንፈሳዊ ሕይወት” ሁለቱም ሕይወት ቢሆኑም፣ አንዱ ጊዜያዊ ሌላው ግን ዘላለማዊ ነው።


ሕግ፣ የሙሴ ሕግ፣ የእግዚአብሔር ሕግ፣ የያህዌ ሕግ

እነዚህ ቃሎች ሁሉ እስራኤላውያን እንደታዘዟቸው እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠውን ትእዝዞችና ትምህሮች የሚያመልክቱ ናቸው። “ሕጉ” እና፣ “የእግዚአብሔር ሕግ” የተሰኙት በአጠቃላይ እግዚአብሔር ሕዝቡ እንዲታዘዙ የሚፈልጋቸው ማንኛውንም ነገር ያመለክታሉ።


መለኮት

መለኮት የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር የሆነ ማንኛውንም ነገር ይመለከታል። ይህ ቃል ጥቅም ላይ ከሚውልባቸው መንገዶች ጥቂቶቹ “መለኮታዊ ሥልጣን”፣ “መለኮታዊ ፍርድ”፣ “መለኮታዊ ባሕርይ”፣ “መለኮታዊ ኃይል” እና፣ “መለኮታዊ ክብር የተሰኙት ናቸው።


መለየት

መለየት አንድን ነገር ወይም ሰው እግዚአብሔርን እንዲያገለግል መመደብ ማለት ነው። በዚህ መልኩ የተለየ ሰው ወይም እቃ ለእግዚአብሔር እንደ ተቀደሰና እንደ ተለየ ይቆጠራል።


መለየት

“መለየት” የሚለው ቃል አንድ ዓላማን ለመፈጸም ከአንድ ነገር ተለይቶ መውጣትን ያመለክታል


መልአክ፤የመላእክት አለቃ

መልአክ በእግዚአብሔር የተፈጠረ ሃያል መንፈዊ ፍጡር ነው፤መላአኮች የተፈጥጠሩት እርሱ የሚነግራቸውን በማድረግ እግዚአብሔርን እንድያገለግሉ ነው፤የመላክት አለቃ ሌሎች መላአኮችን ሁሉ የሚያዝዝ ወይም የ መልአክን ያመለክታል።

ለሰወች ሲናገር በመልአክ ተመስሎ የመጣ ራሱ እግዚአብሔር ሊያመለክት ይችላል፤አንድ መልአክ ያህዌ ራሱ የተናገረ ያህል’’እኔ’’እያለ የተናገረው ለምን እንደ ነበር ከእነዚህ ትርጉሞች አንዱ በቂ ገለጻ ይሰጠን ይሆናል።


መልካም፣ መልካምነት

“መልካም” የሚለው ቃል እንደ ምንባቡ ዐውድ ሁኔታ የተለያዩ ትርጕሞች ይኖሩታል። እነዚህን የተለያዩ ቃሎች ለመተርጎም የተለያዩ ቋንቋዎች የተለያዩ ትርጕሞች ያቀርባሉ።


መመለስ፣ መታደስ

“መመለስ” እና፣ “መታደስ” አንድን ነገር ቀድሞ ወደ ነበረበት ቦታ፣ ወደ ተሻለ ሁኔታ መመለስ ማለት ነው።


መመስከር፣ ምስክርነት

መመስከር አንድ ነገር እውነት መሆኑን መቀበል ወይም መናገር ማለት ነው። “ምስክርነት” አንድ ነገር እውነት መሆኑን በቃል ወይም በጽሑፍ በዚያም መስማማት ማለት ነው።


መመካት፣ ትምክህተኛ

“መመካት” በሰዎች ወይም በነገሮች በመመካት በትዕቢት መናገር ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ስለ አራስ በእብሪት መናገር ማለት ነው።


መማልጃ፣ ምልጃ

“መማለጃ” እና፣ “ምልጃ” በሌሎች ስፍራ ሆኖ ስለ እነርሱ መለመን ወይም መጸለይን ያመለክታል። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ስለሌሎች ከመጸለይ ጋር ነው።


መሠዊያ

መሠዊያ ለእግዚአብሔር መባ(ስጦታ)እንዲሆን እስራኤላውያን እንስሳትና የእህል ዓይነቶችን የሚያቃጥልበት ከፍ ብሎ የሚሠራ ነገር ነው።


መርሳት፣ ተረሳ

“መርሳት” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር ጨርሶ መተው ማለት ነው። “የተረሳ” በሌላው ወገን ጨርሶ የተተወ ግምት ውስጥ የማይገባ ሰው ነው።


መርገም፣ የተረገመ

“መርገም” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ላይ መጥፎ ነገር እንዲደርስበት ማድረግ ነው።


መስቀል

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን መስቀል አንድ ቀጥ ብሎ የወጣ እንጨት ሲሆን ጫፉ አካባቢ አንድ ሌላ ግንድ ይጋደምበት ነበር።


መስቀል (ሰውን)

“መስቀል” ማለት አንድን ሰው መስቀል ላይ ማሰርና በታላቅ ሕመምና ስቃይ እስኪሞት ድረስ እዚያው መተው ማለት ነው።


መሾም፤ይሾም

መሾም እና የተሾመ የተሰኙት ቃላት አንድ የተለየ ተግባርን ወይም ተልኮን እንዲሁም አንድን ሰው መምረጥን ያመለክታል።

እንዲቀበሉ ተመርጠዋል ማለት ነው።


መቀደ፣ ቅድስና

መቀደስ፣ ቅዱስ ይሆን ዘንድ አንድን ነገር መለየት ማለት ነው። ቅድስና ቅዱስ የመሆን ሂደት ነው


መቃባት፤የተቀባ

“መቀባት” የሚለው ቃል ሰውን ወይም አንድን ነገር በ ማሰብ ወይም ላይ ላይ ዘይት ማፍሰስ ማለት ነው፤አንዳንዴ ዘይቱ ከተለዩ ቅመሞች ጋር ስለሚቀላቀል በጣም ጣፋጭ መዕዛ ያለው ሽቶ ይሆናል፤ቃሉ ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ መንፈስ ቅዱስ ሰው መምረጡንና ሃይል ማስታጠቁን ያመለክታል።


መባረክ፣ ተባረክ፣ በረከት

አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር፣ “መባረክ” በዚያ ሰው ወይም ነገር ላይ መልካምና ጠቃሚ ነገር እንዲሆን ማድረግ ማለት ነው።


መተላለፍ

“መተላለፍ” ትእዛዝን፣ ደንብን ወይም ሕግን ማፍረስ ማለት ነው።


መታመን፣ ታማኝ፣ ታማኝነት

“መታመን” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር እውነት ወይም እምነት ሊጣልበት የሚገባ መሆኑን ያመለክታል። “ታማኝ” ሰው ትክክልና እውነት የሆነ ነገር እንደሚያደርግና እንደሚናገር እምነት ይጣልበታል።


መቶ አለቃ

መቶ አለቃ ከእርሱ ሥር 100 ወታደሮች የነበሩት የሮም ሰራዊት ባለ ሥልጣን ነበር።


መና

መና ከግብፅ ከወቱ በኋላ እስራኤል በምድረ በዳ ይንከራተቱ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሰጣቸው እንጀራ የመሰለ ስስ ምግብ ነበር።


መንፈስ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ፣ የጌታ መንፈስ

እነዚህ ሦስት ቃሎች የሚያመለክቱት እርሱ ራሱ እግዚአብሔር የሆነው መንፈስ ቅዱስን ነው። እውነተኛው አንድ አምላክ አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ የሚባሉ አካላት አሉት።


መንፈስ፥ መንፈሳዊ

“መንፈስ” የሚለው ቃል የሰዎችን ቁሳዊ ያልሆነና የማይታይ ክፍል ያመለክታል። ሰው ሲሞት መንፈሱ ከአካሉ ይለያያል


መኮነን፣ ኵነኔ

“መኮነን” እና “ኵነኔ” አንዳች በደል ከመፈጸሙ የተነሣ ሌላው ላይ መፍረድን ያመለክታል።


መወሰን፣ የተወሰነ

“መወሰን” እና፣ “የተወሰነ” የተሰኙት ቃሎች አንድ ነገር ከመሆኑ በፊት እንደዚያ እንዲሆን መቁረጥን ወይም ማቀድን ያመለክታሉ።

መንጠቅ፣ ንጥቂያ “መንጠቅ” የሚያመለክተው አንድን ነገር፣ ብዙውን ጊዜ ደግሞ ለምግብ የሚሆን እንስሳን ማደንን ነው።


መዋጀት

“መዋጀት” የሚለው ቃል በሌሎች ተወስዶ የነበረ ነገርን በመግዛት የራስ ማድረግ ማለት ነው።


መውረስ፣ ውርስ፣ መብት፣ ወራሽ

“መውረስ” እና፣ “ውርስ” ከእነርሱ ጋር ካለ የተለየ መቀራረብ የተነሣ ከወላጆቹ ወይም ከሌሎች ጠቃሚ ነገር መቀበል ማለት ነው። ያንን ውርስ የሚቀበል ወራሽ ይባላል።


መዓት፣ ቁጣ

መዓት ለረጅም ጊዜ የሚቆይ በጣም ከባድ ቁጣ ነው። ብዙውን ጊዜ ኀጢአት ላይ የሚመጣውን የእግዚአብሔር ጻድቅ ፍርድና በእርሱ ላይ የሚያምፁ ሰዎችን ቅጣት ያመለክታል።


መዝሙር

ቅዱስ ዝማሬ፣ ብዙ ጊዜ በሙዚቃ የታጀበ ግጥም ወይም ቅኔ ማለት ነው። ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለው መጽሐፈ መዝሙር በእስራኤላውያን የተጻፉ የመዝሙሮች ስብስብ ይዟል።


መገረዝ፣ ግዝረት

“መግረዝ” ከወንድ ወይም ወንድ ከሆነ ትንሽ ልጅ ብልት ትርፍ የሆነውን ቆዳ መቊረጥ ማለት ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የግርዘት ሥርዓት ሊኖርም ይችላል።


መገናኛ ድንኳን

መገናኛ ድንኳን እስራኤላውያን 40 ዓመት በምድረ በዳ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሚያመልኩበት ድንኳን መሰል ነገር ነበር


መግለጽ፣ መገለጽ (ራእይ)

“መግለጽ” አንድ ነገር እንዲታወቅ ማድረግ ማለት ነው “መገለጽ” እንዲታወቅ የተደረገ ነገር ነው።


መጣስ፣ መዳፈር

“መጣስ” ሕግ ማፍረስ ወይም የሌሎችን መብት መንካት ማለት ነው።


መጥራት፣ ጥሪ፣ ተጠራ፣ መጣራት

“መጥራት” እና “መጣራት” የተሰኙ ቃሎች ቅርብ ላልነበረ ሰው ጮኽ ብሎ አንዳች ነገር መናገር ማለት ነው። ሌሎች ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሏቸው።


መጥፋት፣ ጥፋት፣ የሚጠፋ

“መጥፋት” የሚለው ቃል አብዛኛውን ጊዜ በአንድ ዓይነት ጥቃት ወይም አደጋ የተነሣ መሞት ወይም መደምሰስ ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለይ ለዘላለም በገሃነም መቀጣት የሚል ትርጕም አለው።


መጸለይ፣ ጸሎት

መጸለይ ለእግዚአብሔር መናገር ነው።


መፈተን፣ ፈተና

መፈተን አንድ ሰው ተገቢ ያልሆነ ነገር እንዲያደርግ መሞከር ማለት ነው።


መፈጸም

“መፈጸም” አንዳች የሚጠበቅ ነገርን ፈጽሞ ወይም አከናውኖ መገኘት ማለት ነው።


ማመን፥ አመነ፥ እምነት

“ማመን” እና “አመነ” በጣም የተያያዙ ቢሆንም በመጠኑ የሚለያይ ትርጉም አላቸው


ማምለክ፣ መስገድ

“ማምለክ፣ መስገድ” እግዚአብሔርን ማክበር፣ ማመስገንና ለእርሱ መታዘዝ ማለት ነው።


ማሰር፣ ማሰሪያ፣ አሰረ

“ማሰር” አንድን ነገር ጥብቅ አድርጎ ማሰር ወይም እንዳይበታተን አድርጎ መቋጠር ማለት ነው። አንድ ነገር የሚያስር ወይም እርስ በርስ የሚያያይዝ፣ “ማሰሪያ” ይባላል።


ማስተሰሪያ

“ማስተሰረያ” የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ፍትሕ ለማርካት ወይም ለመፈጸምና ቁጣውን ለማስታገሥ የሚቀርብ መሥዋዕት ነው።


ማስታረቅ፣ ዕርቅ

“ማስታረቅ” እና፣ “ዕርቅ” ቀድሞ እርስ በርስ ይጠላሉ በነበሩ ሰዎች መካከል፣ “ሰላም ማድረግ” ማለት ነው።


ማበረታታት

“ማበረታታት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች ትክክልና እውነት የሆነውን ነገር እንዲያደርጉ ማደፋፈርን ነው።


ማዘዝ፣ ትእዛዝ

ማዘዝ ማለት አንዳች ነገርን እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ለሰዎች መናገር ማለት ነው። ትእዛዝ የሚባለው እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ለሰዎች የተሰጠው መመሪያ ነው።


ማዳን፣ ደኅንነት

“ማዳን” አንድን ሰው ከአንዳች መጥፎ ወይም ጎጂ ነገር መጠበቅ ማለት ነው “ደኅንነት” ከጉዳት ወይም ከአደጋ የተጠበቀ ማለት ነው


ማጥመቅ፥ ጥምቀት

አዲስ ኪዳን ውስጥ “ማጥመቅ” እና፥ “ጥምቀት” የተሰኙ ቃሎች ብዙውን ጊዜ ከኃጢአት መንጻቱንና ከክርስቶስ ጋር መተባበሩን ለማሳየት ክርስቲያኑን ውሃ ውስጥ የመንከር ስርዓትን ያመለክታል


ምልክት፥ ማረጋገጫ፣ ማሳሰቢያ

ምልክት የተለየ ትርጉም ያለው መልእክት የሚያስተላልፍ ዕቃ፣ ሁኔታ ወይም ድርጊት ሊሆን ይችላል


ምሕረት፣ መሐሪ

“ምሕረት” እና፣ “መሐሪ” የተሰኙት ቃሎች ችግር ውስጥ በተለይም እጅግ በተዋረደ ዝቅረኛ ደረጃ ያሉ ሰዎችን መርዳትን ያመለክታሉ።


ምሳሌ

ምሳሌ ግብረ ገባዊ ወይም ሃይማኖታዊ ትምህርት ለማስተማር የሚቀርብ አጭር ታሪክ ነው።


ምስክር፣ መመስከር

“ምስክር” እና፣ “መመስከር” አንድን ነገር በተመለከተ የሚያውቁትን እውነት በግልጽና በሰው ሁሉ ፊት መናገር ማለት ነው።


ምኩራብ

ምኩራብ አይሁድ እግዚአብሔርን ለማምለክ የሚሰበሰቡበት ቦታ ነው። ከጥንት ዘመን ጀምሮ ምኩራቦች ለጸሎት፣ ቅዱሳት መጽሐፍትን ለማንበብና ለመማር አገልግሎት ላይ ውለው ነበር


ሞኝ፣ ሞኝነት፣ ከንቱነት

“ሞኝ” የሚባለው ብዙውን ጊዜ የተሳሳተ ምርጫ የሚያደርግ በተለይም አለመታዘዝን የሚመርጥ ሰው ነው። “ሞኝነት” ማስተዋል የሌለው ሰው ወይም ፀባይ የሚገለጥበት መንገድ ነው።


ሞገስ፣ ሞገስ ያለው፣ አድልዎ (ከሌሎች የተለየ ሞገስ የሚደረግለት)

ሞገስ እርሱን በተመለከተ ጥሩ አመለካከት ያለንን ሰው ለመጥቀም የሚደረግ ነገርን ያመለክታለ። “ሞገስ ያለው” ነገር ቀና ተቀባይነት ያለው ወይም ጠቃሚ ነው።


ሥልጣን

“ሥልጣን” የተሰኘው ቃል አንድ ሰው ሌላው ሰው ላይ ያለውን ተፅዕኖ የማሳደር ወይም የመቆጣጠር ኅይልን ያመለክታል


ሥራዎች፣ ተግባሮች፣ ሥራ፣ ተግባር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሥራዎች”፣ “ተግባሮች” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ የዋሉት እግዚአብሔር ወይም ሰዎች ያደረጉትን በአጠቃላይ ለማሳየት ነው።


ሥርዓት፥ ራስን መግዛት ወይም ራስን በሥርዓት መምራት

“ሥርዓት” ለተወሰኑ ግብረ ገባዊ መመሪያዎች እንዲታዘዙ ሰዎችን መሠልጠንን ነው የሚያመለክተው።


ሥጋ

መጽሐፍ ቅዱስ ሥጋ ሲል ቃል በቃል የሰውን ወይም የእንስሳን ለስላሳውን የአካል ክፍል ያመለክታል።


ረቢ፣ ረቡኒ

ቃል በቃል፣ “ረቢ” – “ጌታዬ” ወይም፣ “መምህሬ” ማለት ነው።


ርኅራኄ፣ ርኅሩኅ

“ርኅራኄ” ለሰዎች ማሰብ፣ አተለይም መከራ ለደረሰባቸው ሰዎች እነርሱ ቦታ ሆኖ ስሜታቸውን መጋራትን ያመለክታል። “ርኅሩኅ” ሰው ለሌሎች ሰዎች ያስባል እነርሱንም ይረዳል።


ርኩሰት

“ርኩሰት” የሚለው ቃል ትርጉም፣ “ኀጢአት” ከሚለው ጋር በጣም ተመሳሳይ ቢሆንም በተለይ፣ ሆን ተብሎ የሚፈጸም በደልን ወይም ታላቅ ዐመፃን ሊያመለክት ይችላል።


ሰማይ፣ ሰማያት፣ ሰማያዊ

“ሰማይ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል የእግዚአብሔር መኖሪያን ያመለክታል።


ሰንበት

ሰንበት የሳምንቱ ሰባተኛ ቀን ነው፤ ይህ ቀን ምንም ሥራ የማይሠራበት የዕረፍት ቀን እንዲሆን እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዝዞ ነበር።


ሰይጣን፣ ዲያብሎስ፣ ክፉው

ዲያብሎስ እግዚአብሔር የፈጠረው መንፈሳዊ አካል ነበር፤ በእግዚአብሔር መማመፁ የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ። ዲያብሎስ፣ “ሰይጣን” እና፣ “ክፉው” ተብሎ ይጠራል


ሰዱቃውያን

ሰዱቃውያን ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያላቸው የአይሁድ ካህናት ነበሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ባገለገለ ዘመን የነበረውን የሮም አገዛዝ ይደግፉ ነበር። በሙታን ትንሣኤ አያምኑም


ስም

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስም በተለያዩ ምሳሌያዊ አነጋገርና ጥቅም ላይ ውሏል።


ስእለት

ስእለት አንድ ሰው ለእግዚአብሔር የሚገባው ቃል ነው። እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ሁኔታ ለማክበር ወይም ም ያህል ለእርሱ የተሰጠ መሆኑን ለማሳየት አንድ ሰው አንድ ነገር እንደሚያደርግ ለእግዚአብሔር ቃል ይገባል።


ስድብ፣ ተሰደበ

መጽሐፍ ቁስ ውስጥ፣ “ስድብ” እግዚአብሔርንና ሰውን በጣም በሚያንቋሽሽ መንገድ መናገርግን ያመለክታል። አንድን ሰው፣ “መስደብ” ሰዎች ሐሰት የሆነ መጥፎ ነገር እንዲያስቡ በዚያ ሰው ላይ ክፉ ነገር መናገር ማለት ነው።


ስጦታ

“ስጦታ” የሚለው ለሌላው ወገን የተሰጠ ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ስጦታ የሚሰጠው በምላሹ ምንም ነገር ባለ መጠበቅ ነው።


ቀናተኛ፣ ቅናት

“ቀናተኛ” እና “ቅናት” የተሰኙት ቃሎች አንድ ሰው የግል የማድረግ ጽኑ ፍላጎት ያመለክታሉ። አንድን ነገር ወይም ንብረት አጥብቆ የመያዝ ፍላጎትንም ያመለክታል።


ቀኝ እጅ

“ቀኝ እጅ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር፣ በአንድ መሪ፣ ወይም ሥልጣን ባለው ሰው ቀኝ ያለውን የክብር ቦታ ያመለክታል።


ቅንዓት፣ ቀናተኛ (ቀናዒ)

“ቅንዓት” እና፣ “ቀናተኛ” የአንድ ሰው ወይም ሐሰብ ጠንካራ ደጋፊ መሆንን ያመለክታል።


ቅዱሳን

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ቅዱሳን” – “ቅዱስ የሆኑ ሰዎች” ማለት ሲሆን፣ በኢየሱስ ያመኑ ወገኖችን የመለክታል


ቅዱስ

“ቅዱሱ” የሚለው መጠሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሌም የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው።


ቅዱስ ቦታ

“ቅዱስ ቦታ” ቃል በቃል እግዚአብሔር የሚቀደስበትና የሚመለክበት የተለይ ቦታ ማለት ነው። ከለላና ደኅንነት የሚገኝበትንም ቦታ ሊያመለክት ይችላል


ቅዱስ፣ ቅድስና

“ቅዱስ” እና “ቅድስና” ኀጥእ ከሆነውና ፍጽምና ከሌለው ማንኛውም ነገር ፍጹም ልዩ የሚያደርገውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ ያመለክታል።


ቅድስት፣ ቅድስተ ቅዱሳን

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ቅድስት” እና፣ “ቅድስተ ቅዱሳን” የተሰኙ ቃሎች መገናኛው ድንኳን ወይም ቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩ ሁለት ክፍሎች ያመለክታሉ። አንዳንዴ፣ “ቅድስት” ወይም፣ “ቅዱስ ቦታ” የሚለው በጠቅላላው ለእግዚአብሔር የለለየ ማንኛውንም ቦታ ያመለክታል።


በመንፈስ መሞላት

“በመንፈስ ቅዱስ መሞላት” የሚለው አገላለጽ የእግዚአብሔር ፈቃድ ማድረግ እንዲችል መንፈስ ቅዱስ ለሰው የሚሰጠውን ኅይል የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው።


በግ፣ የእግዚአብሔር በግ

በግ ጥቅጥቅ ያሉ ለሱፍ መሥሪያ የሚያገለግሉ ጠጉሮች ያሉት ባለ አራት እግር እንስሳ ሲሆን፣ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይቀርባል። እርሱ ለሕዝቡ ኃጢአት መሥዋዕት ሆኖ በመሞቱ ኢየሱስ፣ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሏል።


ቤተ መቅደስ

ቤተ መቅደስ እስራኤል ለጸሎትና ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ የሚሰበሰቡበት ዙሪያውን በተከበበ አደባባይ ውስጥ ያለ ሕንፃ ነው። ቤተ መቅደስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ባለው የሞሪያ ተራራ ነበር።


ቤተ ክርስቲያን

በአዲስ ኪዳን መሠረት ቤተ ክርስቲያን የሚባለው ለመጸለይና የእግዚአብሔር ቃል ሲሰበክ ለመስማት ዘወትር የሚሰበሰቡ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች ስብስብ ነው። “ቤተ ክርስቲያን” ብዙውን ጊዜ፣ ክርስቲያኖችን ሁሉ ያመለክታል።


ቤዛ

“ቤዛ” የሚለው ቃል በምርኮ የተያዘ ሰውን ለማስለቀቅ እንዲከፈል የተጠየቀ ገንዘብ ወይም ሌላ ነገር ያመለክታል።


ቤዛነት፥ቤዛ

“ቤዛ” እና “ቤዛነት” ለሰው ልጆች ኃጢአት የሚከፈልና የእርሱን በኃጢአት መቆጣት የሚያበርድ መሥዋዕት እግዚአብሔር ያዘጋጀበትን ሁኔታ ያመለክታል


ተስፋ

ተስፋ አንድ መልካም ነገር ይሆናል ብሎ መጠበቅና የተሻለ ነገር እንደሚመጣ መጠባበቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “ተስፋ” እግዚአብሔር ለሕዝቡ ቃል የገባውን እንደሚቀበሉ እርግጠኛ ሆ መጠበቅን ነው የሚያመለክተው። ይሁን እንጂ፣ አንድን ነገር እርግጠኛ ሆኖ ወይም በልበ ሙሉነት መጠበቅን የሚያመለክት በመሆኑ ULB በተሰኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም አብዛኛውን ጊዜ፣ “እምነት” ወይም፣ “ድፍረት” ተብሎ ተተርጕሞአል።


ተስፋ ቃል

ተስፋ ቃል አንድን ነገር ለመስጠት ወይም ለማድረግ ቃል መግባት ማለት ነው። አንድ ሰው አንድ ነገር ለማድረግ ተስፋ ከሰጠ ያንን ለመፈጸም ይተጋል ማለት ነው።


ተአምር፣ ድንቅ፣ ምልክት

“ተአምር”እግዚአብሔር ራሱ ካላደረገው በቀር ጨርሶ ሊሆን የማይችል አስደናቂ ነገር ነው።


ታማኝ፣ ታማኝነት

ለእግዚአብሔር፣ “ታማኝ” መሆን ዘወትር በእርሱ ትምህርት መኖር ማለት ነው። ለእርሱ በመታዘዝ እውነተኛነትን ማሳየት ማለት ነው ታማኝ ሆኖ የመገኘት ሁኔታ፣ “ታማኝነት” ይባላል።


ታቦት


ትሑት፣ ትሕትና

ትሑት ሰው ከሌሎች ሁሉ የበለጠ እንደ ሆነ አያስብም። ትዕቢተኛ ወይም እብሪተኛ አይደለም።


ትሩፍ፣ ትሩፋን

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ትሩፋን” ማለት፣ በጣም ብዙ ከሆነው ክፍል ወይም ወገን “የተረፉ” ወይም፣ “የቀሩ” ሰዎች ወይም ነገሮች ማለት ነው።


ትንሣኤ

“ትንሣኤ” ከሞት በኋላ ተመልሶ ወደ ሕይወት መምጣት ነው።


ትክክል፣ ፍትሕ፣ በፍትሕ

እነዚህ ቃሎች የሚያመለክቱት በእግዝአብሔር ቃል መሠረት ሰዎችን በአግባቡ መያዝን ወይም ማስተናገድን ነው። ትክክል የሆነውን የእግዚአብሔር መስፈርት የሚያንጸባርቁ የሰው ልጆች ሕጎችም ፍትሕ ይባላሉ።


ኀይል፣ ኀይላት

“ኀይል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብዛኛውን ጊዜ በታላቅ ብርታት ነገሮችን ማድረግን ወይም ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ችሎታን ነው። “ኀይላት” የሚያመለክተው ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ታላቅ ችሎታ ያላቸው ሰዎችን ወይም መናፍስትን ነው።


ኅሊና

ኅሊና አንድ ሰው ኃጢአት እያደረገ መሆኑን እግዚአብሔር ለእርሱ የሚያሳውቅበት የሰውየው አስተሳሰብ አንድ ክፍል ነው።


ኅብረት

አጠቃላይ በሆነ ደረጃ፣ “ኅብረት” ተመሳሳይ ፍላጎትና ልምምድ ያላቸው የአንድ ማኅበር አባሎች መካከል የሚደረግ የወዳጅነት ግንኙነትን ያመለክታል።


ኅጢአት፣ ኅጥእ፣ ኅጢአተኛ፣ ኅጢአት ማድረግ

“ኅጢአት” የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር የሚደረግ ተግባርን፣ ሐሳብንና ቃልን ያመለክታል። እግዚአብሔር ያዘዘውን አለማድረግም ኅጢአት ነው


ነቀፋ የሌለበት

“ነቀፋ የሌለበት” የሚለው ቃል በቃል፣ “ነውር፣ እንከን” የሌለበት ማለት ነው። በፍጹም ልቡ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝ ሰውን የሚያመለክት ቢሆንም፣ ያ ሰው ምንም ኃጢአት የለበትም ማለት አይደለም።


ነቢይ፣ ትንቢት፣ ትንቢት ተናገረ፣ ተመልካች፣ ነቢዪት

“ነቢይ” የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው። ይህን የምታደርግ ሴት ነቢዪት ትባላለች።


ነጻ

“ነጻ” የሚለው ቃል ወንጀል ከመፈጸም ወይም ከሌሎች በደሎች ነጻ የሆነ ማለት ነው። በጠቅላላው በማንኛውም ክፉ ነገር አለመሳተፉን ያመለክታል።


ነፍስ

ነፍስ የሰው ውስጣዊ፣ የማይታይና ዘላለማዊ ክፍል ነው። የሰውን ቁሳዊ ያልሆነ ነገር ሁሉ ይጨምራል


ናዝራዊ፣ የናዝራዊ ስእለት

ናዝራዊ የሚባለው ናዝርውያን የሚሳሉትን ስእለት የተሳለ ሰው ነው።


ንስሐ መግባት፣ ንስሐ

“ንስሐ መግባት” እና፣ “ንስሐ” ከኀጢአት ወደ እግዚአብሔር መመለስን ያመለክታል።


ንጹሕ፣ ማንጻት

“ንጹሕ” መሆን እንከን የሌለው ወይም እዚይ ኣመገኘት ያልነበረበት የተቀላቀለ ነገር የሌለው ማለት ነው። አንድን ነገር ማንጻት ማለት ንጹሕ ማድረግና የሚያቆሽሸውንና የሚበክለውን ማንኛውንም ነገር ማስወገድ ማለት ነው።


ንጽሕ፣ ማንጻት

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ንጹሕ” ምንም ቆሻሻ ወይም እድፍ የሌለበት ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ቅዱስ” እና “ከኃጢአት የነጻ” የሚሉትን ለማመልከት በምሳሌያዊ አነጋገር ጥቅም ላይ ይውላል።


አሕዛብ

አሕዛብ የያዕቆብ ወይም የአሥራ ሁለቱ የእርሱ ልጆች ዘር ያልሆነ ሰው ነው። ስለሆነም አሕዛብ አይሁድ አይድለም ማለት ነው።


አሜን፣በእውነት ይሁን

“አሜን” የሚለውለንድ ሰው የተናገረውን አጽንዖት ለመስጠት ወይም ትኩረት እንዲሰጠው ለማድረግ ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። ኢያሱስ ይህን ቃል ሲናገር ብዙውን ጊዜ አሜን ይሁን እንደ ማለት ነው።


አምላካዊ፣ አምላካዊነት

“አምላካዊ” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን በሚያስከብርና የእግዚአብሔርን ማንነት በሚያሳይ መንገድ የሚኖር ሰውን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል። የእግዚአብሔርን ፈቃድ በማድረግ እርሱን የማያከብር ሰው ባሕርይ አምላካዊነት ይባላል።


አሥራ ሁለቱ፣ አሥራ አንዱ

“አሥራ ሁለቱ” የቅርብ ደቀ መዛሙርቱ ወይም ሐዋርያቱ እንደሆኑ ኢየሱስ የመረጣቸው አሥራ ሁለት ሰዎች ናቸው። ይሁዳ ራሱን ከገደለ በኋላ፣ “አሥራ አንዱ ቀሩ።


አካል

“አካል” ቃል በቃል የሰው ወይም የእንስሳ ሥጋ ማለት ነው። ይህ ቃል አንድን ነገር ወይም በአንድ ቡድን ውስጥ ያሉ ግለ ሰቦችን ለማመልከትም ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።


አይሁድ፣ አይሁዳዊ

አይሁድ በልጅ ልጁ በያዕቆብ በኩል የአብርሃም ዘር የሆኑ ሕዝብ ናቸው።


አዳኝ

“አዳኝ” የሚለው ቃል ሌሎችን የሚያድን ወይም የሚታደግ ሰውን ያመለክታል። ለሌሎች ብርታትን ወይም የሚያስፈልጋቸውን የሚሰጥ ሰውንም ያመለክታል


አገልጋይ፣ አገልግሎት

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “አገልጋይ” እና፣ “አገልግሎት” የተሰኙት ቃሎች እግዚአብሔርን በተመለከተ ሰዎችን በማስተማር፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታቸውም በማሰብ ሌሎችን መርዳት ማለት ነው። በዚህ መልኩ ሰዎችን የሚረዳ ሰው አገልጋይ ይባላል።


አጋንንት ያደሩበት

አጋንንት ያደሩበት ሰው የሚያደርገውንና የሚያስበውን የሚቆጣጠሩ አጋንንት ወይም ክፉ መናፍሳት ውስጥ ይኖራሉ።


ኢየሱስ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ክርስቶስ ኢየሱስ

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ኢየሱስ ማለት፣ “ያህዌ ያድናል” ማለት ነው። “ክርስቶስ” “የተቀባው” የሚል ትርጉም ያለው ቃል ሲሆን፣ መሲህ የሚለው ሌላ ቃል ነው።


ኤፉድ

ኤፉድ እስራኤላውያን ካህናት ይለብሱት የነበረ መጎናጸፊያ ዐይነት ጨርቅ ነው። ትከሻ ላይ የሚገናኙ የፊትና የኋላ የሚባሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት፤ ከዚያም በጨርቅ መታጠቂያ ወገብ ላይ ይታሰር ነበር።


እምነት

በአጠቃላይ ደረጃ “እምነት” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር፣ በሰው ወይም፣ በነገሮች መተማመንን፣ መደገፍን፣ ወይም፣ መመካትን ነው።


እምነት የለሽ እምነት ወይም የሚተማመንበት የሌለው ማለት ነው።

እምነት የለሽ፣ እምነት የለሽነት


እስራኤል፣ እስራኤላውያን፣ የእስራኤል ሕዝብ

እስራኤል እግዚአብሔር ለያዕቆብ የሰጠው ስም ነው። እስራኤል፣ “ከእግዚአብሔር ጋር ታገለ” ማለት ነው።


እንደ ገና መወለድ፣ ከእግዚአብሔር መወለድ፣ አዲስ ልደት

ኢየሱስ፣ “እንደ ገና መወለድ” በሚለው ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው እግዚአብሔር አንድን መንፈሳዊ ሙት የሆነ ሰው መንፈሳዊ ሕያው እንዲሆን እንደሚለውጠው ለማመልከት ነበር። “ከእግዚአብሔር መወለድ” ወይም፣ “ከመንፈስ መወለድ” የተሰኙትም ቃሎች አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት የተሰጠውን ሰው ያመለክታሉ።


እውነት፣ እውነተኛ

“እውነት” የሚለው ቃል ይተረጋገጠ ፅንሰ ሐሳብን፣ በትክክል የተፈጸመ ሁኔታንና በእርግጥ የተነገረ ቃልን ያመለክታል።


እግዚአብሔር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር አጽናፈ ዓለሙን ከምንም ያስገኘው ዘላለማዊ ፈጣሪን ያመለክታል። እግዚአብሔር አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በሚባሉ ሦስት አካሎች ተገልጧል። የእግዚአብሔር ተፀውዖ (መጠሪያ) ስም፣ “ያህዌ” ነው።


እግዚአብሔር አብ፣ ሰማያዊ አባት፣ አባት

“እግዚአብሔር አብ” እና፣ “ሰማያዊ አባት” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት አንዱን እውነተኛ አምላክ ያህዌን ነው። ይህ ቃል በተለይም ኢየሱስ ሲጠቀምበት “አባት” ተብሎም ተጠርቷል።


ከርቤ

ከርቤ ከተለየ ዐይነት ዛፍ ሙጫ የሚዘጋጅ ቅመም ነው።


ከፍ ማድረግ፣ ከፍታ

ከፍ ማድረግ በከፍተኛ ደረጃ ማመስገንና ማክበር ማለት ነው። ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ማድረስንም ያመለክታል።


ኪዳን

ኪዳን አንዱ ወይም ሁለቱም የሚፈጽሙት በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ መደበኛ አሳሪ ስምምነት ነው።


ካህን፣ ክህነት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካህን ሕዝብን በመወከል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚያቀርብ ሰው ነው። “ክህነት” እንዲህ ላለው ሰው ተግባር የተሰጠ ስም ወይም ቦታ ነው።


ክርስቲያን

ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከሄደ ጥቂት ጊዜ በኋላ ስዎች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም አወጡ፤ ክርስቲያን የክርቶስ ተከታይ ማለት ነው።


ክርስቶስ፣ መሲሕ

“መሲሕ” ወይም፣ “ክርስቶስ” የሚለው ቃል፣ “የተቀባ” ማለት ሲሆን፣ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስን ነው የሚያመለክተው።


ክብር፣ ማክበር

“ክብር” የሚለው ቃል ለእግዚአብሔር ወይም ለሰው ልጅ የሚሰጥ የላቀ ቦታ፣ ግምት ወይም አክብሮታዊ ፍርሃት ነው።


ክብር፣ የከበረ

በአጠቃላይ “ክብር” ማለት ምስጋና፣ ውበትና የላቀ ታላቅነት ማለት ነው። ክብር ያለው ነገር “የከበረ” ይባላል።


ክፉ፣ ዐመጽ(ዐመጸኛ)፣ ዐመጻ

“ክፉ” እና “ዐመጸኛ” የተሰኙት ቃሎች ሁለቱም የእግዚአብሔርን ቅዱስ ባሕርይና ፈቃድ የሚቃወም ማንኛውንም ነገር ያመለክታሉ።


ወንድም

ብዙውን ጊዜ ወንድም የሚባለው ቢያንስ ከወላጆች ከአንዱ የተወለደ ወንድ ልጅ ነው።


ወንጌላዊ

“ወንጌላዊ” የኢየሱስ ክርስቶስን የምሥራች(ወንጌል) ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው።


ወዮ

“ወዮ” ከፍ ያለ ጭንቀትና ሐዘንን ያመለክታል። ስለሚመጣው ከባድ ጥፋት ማስጠንቀቂያም ይሆናል።


ዋይታ፣ ሰቆቃ

“ዋይታ” እና፣ “ሰቆቃ” የተሰኙት ቃሎች የከባድ ለቅሶ፣ ሕዘን ወይም ትኬ መገለጫዎች ናቸው።


ዓለም፣ ዓለማዊ

ብዙውን ጊዜ፣ “ዓለም” የሚያመለክተው አጽናፈ ዓለሙ ውስጥ ሰዎች የሚኖሩበትን ማለትንን ማለትን ምድርን ነው። “ዓለማዊ” በዚህ ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ክፉ መንገድና አሠራር ያመለክታል።


ዕብራዊ

“ዕብራውያን” በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ሐረግ በኩል የተገኙ የአብርሃም ዘሮች ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ዕብራዊ” ተብሎ የተጠራ የመጀመሪያ ሰው አብርሃም ነበር። “ዕብራውያን” በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ሐረግ በኩል የአብርሃም ዘር የሆኑ ሕዝብ ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ዕብራው” ተብሎ የተጠራ የመጀመሪያ ሰው አብርሃም ነው።


ዘላለም፣ ዘላለማዊ

“ዘላለም” እና “ዘላለማዊ” በጣም ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆን፣ የሚያመለክቱት ሁሌም የሚኖር ወይም ማለቂያ ማብቂያ የሌለውን ነገር ወይም ሁኔታ ነው።


ዝሙት፣ዘማዊነት፣ዘማዊ፣ዘማዊት

“ዝሙት” አንድ ያገባ ሰው የትዳር ጓደኛው ካልሆነች ጋር ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን ኃጢአት ያመለክታል። “ዘማዊነት”የዚህ ዐይነት ተግባርን ወይም ይህን ኃጢያት የሚያደርግ ሰው ድትጊት ያመለክታል።


የመወለድ መብት

“የመወለድ መብት” የተሰኘው ቃል ከቤተ ሰቡ የተወለዱ የመጀመሪያ ወንድ ልጅ ያለውን ክብር፣ ከቤተ ሰቡ መጠራትንና ሀብት መወሰድን መደበኛ መብት ያመለክታል።


የመጨረሻ ቀን፣ የመጨረሻዎቹ ቀኖች፣ የኋለኞቹ ቀኖች

“የመጨረሻ ቀን” ወይም፣ “የመጨረሻዎቹ ቀኖች” በአጠቃላይ የሚያመለክቱት በአጠቃላይ ኢየሱስ ወደሚመለስበት ጊዜ የሚያደርሱ ወቅቶች ናቸው።


የሚገባው፣ ዋጋ ያለው፣ የማይገባው፣ ዋጋ ቢስ

“የሚገባው” የሚለው ቃል ክብርና ምስጋና መቀበል ያለበትን ያመለክታል። “ዋጋ ያለው” ውድ ወይም ጠቃሚ ነገርን ያመለክታል። “ዋጋ ቢስ” ግን ለምንም የማይጠቅም ማለት ነው።


የማእዘን ድንጋይ

“የማእዘን ድንጋይ” የሚለው ሐረግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ተጠርቦ የሕንጻው መሠረት አንድ ጥግ ላይ የሚቀመጥ ትልቅ ድንጋይ ነው።


የምሥራች፣ ወንጌል

ቃል በቃል የምሥራች ማለት ሲሆን፣ ሰዎችን የሚጠቅምና ደስ የሚያሰኛቸውን መልእክት ያመለክታል።


የሰራዊት ጌታ ያህዌ፣ የሰራዊት ጌታ፣ ሰራዊት

“የሰራዊት ጌታ ያህዌ” እና፣ “የሰራዊት ጌታ” የሚሉት ሐረጎች ለእርሱ በሚታዘዙ እጅግ ብዙ መላእክት ላይ እግዚአብሔር ያለውን ሥልጣን የሚገልጡ አባባሎች ናቸው።


የሰው ልጅ

የሰው ልጅ“የሰው ልጅ” የሚለው ሐረግ ብዙ ጊዜ ኢየሱስ ራሱን የሚጠራበት ስም ነበር። ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “የሰው ልጅ” ማንኛውም ሰው የሚታወቅበት ስም ነበር

ጥቅሶች እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታሉ


የስርየት መክደኛ

“የስርየት መክደኛ” ከወርቅ የተሠራ ጠፍጣፋ ነገር ሲሆን የታቦቱን የላይኛ ክፍል ለመሸፈን ጥቅም ላይ ይውል ነበር። አንዳንድ ትርጉሞች “የስርየት መሸፈኛ” ይሉታል


የበደል መሥዋዕት

“በደል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኀጢአት ማድረግን ወይም ወንጀል መፈጸምን ነው።


የተመረጠ፣ የተመረጠ ሕዝብ፣ የተመረጠው፣ ምርጦች

“የተመረጠ” ወይም፣ “ምርጦች” የሚለው ቃል በቃል፣ “የተመረጡት” ወይም፣ “የተመረጠ ሕዝብ” ማለት ሲሆን አባባሉ የእርሱ ሕዝብ እንደሆኑ እግዚአብሔር የመደባቸውን ወይም የመረጣቸውን ያመልክታል። “የተመረጡ” ወይም፣ “በእግዚአብሔር የተመረጠው፣ የተመረጠ መሲሕ የሆነው የኢየሱስ መጠሪያ ነው።


የተስፋ ምድር

“የተስፋ ምድር” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እንጂ በጠቅላላው መጽሐፍ ቅዱስ አይደለም። ለአብርሃምና ለዘሮቹ እንደሚሰጥ እግዚአብሔር ቃል የገባላት የምድረ ከነዓን አማራጭ ቃል ነው።

ነቢይ፣ ትንቢት፣ ትንቢት ተናገረ፣ ተመልካች፣ ነቢዪት “ነቢይ” የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው። ይህን የምታደርግ ሴት ነቢዪት ትባላለች።


የተወደደ

“የተወደደ” በሌላው ሰው የተወደደና ውድ የሆነ ሰውን የሚያሳይ የፍቅር መገለጫ ቃል ነው


የአራተኛው ክፍል ገዥ

የአራተኛው ክፍል ገዥ የሚባለው የሮም መንግሥትን የተወሰነ ክፍል በመግዛት ላይ ያለ ባለ ሥልጣንን ነው። እያንዳንዱ የአራተኛው ክፍል ገዥ ከሮም ንጉሥ ሥልጣን ሥር ነበር።


የአይሁድ ንጉሥ


የእግዚአብሔር ልጅ፣ ልጁ፣ ልጅ(ወልድ)

“የእግዚአብሔር ልጅ” ሰው ሆኖ ወደ ዓለም የመጣውን ቃል ኢየሱስን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ፣ “ልጁ” ተብሎም ይጠራል


የእግዚአብሔር ልጆች

“የእግዚአብሔር ልጆች” በርካታ ትርጉሞች ያሉት ምሳሌያዊ አነጋገር ሊሆን ይችላል


የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ ሕዝቤ

“የእግዚአብሔር ሕዝብ” የተሰኘው ሐረግ ከእርሱ ጋር የተለየ ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር ከዓለም የጠራውን ሕዝብ ነው።


የእግዚአብሔር መንግሥት፣ መንግሥተ ሰማይ

“የእግዚአብሔር መንግሥት” እና፣ “መንግሥተ ሰማይ” የሚሉት ሁለቱም የሚያመለክቱት በሕዝቡና በፍጥረት ሁሉ ላይ እግዚአብሔር ያለውን አገዛዝ ነው።


የእግዚአብሔር ቃል፣ የያህዌ ቃል፣ የጌታ ቃል፣ ቅዱሳት መጻሕፍት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “የእግዚአብሔር ቃል” የሚባለው እግዚአብሔር ለሰዎች የተናገረው ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ይህም ንግግርና በጽሑፍ የሰፈረ መልእክትን ይጨምራል። ኢየሱስ ራሱ፣ “የእግዚአብሔር ቃል” ተብሏል።


የእግዚአብሔር ቤት፣ የያህዌ ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “የእግዚአብሔር ቤት” እና፣ “የያህዌ ቤት” የተሰኙት ሐረጎች የሚያመለክቱት እግዚአብሔር የሚመለክትበትን ቦታ ነው።


የእግዚአብሔር አምሳል፣ ምስል

“አምሳያ” የሚለው ሌላውን የሚመስል፣ በጸባይም ሆነ በጥንተ ተፈጥሮው ሌላውን የመሰለ ማለት ነው። “የእግዚአብሔር አምሳል” የሚለው ሐረግ እንደ አውዱ ሁኔታ በተለያየ መንገድ ጥቅም ላይ ይውላል።


የእግዚአብሔር ፈቃድ

“የእግዚአብሔር ፈቃድ” የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ፍላጎትና እቅድ ነው።


የክርስቶስ ተቃዋሚ

የክርስቶስ ተቃዋሚ የሚለው አገላለጽ እየሱስ ክርስቶስንና ሥራውን የሚቃወም ሰውን ወይም ትምህርትን ነው የሚያመለክተው በዓለም ውስጥ ብዙ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች አሉ።


የጌታ ቀን፣ ይያህዌ ቀን

“የያህዌ ቀን” የተሰኘው የብሉይ ኪዳን አገላለጽ ከኀጢአታቸው የተነሣ እግዚአብሔር ሕዝቡን የሚቀጣበትን የተለየ ቀን ወይም ቀኖች ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል።


የጌታ እራት

“የጌታ እራት” የሚለውን ቃል ሐዋርያው ጳውሎስ የተጠቀመበት በአይሁድ መሪዎች በተያዘበት ሌሊት ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የበላውን የፋሲካ ምግም ለማመልከት ነበር።


የጽዮን ሴት ልጅ

የጽዮን ሴት ልጅ የእስራኤልን ሕዝብ የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው። ብዙውን ጊዜ ትንቢት ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።


የፍርድ ቀን

“የፍርድ ቀን” እግዚአብሔር በማንኛውም ሰው ላይ የሚፈርድበት ወደፊት የሚመጣ ጊዜ ነው።


ያህዌ

“ያህዌ” የእግዚአብሔር የተፀውዖ ስም ሲሆን፣ በሚቃጠለው ቁጥቋጦ ውስጥ እግዚአብሔር ራሱን ለሙሴ የገለጠው በዚህ ስሙ ነበር።


ያልቦካ እንጀራ

“ያልቦካ እንጀራ” የሚያመለክተው ያለ እርሾ ወይም እንዲቦካ የሚያደርግ ሌላ ነገር ሳይገባበት የተጋገረ እንጀራን ነው። ያልቦካ ዳቦ ኩፍ አይልም፣ ስለዚህ ጠፍጣፋ ነው።


ይቅር ማለት ይቅርታ

አንድን ሰው ይቅር ማለት ከዚህ ቀደም ባደረገው መጥፎ ነገር ቂም አለመያ ማለት ነው። “ይቅርታ” ሌላውን ይቅር የማለት ተግባር ነው።


ደም

“ደም” ጉዳት ወይም ቁስል ሲኖር ከአንድ ሰው ቆዳ የሚወጣ ቀይ ፈሳሽ ነገርን ያመለክታል። ደም ለሰው አካል ሕይወት ሰጪ ምግብን ያመጣል።


ደቀ መዝሙር

“ደቀ መዝሙር” በቃልም ሆነ በሕይወት ምሳሌነት ከመምህሩ ለመማር ሲል ብዙ ጊዜውን ከመምህሩ ጋር የሚያሳልፍ ሰው ነው።


ዲያቆን

ዲያቆን ምግብን ወይም ገንዘብን በመሳሰሉ ተግባራዊ ነገሮች አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉትን በመርዳት የሚያገለግል ሰው ነው።


ድንጋይ፣ በድንጋይ መውገር

ድንጋይ አነስ ያለ ዐለት ነው። በድንጋይ መውገር አንድን ሰው ለመግደል እርሱ ላይ ድንጋዮች መወርወር ማለት ነው


ጃንደረባ

ብዙ ጊዜ፣ “ጃንደረባ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተኮላሸ ወንድን ነው በኋላ ግን ቃሉ አካላዊ ጉድለት ባይኖርባቸውም በአጠቃላይ ማንኛውንም የመንግሥት ባለሥልጣን የሚያመለክት ሆነ።


ገሃነም፣ የእሳት ባሕር

ገሃነም በእርሱ ላይ የሚያምፁትንና በኢየሱስ መሥዋዕትነት በኩል እነርሱን የማድኑን ዕቅድ ችላ የሚሉትን የሚቀጣበት የመጨረሻው የስቃይ ቦታ ነው። “የእሳት ባሕር” ተብሎም ይጠራል።


ጋኔን፣ ክፉ መንፈስ፣ ርኵሳን መናፍስት

እነዚህ ሁሉ የሚያመለክቱት አጋንንትን ሲሆን፣ አጋንንት የእግዚአብሔርን ፈቀድ የሚቀወሙ መንፈሳዊ ፍጥረቶች ናቸው።


ጌታ ያህዌ፣ ያህዌ አምላክ

እንዱ እውነተኛ አምላክን በተመለከተ እነዚህ ቃሎች ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሰዋል።


ጌታ፣ አዛዥ፣ አለቃ

“ጌታ” የሚለው ቃል ሰዎች ላይ ባለቤትነት ወይም ሥልጣን ያለውን ሰው ያመለክታል።


ግርማ

ብዙውን ጊዜ “ግርማ” ከንጉሥ ክብር ጋር በተያያዘ መልኩ ትልቅነትንና ውበትን ነው የሚያመለክተው።


ግብዝ፣ ግብዝነት

“ግብዝ” የሚለው ልቡ ክፉና ጠማማ ሆኖ በሰዎች ፊት ግን መልካም ሰው መስሎ ለመታየት የሚሞክር ሰው ነው። “ግብዝነት” መልካምና እውነተኛ መስሎ ለመታየት አንድ ሰው የሚያደርገው ነው።


ግዛት

ግዛት ሰዎችን፣ እንስሳትንና መሬትን የመቆጣጠር፣ የመግዛት ኃይልና ሥልጣንን ያመለክታል።


ጠቢባን

“ጢቢባን” የተሰኘው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የተለየ ዕውቀትና ችሎታ ያላችው ሰዎችን ለማመልከት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሰዎች በንጉሡ አደባባይ ነበር የሚገኙት።


ጴንጠቆስጤ (በዓለ ሃምሳ)፣ የሳምንቶች በዓል

በዓለ ሃምሳ ከፋሲካ ሃምሳ ቀን በኋላ የሚከበረው የአይሁድ በዓል ግሪክኛ ስም ነው።


ጸሐፍት፣ የአይሁድ ሕግ መምሕራን

ጸሐፍት መንግሥታዊ ወይም ሃይማኖታዊ ሰንዶችን በእጅ ጽሑፍ የማርቀቅ ወይም የመገልበጥ ኅላፊነት የነበረባቸው ባለ ሥልጣኖች ናቸው


ጸያፍ


ጸጋ፣ ባለጸጋ

“ጸጋ” የሚለው ቃል ምንም ሳይለፋና ሳይደክም አንድን ሰው መርዳትን ወይም መባረክን ያመለክታል። “ባለ ጸጋ” ሌሎችን ጸጋ የሚያሳይን ሰው ይመለከታል።


ጻድቅ፣ ጽድቅ

“ጻድቅ” እና፣ “ጽድቅ” የእግዚአብሔር ፍጹም መልካምነት፣ ፍትሕ፣ ታማኝነትና ፍቅር ያመለክታል። እግዚአብሔር ጻድቅ ስለሆነ ኀጢአት ላይ መፍረድ አለበት።


ጽዮን፣ የጽዮን ተራራ

መጀመሪያ ላይ፣ “ጽዮን” ወይም፣ “የጽዮን ተራራ” ተብሎ ይጠራ የነበረው ንጉሥ ዳዊት ከኢያቡሳውያን የያዝሰው ምሽግ ወይም መሸሸጊያ ቦታ ስም ነበር። የኢየሩሳሌም ከተማ በተመሠረተችባቸውና የዳዊት መኖሪያ ከሆነው ኮረብቶች አንዱ ላይ ነበር የሚገኘው።


ፈሪሳዊ

ፈሪሳውያን ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ዘመን በጣም ታዋቂ የእስራኤል ሃይማኖት መሪዎች ነበር። አብዛኞቹ መካከለኛ ኑሮ ያላቸው ሠራተኞች ሲሆኑ፣ ጥቂቶቹም ካህናት ነበሩ።


ፈራጅ፣ ፍርድ

ብዙውን ጊዜ፣ “ፈራጅ” ወይም፣ “ፍርድ” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት ከግብረ ገብ አንጻር አንድ ነገር ትክክል መሆን አለመሆኑን በተመለከተ ውሳኔ መስጠት ነው።


ፈተና

“ፈተና” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ብርታትና ድካም ለይቶ የሚያሳይ አስቸጋሪ ወይም አዳጋች ሁኔታ ያመለክታል።


ፋሲካ (ማለፍ)

ፋሲክ እግዚአብሔር አባቶቻቸው እስራኤላውያንን እንዴት ከግብፅ ባርነት እንዳዳናቸው ለማሰብ አይሁድ በየዓመቱ የሚያከብሩት ሃይማኖታዊ በዓል ስም ነው።


ፍርሃት፣ ፈራ፣ የያህዌ ፍርሃት

“ፍርሃት” እና፣ “ፈራ” የሚሉት በእርሱ ወይም በሌሎች ላይ ጉዳት ይመጣል ብሎ ሲያስብ የሚኖረው ደስ የማይል ስሜት ነው።


ፍቅር

አንድን ሰው መውደድ ለዚያ ሰው ማሰብና መጠንቀቅ እንዲሁም ለእርሱ የሚጠቅመውን ነገር ማድረግ ነው። “ፍቅር” የተለያዩ ትርጕሞች አሉት፤ አንዳንድ ቋንቋዎች በተለያዩ ቃሎች ይገልጹታል። 1. ከእግዚአብሔር የሚመጣው ፍቅር ምንም እንኳ ራስን የሚጠቅም ባይሆንም ሌሎችን መጥቀም ላይ ያተኩራል። ምንም ያድርጉ ምን ይህ ፍቅር ለሌሎች ያስባል፣ ለሌሎች ይጠነቃቃል። እግዚአብሔር ራሱ ፍቅር ነው፤ የእውነተኛ ፍቅር ምንጭም እርሱ ነው።

  1. ሌላው የአዲስ ኪዳን ቃል የወንድማማችነት ፍቅርን ወይም ጓደኛን ወይም ቤተ ሰብን ማፍቀርን የሚመለከተው ነው።
  1. “ፍቅር” የሚለው ቃል በወንድና በሴት መካከል ያለውን መሳሳብና ማደድንም ያመለክታል። 4. “ያዕቆብን ወደድሁ (አፈቀርሁ) ኤሳውን ግን ጠላሁ” በሚለው አነጋገር ውስጥ፣ “ወደድሁ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብ ከእርሱ ጋር የኪዳን ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር መምረጡን ነው። ስለዚህ እዚህ ላይ ይህ ቃል፣ “መረጥሁ” ተብሎ መተርጎም ይችላል ማለት ነው። ምንም እንኳ ኤሳውም በእግዚአብሔር ቢበክም፣ ከእርሱ ጋር ኪዳን የማድረግን መብት አላገኘም። “ጠላሁ” የሚለውም ቃል፣ “አልፈለግሁትም” ወይም፣ “አልመረጥሁም” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።

ፓስተር

“ፓስተር” የሚለው ቃል በቃል፣ “እረኛ” ከሚለው ጋር አንድ ነው። የአማኞች ስብስብ መንፈሳዊ መሪ ለሆነ ሰው የሚሰጥ ስም ነው።