አማርኛ (Amharic): Translation Words

Key Terms

ሁሉን ቻይ

“ሁሉን ቻይ” የሚለው ቃል በቃል “ኃይል ሁሉ የእርሱ የሆነ” ማለት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሉም የሚያመልክተው እግዚኣብሔርን ነው።


ለኪዳኑ ታማኝ፣ ለኪዳኑ እውነተኛ

ይህ አገላለጽ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለሕዝቡ የሰጠውን ተስፋ ለመፈጸም ታማኝ መሆኑን ነው።


ሊቀ ካህን

“ሊቀ ካህን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተቀሩት እስራኤላውያን ካህናት መሪ በመሆን ለአንድ ዓመት እንዲያገለግል የተሾመ የተለየ ካህንን ያመለክታል።


ልብ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልብ የሰውን ሐሳብ፣ ስሜት፣ ፍላጎት ወም ፈቃድ ለማመልከት ብዙውን ጊዜ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።


ልዑል እግዚአብሔር

“ልዑል እግዚአብሔር” ከእግዚአብሔር መጠሪያዎች አንዱ ሲሆን፣ የእርሱን ታላቅነትና ሥልጣን ያመለክታል።


ልጅ፣ የ. . . ልጅ

“ልጅ” የሚለው ቃል ከወላጆቹ ጋር ካለው ግንኙነት አንፃር ትንሽ ልጅን ወይም ሰውን ያመለክታል። የአንድ ሰው ወንድ ወይም ሴት ልጅ ወይም እንደ ልጅ የተቀበለውን ሰው ያመለክታል


ልጅነት/ልጅ አድርጎ መቀበል

“ልጅነት” የተሰኘው ቃል አንድን ሰው በተፈጥሮ ወላጆቹ ያልሆኑ ሰዎች ሕጋዊ ልጅ የማድረግ ሂደት ያመለክታል።


ልጆች፣ ልጅ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ልጅ” የሚለው ቃል ሕፃንን ጨምሮ በአጠቃላይ በዕድሜ ወጣት የሆነውን ያመለክታል። “ልጆች” የብዙ ቊጥር ሲሆን፣ ጥቂት ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።

ይህ አባባል መንፈሳዊ ልጆች የሆኑ ሰዎችንም ያመለክታል። ለምሳሌ፣ “የእግዚአብሔር ልጆች” ሲባል በኢየሱስ በማመን የእግዚአብሔር የሆኑ ሰዎችን ያመለክታል።


ሐሰተኛ አምላክ፣ ባዕድ አምላክ፣ ጣዖት

ሐሰተኛ አምላክ በአንዱ እውነተኛ አምላክ ቦታ ሰዎች የሚያመልኩት ነገር ነው። ወንድ ጣዖት እንዳለ ሁሉ ሴት ጥዖትም አለች።


ሐዋርያ ፣ ሐዋርያነት

ሐዋርያት ስለ እግዚአበሔር ስለ መንግሥቱ ለሰዎች እንዲሰበኩ እየሱስ የላካቸው ሰዎች ነበሩ፤ሐዋርያነት የሚለው ቃል ሐዋርያነት ለመሆን የተመረጡ ሰወች የነበራቸውን ቦታና ስልጣን ያመለክታል።


ሐዴስ፣ ሲኦል

ሞትንና ሰዎች ሲሞቱ የሚሄዱበትን ቦታ ለማመልከትት “ሐዴስ” እና “ሲኦል” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ ውለዋል። የሁለቱም ትርጕም ተመሳሳይ ነው።


ሕይወት፣ ሕያው፣ ሕይወት

እነዚህ ቃሎች ሁሉ የሚመለከቱት በሕይወት መሆንን፣ አለመሞትን ነው። መንፈሳዊ ሕያውነትን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላሉ። “ሥጋዊ ሕይወት” እና፣ “መንፈሳዊ ሕይወት” ሁለቱም ሕይወት ቢሆኑም፣ አንዱ ጊዜያዊ ሌላው ግን ዘላለማዊ ነው።


ሕግ፣ የሙሴ ሕግ፣ የእግዚአብሔር ሕግ፣ የያህዌ ሕግ

እነዚህ ቃሎች ሁሉ እስራኤላውያን እንደታዘዟቸው እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠውን ትእዝዞችና ትምህሮች የሚያመልክቱ ናቸው። “ሕጉ” እና፣ “የእግዚአብሔር ሕግ” የተሰኙት በአጠቃላይ እግዚአብሔር ሕዝቡ እንዲታዘዙ የሚፈልጋቸው ማንኛውንም ነገር ያመለክታሉ።


መለኮት

መለኮት የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር የሆነ ማንኛውንም ነገር ይመለከታል። ይህ ቃል ጥቅም ላይ ከሚውልባቸው መንገዶች ጥቂቶቹ “መለኮታዊ ሥልጣን”፣ “መለኮታዊ ፍርድ”፣ “መለኮታዊ ባሕርይ”፣ “መለኮታዊ ኃይል” እና፣ “መለኮታዊ ክብር የተሰኙት ናቸው።


መለየት

መለየት አንድን ነገር ወይም ሰው እግዚአብሔርን እንዲያገለግል መመደብ ማለት ነው። በዚህ መልኩ የተለየ ሰው ወይም እቃ ለእግዚአብሔር እንደ ተቀደሰና እንደ ተለየ ይቆጠራል።


መለየት

“መለየት” የሚለው ቃል አንድ ዓላማን ለመፈጸም ከአንድ ነገር ተለይቶ መውጣትን ያመለክታል


መልአክ፤የመላእክት አለቃ

መልአክ በእግዚአብሔር የተፈጠረ ሃያል መንፈዊ ፍጡር ነው፤መላአኮች የተፈጥጠሩት እርሱ የሚነግራቸውን በማድረግ እግዚአብሔርን እንድያገለግሉ ነው፤የመላክት አለቃ ሌሎች መላአኮችን ሁሉ የሚያዝዝ ወይም የ መልአክን ያመለክታል።

ለሰወች ሲናገር በመልአክ ተመስሎ የመጣ ራሱ እግዚአብሔር ሊያመለክት ይችላል፤አንድ መልአክ ያህዌ ራሱ የተናገረ ያህል’’እኔ’’እያለ የተናገረው ለምን እንደ ነበር ከእነዚህ ትርጉሞች አንዱ በቂ ገለጻ ይሰጠን ይሆናል።


መልካም፣ መልካምነት

“መልካም” የሚለው ቃል እንደ ምንባቡ ዐውድ ሁኔታ የተለያዩ ትርጕሞች ይኖሩታል። እነዚህን የተለያዩ ቃሎች ለመተርጎም የተለያዩ ቋንቋዎች የተለያዩ ትርጕሞች ያቀርባሉ።


መመለስ፣ መታደስ

“መመለስ” እና፣ “መታደስ” አንድን ነገር ቀድሞ ወደ ነበረበት ቦታ፣ ወደ ተሻለ ሁኔታ መመለስ ማለት ነው።


መመስከር፣ ምስክርነት

መመስከር አንድ ነገር እውነት መሆኑን መቀበል ወይም መናገር ማለት ነው። “ምስክርነት” አንድ ነገር እውነት መሆኑን በቃል ወይም በጽሑፍ በዚያም መስማማት ማለት ነው።


መመካት፣ ትምክህተኛ

“መመካት” በሰዎች ወይም በነገሮች በመመካት በትዕቢት መናገር ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ስለ አራስ በእብሪት መናገር ማለት ነው።


መማልጃ፣ ምልጃ

“መማለጃ” እና፣ “ምልጃ” በሌሎች ስፍራ ሆኖ ስለ እነርሱ መለመን ወይም መጸለይን ያመለክታል። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ስለሌሎች ከመጸለይ ጋር ነው።


መሠዊያ

መሠዊያ ለእግዚአብሔር መባ(ስጦታ)እንዲሆን እስራኤላውያን እንስሳትና የእህል ዓይነቶችን የሚያቃጥልበት ከፍ ብሎ የሚሠራ ነገር ነው።


መርሳት፣ ተረሳ

“መርሳት” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር ጨርሶ መተው ማለት ነው። “የተረሳ” በሌላው ወገን ጨርሶ የተተወ ግምት ውስጥ የማይገባ ሰው ነው።


መርገም፣ የተረገመ

“መርገም” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ላይ መጥፎ ነገር እንዲደርስበት ማድረግ ነው።


መስቀል

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን መስቀል አንድ ቀጥ ብሎ የወጣ እንጨት ሲሆን ጫፉ አካባቢ አንድ ሌላ ግንድ ይጋደምበት ነበር።


መስቀል (ሰውን)

“መስቀል” ማለት አንድን ሰው መስቀል ላይ ማሰርና በታላቅ ሕመምና ስቃይ እስኪሞት ድረስ እዚያው መተው ማለት ነው።


መሾም፤ይሾም

መሾም እና የተሾመ የተሰኙት ቃላት አንድ የተለየ ተግባርን ወይም ተልኮን እንዲሁም አንድን ሰው መምረጥን ያመለክታል።

እንዲቀበሉ ተመርጠዋል ማለት ነው።


መቀደ፣ ቅድስና

መቀደስ፣ ቅዱስ ይሆን ዘንድ አንድን ነገር መለየት ማለት ነው። ቅድስና ቅዱስ የመሆን ሂደት ነው


መቃባት፤የተቀባ

“መቀባት” የሚለው ቃል ሰውን ወይም አንድን ነገር በ ማሰብ ወይም ላይ ላይ ዘይት ማፍሰስ ማለት ነው፤አንዳንዴ ዘይቱ ከተለዩ ቅመሞች ጋር ስለሚቀላቀል በጣም ጣፋጭ መዕዛ ያለው ሽቶ ይሆናል፤ቃሉ ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ መንፈስ ቅዱስ ሰው መምረጡንና ሃይል ማስታጠቁን ያመለክታል።


መባረክ፣ ተባረክ፣ በረከት

አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር፣ “መባረክ” በዚያ ሰው ወይም ነገር ላይ መልካምና ጠቃሚ ነገር እንዲሆን ማድረግ ማለት ነው።


መተላለፍ

“መተላለፍ” ትእዛዝን፣ ደንብን ወይም ሕግን ማፍረስ ማለት ነው።


መታመን፣ ታማኝ፣ ታማኝነት

“መታመን” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር እውነት ወይም እምነት ሊጣልበት የሚገባ መሆኑን ያመለክታል። “ታማኝ” ሰው ትክክልና እውነት የሆነ ነገር እንደሚያደርግና እንደሚናገር እምነት ይጣልበታል።


መቶ አለቃ

መቶ አለቃ ከእርሱ ሥር 100 ወታደሮች የነበሩት የሮም ሰራዊት ባለ ሥልጣን ነበር።


መና

መና ከግብፅ ከወቱ በኋላ እስራኤል በምድረ በዳ ይንከራተቱ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሰጣቸው እንጀራ የመሰለ ስስ ምግብ ነበር።


መንፈስ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ፣ የጌታ መንፈስ

እነዚህ ሦስት ቃሎች የሚያመለክቱት እርሱ ራሱ እግዚአብሔር የሆነው መንፈስ ቅዱስን ነው። እውነተኛው አንድ አምላክ አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ የሚባሉ አካላት አሉት።


መንፈስ፥ መንፈሳዊ

“መንፈስ” የሚለው ቃል የሰዎችን ቁሳዊ ያልሆነና የማይታይ ክፍል ያመለክታል። ሰው ሲሞት መንፈሱ ከአካሉ ይለያያል


መኮነን፣ ኵነኔ

“መኮነን” እና “ኵነኔ” አንዳች በደል ከመፈጸሙ የተነሣ ሌላው ላይ መፍረድን ያመለክታል።


መወሰን፣ የተወሰነ

“መወሰን” እና፣ “የተወሰነ” የተሰኙት ቃሎች አንድ ነገር ከመሆኑ በፊት እንደዚያ እንዲሆን መቁረጥን ወይም ማቀድን ያመለክታሉ።

መንጠቅ፣ ንጥቂያ “መንጠቅ” የሚያመለክተው አንድን ነገር፣ ብዙውን ጊዜ ደግሞ ለምግብ የሚሆን እንስሳን ማደንን ነው።


መዋጀት

“መዋጀት” የሚለው ቃል በሌሎች ተወስዶ የነበረ ነገርን በመግዛት የራስ ማድረግ ማለት ነው።


መውረስ፣ ውርስ፣ መብት፣ ወራሽ

“መውረስ” እና፣ “ውርስ” ከእነርሱ ጋር ካለ የተለየ መቀራረብ የተነሣ ከወላጆቹ ወይም ከሌሎች ጠቃሚ ነገር መቀበል ማለት ነው። ያንን ውርስ የሚቀበል ወራሽ ይባላል።


መዓት፣ ቁጣ

መዓት ለረጅም ጊዜ የሚቆይ በጣም ከባድ ቁጣ ነው። ብዙውን ጊዜ ኀጢአት ላይ የሚመጣውን የእግዚአብሔር ጻድቅ ፍርድና በእርሱ ላይ የሚያምፁ ሰዎችን ቅጣት ያመለክታል።


መዝሙር

ቅዱስ ዝማሬ፣ ብዙ ጊዜ በሙዚቃ የታጀበ ግጥም ወይም ቅኔ ማለት ነው። ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለው መጽሐፈ መዝሙር በእስራኤላውያን የተጻፉ የመዝሙሮች ስብስብ ይዟል።


መገረዝ፣ ግዝረት

“መግረዝ” ከወንድ ወይም ወንድ ከሆነ ትንሽ ልጅ ብልት ትርፍ የሆነውን ቆዳ መቊረጥ ማለት ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የግርዘት ሥርዓት ሊኖርም ይችላል።


መገናኛ ድንኳን

መገናኛ ድንኳን እስራኤላውያን 40 ዓመት በምድረ በዳ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሚያመልኩበት ድንኳን መሰል ነገር ነበር


መግለጽ፣ መገለጽ (ራእይ)

“መግለጽ” አንድ ነገር እንዲታወቅ ማድረግ ማለት ነው “መገለጽ” እንዲታወቅ የተደረገ ነገር ነው።


መጣስ፣ መዳፈር

“መጣስ” ሕግ ማፍረስ ወይም የሌሎችን መብት መንካት ማለት ነው።


መጥራት፣ ጥሪ፣ ተጠራ፣ መጣራት

“መጥራት” እና “መጣራት” የተሰኙ ቃሎች ቅርብ ላልነበረ ሰው ጮኽ ብሎ አንዳች ነገር መናገር ማለት ነው። ሌሎች ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሏቸው።


መጥፋት፣ ጥፋት፣ የሚጠፋ

“መጥፋት” የሚለው ቃል አብዛኛውን ጊዜ በአንድ ዓይነት ጥቃት ወይም አደጋ የተነሣ መሞት ወይም መደምሰስ ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለይ ለዘላለም በገሃነም መቀጣት የሚል ትርጕም አለው።


መጸለይ፣ ጸሎት

መጸለይ ለእግዚአብሔር መናገር ነው።


መፈተን፣ ፈተና

መፈተን አንድ ሰው ተገቢ ያልሆነ ነገር እንዲያደርግ መሞከር ማለት ነው።


መፈጸም

“መፈጸም” አንዳች የሚጠበቅ ነገርን ፈጽሞ ወይም አከናውኖ መገኘት ማለት ነው።


ማመን፥ አመነ፥ እምነት

“ማመን” እና “አመነ” በጣም የተያያዙ ቢሆንም በመጠኑ የሚለያይ ትርጉም አላቸው


ማምለክ፣ መስገድ

“ማምለክ፣ መስገድ” እግዚአብሔርን ማክበር፣ ማመስገንና ለእርሱ መታዘዝ ማለት ነው።


ማሰር፣ ማሰሪያ፣ አሰረ

“ማሰር” አንድን ነገር ጥብቅ አድርጎ ማሰር ወይም እንዳይበታተን አድርጎ መቋጠር ማለት ነው። አንድ ነገር የሚያስር ወይም እርስ በርስ የሚያያይዝ፣ “ማሰሪያ” ይባላል።


ማስተሰሪያ

“ማስተሰረያ” የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ፍትሕ ለማርካት ወይም ለመፈጸምና ቁጣውን ለማስታገሥ የሚቀርብ መሥዋዕት ነው።


ማስታረቅ፣ ዕርቅ

“ማስታረቅ” እና፣ “ዕርቅ” ቀድሞ እርስ በርስ ይጠላሉ በነበሩ ሰዎች መካከል፣ “ሰላም ማድረግ” ማለት ነው።


ማበረታታት

“ማበረታታት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰዎች ትክክልና እውነት የሆነውን ነገር እንዲያደርጉ ማደፋፈርን ነው።


ማዘዝ፣ ትእዛዝ

ማዘዝ ማለት አንዳች ነገርን እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ለሰዎች መናገር ማለት ነው። ትእዛዝ የሚባለው እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ለሰዎች የተሰጠው መመሪያ ነው።


ማዳን፣ ደኅንነት

“ማዳን” አንድን ሰው ከአንዳች መጥፎ ወይም ጎጂ ነገር መጠበቅ ማለት ነው “ደኅንነት” ከጉዳት ወይም ከአደጋ የተጠበቀ ማለት ነው


ማጥመቅ፥ ጥምቀት

አዲስ ኪዳን ውስጥ “ማጥመቅ” እና፥ “ጥምቀት” የተሰኙ ቃሎች ብዙውን ጊዜ ከኃጢአት መንጻቱንና ከክርስቶስ ጋር መተባበሩን ለማሳየት ክርስቲያኑን ውሃ ውስጥ የመንከር ስርዓትን ያመለክታል


ምልክት፥ ማረጋገጫ፣ ማሳሰቢያ

ምልክት የተለየ ትርጉም ያለው መልእክት የሚያስተላልፍ ዕቃ፣ ሁኔታ ወይም ድርጊት ሊሆን ይችላል


ምሕረት፣ መሐሪ

“ምሕረት” እና፣ “መሐሪ” የተሰኙት ቃሎች ችግር ውስጥ በተለይም እጅግ በተዋረደ ዝቅረኛ ደረጃ ያሉ ሰዎችን መርዳትን ያመለክታሉ።


ምሳሌ

ምሳሌ ግብረ ገባዊ ወይም ሃይማኖታዊ ትምህርት ለማስተማር የሚቀርብ አጭር ታሪክ ነው።


ምስክር፣ መመስከር

“ምስክር” እና፣ “መመስከር” አንድን ነገር በተመለከተ የሚያውቁትን እውነት በግልጽና በሰው ሁሉ ፊት መናገር ማለት ነው።


ምኩራብ

ምኩራብ አይሁድ እግዚአብሔርን ለማምለክ የሚሰበሰቡበት ቦታ ነው። ከጥንት ዘመን ጀምሮ ምኩራቦች ለጸሎት፣ ቅዱሳት መጽሐፍትን ለማንበብና ለመማር አገልግሎት ላይ ውለው ነበር


ሞኝ፣ ሞኝነት፣ ከንቱነት

“ሞኝ” የሚባለው ብዙውን ጊዜ የተሳሳተ ምርጫ የሚያደርግ በተለይም አለመታዘዝን የሚመርጥ ሰው ነው። “ሞኝነት” ማስተዋል የሌለው ሰው ወይም ፀባይ የሚገለጥበት መንገድ ነው።


ሞገስ፣ ሞገስ ያለው፣ አድልዎ (ከሌሎች የተለየ ሞገስ የሚደረግለት)

ሞገስ እርሱን በተመለከተ ጥሩ አመለካከት ያለንን ሰው ለመጥቀም የሚደረግ ነገርን ያመለክታለ። “ሞገስ ያለው” ነገር ቀና ተቀባይነት ያለው ወይም ጠቃሚ ነው።


ሥልጣን

“ሥልጣን” የተሰኘው ቃል አንድ ሰው ሌላው ሰው ላይ ያለውን ተፅዕኖ የማሳደር ወይም የመቆጣጠር ኅይልን ያመለክታል


ሥራዎች፣ ተግባሮች፣ ሥራ፣ ተግባር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሥራዎች”፣ “ተግባሮች” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ የዋሉት እግዚአብሔር ወይም ሰዎች ያደረጉትን በአጠቃላይ ለማሳየት ነው።


ሥርዓት፥ ራስን መግዛት ወይም ራስን በሥርዓት መምራት

“ሥርዓት” ለተወሰኑ ግብረ ገባዊ መመሪያዎች እንዲታዘዙ ሰዎችን መሠልጠንን ነው የሚያመለክተው።


ሥጋ

መጽሐፍ ቅዱስ ሥጋ ሲል ቃል በቃል የሰውን ወይም የእንስሳን ለስላሳውን የአካል ክፍል ያመለክታል።


ረቢ፣ ረቡኒ

ቃል በቃል፣ “ረቢ” – “ጌታዬ” ወይም፣ “መምህሬ” ማለት ነው።


ርኅራኄ፣ ርኅሩኅ

“ርኅራኄ” ለሰዎች ማሰብ፣ አተለይም መከራ ለደረሰባቸው ሰዎች እነርሱ ቦታ ሆኖ ስሜታቸውን መጋራትን ያመለክታል። “ርኅሩኅ” ሰው ለሌሎች ሰዎች ያስባል እነርሱንም ይረዳል።


ርኩሰት

“ርኩሰት” የሚለው ቃል ትርጉም፣ “ኀጢአት” ከሚለው ጋር በጣም ተመሳሳይ ቢሆንም በተለይ፣ ሆን ተብሎ የሚፈጸም በደልን ወይም ታላቅ ዐመፃን ሊያመለክት ይችላል።


ሰማይ፣ ሰማያት፣ ሰማያዊ

“ሰማይ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል የእግዚአብሔር መኖሪያን ያመለክታል።


ሰንበት

ሰንበት የሳምንቱ ሰባተኛ ቀን ነው፤ ይህ ቀን ምንም ሥራ የማይሠራበት የዕረፍት ቀን እንዲሆን እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዝዞ ነበር።


ሰይጣን፣ ዲያብሎስ፣ ክፉው

ዲያብሎስ እግዚአብሔር የፈጠረው መንፈሳዊ አካል ነበር፤ በእግዚአብሔር መማመፁ የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ። ዲያብሎስ፣ “ሰይጣን” እና፣ “ክፉው” ተብሎ ይጠራል


ሰዱቃውያን

ሰዱቃውያን ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያላቸው የአይሁድ ካህናት ነበሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ባገለገለ ዘመን የነበረውን የሮም አገዛዝ ይደግፉ ነበር። በሙታን ትንሣኤ አያምኑም


ስም

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስም በተለያዩ ምሳሌያዊ አነጋገርና ጥቅም ላይ ውሏል።


ስእለት

ስእለት አንድ ሰው ለእግዚአብሔር የሚገባው ቃል ነው። እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ሁኔታ ለማክበር ወይም ም ያህል ለእርሱ የተሰጠ መሆኑን ለማሳየት አንድ ሰው አንድ ነገር እንደሚያደርግ ለእግዚአብሔር ቃል ይገባል።


ስድብ፣ ተሰደበ

መጽሐፍ ቁስ ውስጥ፣ “ስድብ” እግዚአብሔርንና ሰውን በጣም በሚያንቋሽሽ መንገድ መናገርግን ያመለክታል። አንድን ሰው፣ “መስደብ” ሰዎች ሐሰት የሆነ መጥፎ ነገር እንዲያስቡ በዚያ ሰው ላይ ክፉ ነገር መናገር ማለት ነው።


ስጦታ

“ስጦታ” የሚለው ለሌላው ወገን የተሰጠ ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ስጦታ የሚሰጠው በምላሹ ምንም ነገር ባለ መጠበቅ ነው።


ቀናተኛ፣ ቅናት

“ቀናተኛ” እና “ቅናት” የተሰኙት ቃሎች አንድ ሰው የግል የማድረግ ጽኑ ፍላጎት ያመለክታሉ። አንድን ነገር ወይም ንብረት አጥብቆ የመያዝ ፍላጎትንም ያመለክታል።


ቀኝ እጅ

“ቀኝ እጅ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር፣ በአንድ መሪ፣ ወይም ሥልጣን ባለው ሰው ቀኝ ያለውን የክብር ቦታ ያመለክታል።


ቅንዓት፣ ቀናተኛ (ቀናዒ)

“ቅንዓት” እና፣ “ቀናተኛ” የአንድ ሰው ወይም ሐሰብ ጠንካራ ደጋፊ መሆንን ያመለክታል።


ቅዱሳን

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ቅዱሳን” – “ቅዱስ የሆኑ ሰዎች” ማለት ሲሆን፣ በኢየሱስ ያመኑ ወገኖችን የመለክታል


ቅዱስ

“ቅዱሱ” የሚለው መጠሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሌም የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው።


ቅዱስ ቦታ

“ቅዱስ ቦታ” ቃል በቃል እግዚአብሔር የሚቀደስበትና የሚመለክበት የተለይ ቦታ ማለት ነው። ከለላና ደኅንነት የሚገኝበትንም ቦታ ሊያመለክት ይችላል


ቅዱስ፣ ቅድስና

“ቅዱስ” እና “ቅድስና” ኀጥእ ከሆነውና ፍጽምና ከሌለው ማንኛውም ነገር ፍጹም ልዩ የሚያደርገውን የእግዚአብሔርን ባሕርይ ያመለክታል።


ቅድስት፣ ቅድስተ ቅዱሳን

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ቅድስት” እና፣ “ቅድስተ ቅዱሳን” የተሰኙ ቃሎች መገናኛው ድንኳን ወይም ቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩ ሁለት ክፍሎች ያመለክታሉ። አንዳንዴ፣ “ቅድስት” ወይም፣ “ቅዱስ ቦታ” የሚለው በጠቅላላው ለእግዚአብሔር የለለየ ማንኛውንም ቦታ ያመለክታል።


በመንፈስ መሞላት

“በመንፈስ ቅዱስ መሞላት” የሚለው አገላለጽ የእግዚአብሔር ፈቃድ ማድረግ እንዲችል መንፈስ ቅዱስ ለሰው የሚሰጠውን ኅይል የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው።


በግ፣ የእግዚአብሔር በግ

በግ ጥቅጥቅ ያሉ ለሱፍ መሥሪያ የሚያገለግሉ ጠጉሮች ያሉት ባለ አራት እግር እንስሳ ሲሆን፣ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይቀርባል። እርሱ ለሕዝቡ ኃጢአት መሥዋዕት ሆኖ በመሞቱ ኢየሱስ፣ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሏል።


ቤተ መቅደስ

ቤተ መቅደስ እስራኤል ለጸሎትና ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ የሚሰበሰቡበት ዙሪያውን በተከበበ አደባባይ ውስጥ ያለ ሕንፃ ነው። ቤተ መቅደስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ባለው የሞሪያ ተራራ ነበር።


ቤተ ክርስቲያን

በአዲስ ኪዳን መሠረት ቤተ ክርስቲያን የሚባለው ለመጸለይና የእግዚአብሔር ቃል ሲሰበክ ለመስማት ዘወትር የሚሰበሰቡ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ሰዎች ስብስብ ነው። “ቤተ ክርስቲያን” ብዙውን ጊዜ፣ ክርስቲያኖችን ሁሉ ያመለክታል።


ቤዛ

“ቤዛ” የሚለው ቃል በምርኮ የተያዘ ሰውን ለማስለቀቅ እንዲከፈል የተጠየቀ ገንዘብ ወይም ሌላ ነገር ያመለክታል።


ቤዛነት፥ቤዛ

“ቤዛ” እና “ቤዛነት” ለሰው ልጆች ኃጢአት የሚከፈልና የእርሱን በኃጢአት መቆጣት የሚያበርድ መሥዋዕት እግዚአብሔር ያዘጋጀበትን ሁኔታ ያመለክታል


ተስፋ

ተስፋ አንድ መልካም ነገር ይሆናል ብሎ መጠበቅና የተሻለ ነገር እንደሚመጣ መጠባበቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “ተስፋ” እግዚአብሔር ለሕዝቡ ቃል የገባውን እንደሚቀበሉ እርግጠኛ ሆ መጠበቅን ነው የሚያመለክተው። ይሁን እንጂ፣ አንድን ነገር እርግጠኛ ሆኖ ወይም በልበ ሙሉነት መጠበቅን የሚያመለክት በመሆኑ ULB በተሰኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም አብዛኛውን ጊዜ፣ “እምነት” ወይም፣ “ድፍረት” ተብሎ ተተርጕሞአል።


ተስፋ ቃል

ተስፋ ቃል አንድን ነገር ለመስጠት ወይም ለማድረግ ቃል መግባት ማለት ነው። አንድ ሰው አንድ ነገር ለማድረግ ተስፋ ከሰጠ ያንን ለመፈጸም ይተጋል ማለት ነው።


ተአምር፣ ድንቅ፣ ምልክት

“ተአምር”እግዚአብሔር ራሱ ካላደረገው በቀር ጨርሶ ሊሆን የማይችል አስደናቂ ነገር ነው።


ታማኝ፣ ታማኝነት

ለእግዚአብሔር፣ “ታማኝ” መሆን ዘወትር በእርሱ ትምህርት መኖር ማለት ነው። ለእርሱ በመታዘዝ እውነተኛነትን ማሳየት ማለት ነው ታማኝ ሆኖ የመገኘት ሁኔታ፣ “ታማኝነት” ይባላል።


ታቦት


ትሑት፣ ትሕትና

ትሑት ሰው ከሌሎች ሁሉ የበለጠ እንደ ሆነ አያስብም። ትዕቢተኛ ወይም እብሪተኛ አይደለም።


ትሩፍ፣ ትሩፋን

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ትሩፋን” ማለት፣ በጣም ብዙ ከሆነው ክፍል ወይም ወገን “የተረፉ” ወይም፣ “የቀሩ” ሰዎች ወይም ነገሮች ማለት ነው።


ትንሣኤ

“ትንሣኤ” ከሞት በኋላ ተመልሶ ወደ ሕይወት መምጣት ነው።


ትክክል፣ ፍትሕ፣ በፍትሕ

እነዚህ ቃሎች የሚያመለክቱት በእግዝአብሔር ቃል መሠረት ሰዎችን በአግባቡ መያዝን ወይም ማስተናገድን ነው። ትክክል የሆነውን የእግዚአብሔር መስፈርት የሚያንጸባርቁ የሰው ልጆች ሕጎችም ፍትሕ ይባላሉ።


ኀይል፣ ኀይላት

“ኀይል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብዛኛውን ጊዜ በታላቅ ብርታት ነገሮችን ማድረግን ወይም ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ችሎታን ነው። “ኀይላት” የሚያመለክተው ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ታላቅ ችሎታ ያላቸው ሰዎችን ወይም መናፍስትን ነው።


ኅሊና

ኅሊና አንድ ሰው ኃጢአት እያደረገ መሆኑን እግዚአብሔር ለእርሱ የሚያሳውቅበት የሰውየው አስተሳሰብ አንድ ክፍል ነው።


ኅብረት

አጠቃላይ በሆነ ደረጃ፣ “ኅብረት” ተመሳሳይ ፍላጎትና ልምምድ ያላቸው የአንድ ማኅበር አባሎች መካከል የሚደረግ የወዳጅነት ግንኙነትን ያመለክታል።


ኅጢአት፣ ኅጥእ፣ ኅጢአተኛ፣ ኅጢአት ማድረግ

“ኅጢአት” የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር የሚደረግ ተግባርን፣ ሐሳብንና ቃልን ያመለክታል። እግዚአብሔር ያዘዘውን አለማድረግም ኅጢአት ነው


ነቀፋ የሌለበት

“ነቀፋ የሌለበት” የሚለው ቃል በቃል፣ “ነውር፣ እንከን” የሌለበት ማለት ነው። በፍጹም ልቡ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝ ሰውን የሚያመለክት ቢሆንም፣ ያ ሰው ምንም ኃጢአት የለበትም ማለት አይደለም።


ነቢይ፣ ትንቢት፣ ትንቢት ተናገረ፣ ተመልካች፣ ነቢዪት

“ነቢይ” የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው። ይህን የምታደርግ ሴት ነቢዪት ትባላለች።


ነጻ

“ነጻ” የሚለው ቃል ወንጀል ከመፈጸም ወይም ከሌሎች በደሎች ነጻ የሆነ ማለት ነው። በጠቅላላው በማንኛውም ክፉ ነገር አለመሳተፉን ያመለክታል።


ነፍስ

ነፍስ የሰው ውስጣዊ፣ የማይታይና ዘላለማዊ ክፍል ነው። የሰውን ቁሳዊ ያልሆነ ነገር ሁሉ ይጨምራል


ናዝራዊ፣ የናዝራዊ ስእለት

ናዝራዊ የሚባለው ናዝርውያን የሚሳሉትን ስእለት የተሳለ ሰው ነው።


ንስሐ መግባት፣ ንስሐ

“ንስሐ መግባት” እና፣ “ንስሐ” ከኀጢአት ወደ እግዚአብሔር መመለስን ያመለክታል።


ንጹሕ፣ ማንጻት

“ንጹሕ” መሆን እንከን የሌለው ወይም እዚይ ኣመገኘት ያልነበረበት የተቀላቀለ ነገር የሌለው ማለት ነው። አንድን ነገር ማንጻት ማለት ንጹሕ ማድረግና የሚያቆሽሸውንና የሚበክለውን ማንኛውንም ነገር ማስወገድ ማለት ነው።


ንጽሕ፣ ማንጻት

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ንጹሕ” ምንም ቆሻሻ ወይም እድፍ የሌለበት ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ቅዱስ” እና “ከኃጢአት የነጻ” የሚሉትን ለማመልከት በምሳሌያዊ አነጋገር ጥቅም ላይ ይውላል።


አሕዛብ

አሕዛብ የያዕቆብ ወይም የአሥራ ሁለቱ የእርሱ ልጆች ዘር ያልሆነ ሰው ነው። ስለሆነም አሕዛብ አይሁድ አይድለም ማለት ነው።


አሜን፣በእውነት ይሁን

“አሜን” የሚለውለንድ ሰው የተናገረውን አጽንዖት ለመስጠት ወይም ትኩረት እንዲሰጠው ለማድረግ ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። ኢያሱስ ይህን ቃል ሲናገር ብዙውን ጊዜ አሜን ይሁን እንደ ማለት ነው።


አምላካዊ፣ አምላካዊነት

“አምላካዊ” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን በሚያስከብርና የእግዚአብሔርን ማንነት በሚያሳይ መንገድ የሚኖር ሰውን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል። የእግዚአብሔርን ፈቃድ በማድረግ እርሱን የማያከብር ሰው ባሕርይ አምላካዊነት ይባላል።


አሥራ ሁለቱ፣ አሥራ አንዱ

“አሥራ ሁለቱ” የቅርብ ደቀ መዛሙርቱ ወይም ሐዋርያቱ እንደሆኑ ኢየሱስ የመረጣቸው አሥራ ሁለት ሰዎች ናቸው። ይሁዳ ራሱን ከገደለ በኋላ፣ “አሥራ አንዱ ቀሩ።


አካል

“አካል” ቃል በቃል የሰው ወይም የእንስሳ ሥጋ ማለት ነው። ይህ ቃል አንድን ነገር ወይም በአንድ ቡድን ውስጥ ያሉ ግለ ሰቦችን ለማመልከትም ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።


አይሁድ፣ አይሁዳዊ

አይሁድ በልጅ ልጁ በያዕቆብ በኩል የአብርሃም ዘር የሆኑ ሕዝብ ናቸው።


አዳኝ

“አዳኝ” የሚለው ቃል ሌሎችን የሚያድን ወይም የሚታደግ ሰውን ያመለክታል። ለሌሎች ብርታትን ወይም የሚያስፈልጋቸውን የሚሰጥ ሰውንም ያመለክታል


አገልጋይ፣ አገልግሎት

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “አገልጋይ” እና፣ “አገልግሎት” የተሰኙት ቃሎች እግዚአብሔርን በተመለከተ ሰዎችን በማስተማር፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታቸውም በማሰብ ሌሎችን መርዳት ማለት ነው። በዚህ መልኩ ሰዎችን የሚረዳ ሰው አገልጋይ ይባላል።


አጋንንት ያደሩበት

አጋንንት ያደሩበት ሰው የሚያደርገውንና የሚያስበውን የሚቆጣጠሩ አጋንንት ወይም ክፉ መናፍሳት ውስጥ ይኖራሉ።


ኢየሱስ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ክርስቶስ ኢየሱስ

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ኢየሱስ ማለት፣ “ያህዌ ያድናል” ማለት ነው። “ክርስቶስ” “የተቀባው” የሚል ትርጉም ያለው ቃል ሲሆን፣ መሲህ የሚለው ሌላ ቃል ነው።


ኤፉድ

ኤፉድ እስራኤላውያን ካህናት ይለብሱት የነበረ መጎናጸፊያ ዐይነት ጨርቅ ነው። ትከሻ ላይ የሚገናኙ የፊትና የኋላ የሚባሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት፤ ከዚያም በጨርቅ መታጠቂያ ወገብ ላይ ይታሰር ነበር።


እምነት

በአጠቃላይ ደረጃ “እምነት” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር፣ በሰው ወይም፣ በነገሮች መተማመንን፣ መደገፍን፣ ወይም፣ መመካትን ነው።


እምነት የለሽ እምነት ወይም የሚተማመንበት የሌለው ማለት ነው።

እምነት የለሽ፣ እምነት የለሽነት


እስራኤል፣ እስራኤላውያን፣ የእስራኤል ሕዝብ

እስራኤል እግዚአብሔር ለያዕቆብ የሰጠው ስም ነው። እስራኤል፣ “ከእግዚአብሔር ጋር ታገለ” ማለት ነው።


እንደ ገና መወለድ፣ ከእግዚአብሔር መወለድ፣ አዲስ ልደት

ኢየሱስ፣ “እንደ ገና መወለድ” በሚለው ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው እግዚአብሔር አንድን መንፈሳዊ ሙት የሆነ ሰው መንፈሳዊ ሕያው እንዲሆን እንደሚለውጠው ለማመልከት ነበር። “ከእግዚአብሔር መወለድ” ወይም፣ “ከመንፈስ መወለድ” የተሰኙትም ቃሎች አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት የተሰጠውን ሰው ያመለክታሉ።


እውነት፣ እውነተኛ

“እውነት” የሚለው ቃል ይተረጋገጠ ፅንሰ ሐሳብን፣ በትክክል የተፈጸመ ሁኔታንና በእርግጥ የተነገረ ቃልን ያመለክታል።


እግዚአብሔር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር አጽናፈ ዓለሙን ከምንም ያስገኘው ዘላለማዊ ፈጣሪን ያመለክታል። እግዚአብሔር አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በሚባሉ ሦስት አካሎች ተገልጧል። የእግዚአብሔር ተፀውዖ (መጠሪያ) ስም፣ “ያህዌ” ነው።


እግዚአብሔር አብ፣ ሰማያዊ አባት፣ አባት

“እግዚአብሔር አብ” እና፣ “ሰማያዊ አባት” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት አንዱን እውነተኛ አምላክ ያህዌን ነው። ይህ ቃል በተለይም ኢየሱስ ሲጠቀምበት “አባት” ተብሎም ተጠርቷል።


ከርቤ

ከርቤ ከተለየ ዐይነት ዛፍ ሙጫ የሚዘጋጅ ቅመም ነው።


ከፍ ማድረግ፣ ከፍታ

ከፍ ማድረግ በከፍተኛ ደረጃ ማመስገንና ማክበር ማለት ነው። ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ማድረስንም ያመለክታል።


ኪዳን

ኪዳን አንዱ ወይም ሁለቱም የሚፈጽሙት በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ መደበኛ አሳሪ ስምምነት ነው።


ካህን፣ ክህነት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካህን ሕዝብን በመወከል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚያቀርብ ሰው ነው። “ክህነት” እንዲህ ላለው ሰው ተግባር የተሰጠ ስም ወይም ቦታ ነው።


ክርስቲያን

ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከሄደ ጥቂት ጊዜ በኋላ ስዎች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም አወጡ፤ ክርስቲያን የክርቶስ ተከታይ ማለት ነው።


ክርስቶስ፣ መሲሕ

“መሲሕ” ወይም፣ “ክርስቶስ” የሚለው ቃል፣ “የተቀባ” ማለት ሲሆን፣ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስን ነው የሚያመለክተው።


ክብር፣ ማክበር

“ክብር” የሚለው ቃል ለእግዚአብሔር ወይም ለሰው ልጅ የሚሰጥ የላቀ ቦታ፣ ግምት ወይም አክብሮታዊ ፍርሃት ነው።


ክብር፣ የከበረ

በአጠቃላይ “ክብር” ማለት ምስጋና፣ ውበትና የላቀ ታላቅነት ማለት ነው። ክብር ያለው ነገር “የከበረ” ይባላል።


ክፉ፣ ዐመጽ(ዐመጸኛ)፣ ዐመጻ

“ክፉ” እና “ዐመጸኛ” የተሰኙት ቃሎች ሁለቱም የእግዚአብሔርን ቅዱስ ባሕርይና ፈቃድ የሚቃወም ማንኛውንም ነገር ያመለክታሉ።


ወንድም

ብዙውን ጊዜ ወንድም የሚባለው ቢያንስ ከወላጆች ከአንዱ የተወለደ ወንድ ልጅ ነው።


ወንጌላዊ

“ወንጌላዊ” የኢየሱስ ክርስቶስን የምሥራች(ወንጌል) ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው።


ወዮ

“ወዮ” ከፍ ያለ ጭንቀትና ሐዘንን ያመለክታል። ስለሚመጣው ከባድ ጥፋት ማስጠንቀቂያም ይሆናል።


ዋይታ፣ ሰቆቃ

“ዋይታ” እና፣ “ሰቆቃ” የተሰኙት ቃሎች የከባድ ለቅሶ፣ ሕዘን ወይም ትኬ መገለጫዎች ናቸው።


ዓለም፣ ዓለማዊ

ብዙውን ጊዜ፣ “ዓለም” የሚያመለክተው አጽናፈ ዓለሙ ውስጥ ሰዎች የሚኖሩበትን ማለትንን ማለትን ምድርን ነው። “ዓለማዊ” በዚህ ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ክፉ መንገድና አሠራር ያመለክታል።


ዕብራዊ

“ዕብራውያን” በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ሐረግ በኩል የተገኙ የአብርሃም ዘሮች ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ዕብራዊ” ተብሎ የተጠራ የመጀመሪያ ሰው አብርሃም ነበር። “ዕብራውያን” በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ሐረግ በኩል የአብርሃም ዘር የሆኑ ሕዝብ ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ዕብራው” ተብሎ የተጠራ የመጀመሪያ ሰው አብርሃም ነው።


ዘላለም፣ ዘላለማዊ

“ዘላለም” እና “ዘላለማዊ” በጣም ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ሲሆን፣ የሚያመለክቱት ሁሌም የሚኖር ወይም ማለቂያ ማብቂያ የሌለውን ነገር ወይም ሁኔታ ነው።


ዝሙት፣ዘማዊነት፣ዘማዊ፣ዘማዊት

“ዝሙት” አንድ ያገባ ሰው የትዳር ጓደኛው ካልሆነች ጋር ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን ኃጢአት ያመለክታል። “ዘማዊነት”የዚህ ዐይነት ተግባርን ወይም ይህን ኃጢያት የሚያደርግ ሰው ድትጊት ያመለክታል።


የመወለድ መብት

“የመወለድ መብት” የተሰኘው ቃል ከቤተ ሰቡ የተወለዱ የመጀመሪያ ወንድ ልጅ ያለውን ክብር፣ ከቤተ ሰቡ መጠራትንና ሀብት መወሰድን መደበኛ መብት ያመለክታል።


የመጨረሻ ቀን፣ የመጨረሻዎቹ ቀኖች፣ የኋለኞቹ ቀኖች

“የመጨረሻ ቀን” ወይም፣ “የመጨረሻዎቹ ቀኖች” በአጠቃላይ የሚያመለክቱት በአጠቃላይ ኢየሱስ ወደሚመለስበት ጊዜ የሚያደርሱ ወቅቶች ናቸው።


የሚገባው፣ ዋጋ ያለው፣ የማይገባው፣ ዋጋ ቢስ

“የሚገባው” የሚለው ቃል ክብርና ምስጋና መቀበል ያለበትን ያመለክታል። “ዋጋ ያለው” ውድ ወይም ጠቃሚ ነገርን ያመለክታል። “ዋጋ ቢስ” ግን ለምንም የማይጠቅም ማለት ነው።


የማእዘን ድንጋይ

“የማእዘን ድንጋይ” የሚለው ሐረግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ተጠርቦ የሕንጻው መሠረት አንድ ጥግ ላይ የሚቀመጥ ትልቅ ድንጋይ ነው።


የምሥራች፣ ወንጌል

ቃል በቃል የምሥራች ማለት ሲሆን፣ ሰዎችን የሚጠቅምና ደስ የሚያሰኛቸውን መልእክት ያመለክታል።


የሰራዊት ጌታ ያህዌ፣ የሰራዊት ጌታ፣ ሰራዊት

“የሰራዊት ጌታ ያህዌ” እና፣ “የሰራዊት ጌታ” የሚሉት ሐረጎች ለእርሱ በሚታዘዙ እጅግ ብዙ መላእክት ላይ እግዚአብሔር ያለውን ሥልጣን የሚገልጡ አባባሎች ናቸው።


የሰው ልጅ

የሰው ልጅ“የሰው ልጅ” የሚለው ሐረግ ብዙ ጊዜ ኢየሱስ ራሱን የሚጠራበት ስም ነበር። ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “የሰው ልጅ” ማንኛውም ሰው የሚታወቅበት ስም ነበር

ጥቅሶች እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታሉ


የስርየት መክደኛ

“የስርየት መክደኛ” ከወርቅ የተሠራ ጠፍጣፋ ነገር ሲሆን የታቦቱን የላይኛ ክፍል ለመሸፈን ጥቅም ላይ ይውል ነበር። አንዳንድ ትርጉሞች “የስርየት መሸፈኛ” ይሉታል


የበደል መሥዋዕት

“በደል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኀጢአት ማድረግን ወይም ወንጀል መፈጸምን ነው።


የተመረጠ፣ የተመረጠ ሕዝብ፣ የተመረጠው፣ ምርጦች

“የተመረጠ” ወይም፣ “ምርጦች” የሚለው ቃል በቃል፣ “የተመረጡት” ወይም፣ “የተመረጠ ሕዝብ” ማለት ሲሆን አባባሉ የእርሱ ሕዝብ እንደሆኑ እግዚአብሔር የመደባቸውን ወይም የመረጣቸውን ያመልክታል። “የተመረጡ” ወይም፣ “በእግዚአብሔር የተመረጠው፣ የተመረጠ መሲሕ የሆነው የኢየሱስ መጠሪያ ነው።


የተስፋ ምድር

“የተስፋ ምድር” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እንጂ በጠቅላላው መጽሐፍ ቅዱስ አይደለም። ለአብርሃምና ለዘሮቹ እንደሚሰጥ እግዚአብሔር ቃል የገባላት የምድረ ከነዓን አማራጭ ቃል ነው።

ነቢይ፣ ትንቢት፣ ትንቢት ተናገረ፣ ተመልካች፣ ነቢዪት “ነቢይ” የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚናገር ሰው ነው። ይህን የምታደርግ ሴት ነቢዪት ትባላለች።


የተወደደ

“የተወደደ” በሌላው ሰው የተወደደና ውድ የሆነ ሰውን የሚያሳይ የፍቅር መገለጫ ቃል ነው


የአራተኛው ክፍል ገዥ

የአራተኛው ክፍል ገዥ የሚባለው የሮም መንግሥትን የተወሰነ ክፍል በመግዛት ላይ ያለ ባለ ሥልጣንን ነው። እያንዳንዱ የአራተኛው ክፍል ገዥ ከሮም ንጉሥ ሥልጣን ሥር ነበር።


የአይሁድ ንጉሥ


የእግዚአብሔር ልጅ፣ ልጁ፣ ልጅ(ወልድ)

“የእግዚአብሔር ልጅ” ሰው ሆኖ ወደ ዓለም የመጣውን ቃል ኢየሱስን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ፣ “ልጁ” ተብሎም ይጠራል


የእግዚአብሔር ልጆች

“የእግዚአብሔር ልጆች” በርካታ ትርጉሞች ያሉት ምሳሌያዊ አነጋገር ሊሆን ይችላል


የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ ሕዝቤ

“የእግዚአብሔር ሕዝብ” የተሰኘው ሐረግ ከእርሱ ጋር የተለየ ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር ከዓለም የጠራውን ሕዝብ ነው።


የእግዚአብሔር መንግሥት፣ መንግሥተ ሰማይ

“የእግዚአብሔር መንግሥት” እና፣ “መንግሥተ ሰማይ” የሚሉት ሁለቱም የሚያመለክቱት በሕዝቡና በፍጥረት ሁሉ ላይ እግዚአብሔር ያለውን አገዛዝ ነው።


የእግዚአብሔር ቃል፣ የያህዌ ቃል፣ የጌታ ቃል፣ ቅዱሳት መጻሕፍት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “የእግዚአብሔር ቃል” የሚባለው እግዚአብሔር ለሰዎች የተናገረው ማንኛውንም ነገር ያመለክታል። ይህም ንግግርና በጽሑፍ የሰፈረ መልእክትን ይጨምራል። ኢየሱስ ራሱ፣ “የእግዚአብሔር ቃል” ተብሏል።


የእግዚአብሔር ቤት፣ የያህዌ ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “የእግዚአብሔር ቤት” እና፣ “የያህዌ ቤት” የተሰኙት ሐረጎች የሚያመለክቱት እግዚአብሔር የሚመለክትበትን ቦታ ነው።


የእግዚአብሔር አምሳል፣ ምስል

“አምሳያ” የሚለው ሌላውን የሚመስል፣ በጸባይም ሆነ በጥንተ ተፈጥሮው ሌላውን የመሰለ ማለት ነው። “የእግዚአብሔር አምሳል” የሚለው ሐረግ እንደ አውዱ ሁኔታ በተለያየ መንገድ ጥቅም ላይ ይውላል።


የእግዚአብሔር ፈቃድ

“የእግዚአብሔር ፈቃድ” የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ፍላጎትና እቅድ ነው።


የክርስቶስ ተቃዋሚ

የክርስቶስ ተቃዋሚ የሚለው አገላለጽ እየሱስ ክርስቶስንና ሥራውን የሚቃወም ሰውን ወይም ትምህርትን ነው የሚያመለክተው በዓለም ውስጥ ብዙ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች አሉ።


የጌታ ቀን፣ ይያህዌ ቀን

“የያህዌ ቀን” የተሰኘው የብሉይ ኪዳን አገላለጽ ከኀጢአታቸው የተነሣ እግዚአብሔር ሕዝቡን የሚቀጣበትን የተለየ ቀን ወይም ቀኖች ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል።


የጌታ እራት

“የጌታ እራት” የሚለውን ቃል ሐዋርያው ጳውሎስ የተጠቀመበት በአይሁድ መሪዎች በተያዘበት ሌሊት ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የበላውን የፋሲካ ምግም ለማመልከት ነበር።


የጽዮን ሴት ልጅ

የጽዮን ሴት ልጅ የእስራኤልን ሕዝብ የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው። ብዙውን ጊዜ ትንቢት ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።


የፍርድ ቀን

“የፍርድ ቀን” እግዚአብሔር በማንኛውም ሰው ላይ የሚፈርድበት ወደፊት የሚመጣ ጊዜ ነው።


ያህዌ

“ያህዌ” የእግዚአብሔር የተፀውዖ ስም ሲሆን፣ በሚቃጠለው ቁጥቋጦ ውስጥ እግዚአብሔር ራሱን ለሙሴ የገለጠው በዚህ ስሙ ነበር።


ያልቦካ እንጀራ

“ያልቦካ እንጀራ” የሚያመለክተው ያለ እርሾ ወይም እንዲቦካ የሚያደርግ ሌላ ነገር ሳይገባበት የተጋገረ እንጀራን ነው። ያልቦካ ዳቦ ኩፍ አይልም፣ ስለዚህ ጠፍጣፋ ነው።


ይቅር ማለት ይቅርታ

አንድን ሰው ይቅር ማለት ከዚህ ቀደም ባደረገው መጥፎ ነገር ቂም አለመያ ማለት ነው። “ይቅርታ” ሌላውን ይቅር የማለት ተግባር ነው።


ደም

“ደም” ጉዳት ወይም ቁስል ሲኖር ከአንድ ሰው ቆዳ የሚወጣ ቀይ ፈሳሽ ነገርን ያመለክታል። ደም ለሰው አካል ሕይወት ሰጪ ምግብን ያመጣል።


ደቀ መዝሙር

“ደቀ መዝሙር” በቃልም ሆነ በሕይወት ምሳሌነት ከመምህሩ ለመማር ሲል ብዙ ጊዜውን ከመምህሩ ጋር የሚያሳልፍ ሰው ነው።


ዲያቆን

ዲያቆን ምግብን ወይም ገንዘብን በመሳሰሉ ተግባራዊ ነገሮች አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉትን በመርዳት የሚያገለግል ሰው ነው።


ድንጋይ፣ በድንጋይ መውገር

ድንጋይ አነስ ያለ ዐለት ነው። በድንጋይ መውገር አንድን ሰው ለመግደል እርሱ ላይ ድንጋዮች መወርወር ማለት ነው


ጃንደረባ

ብዙ ጊዜ፣ “ጃንደረባ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የተኮላሸ ወንድን ነው በኋላ ግን ቃሉ አካላዊ ጉድለት ባይኖርባቸውም በአጠቃላይ ማንኛውንም የመንግሥት ባለሥልጣን የሚያመለክት ሆነ።


ገሃነም፣ የእሳት ባሕር

ገሃነም በእርሱ ላይ የሚያምፁትንና በኢየሱስ መሥዋዕትነት በኩል እነርሱን የማድኑን ዕቅድ ችላ የሚሉትን የሚቀጣበት የመጨረሻው የስቃይ ቦታ ነው። “የእሳት ባሕር” ተብሎም ይጠራል።


ጋኔን፣ ክፉ መንፈስ፣ ርኵሳን መናፍስት

እነዚህ ሁሉ የሚያመለክቱት አጋንንትን ሲሆን፣ አጋንንት የእግዚአብሔርን ፈቀድ የሚቀወሙ መንፈሳዊ ፍጥረቶች ናቸው።


ጌታ ያህዌ፣ ያህዌ አምላክ

እንዱ እውነተኛ አምላክን በተመለከተ እነዚህ ቃሎች ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሰዋል።


ጌታ፣ አዛዥ፣ አለቃ

“ጌታ” የሚለው ቃል ሰዎች ላይ ባለቤትነት ወይም ሥልጣን ያለውን ሰው ያመለክታል።


ግርማ

ብዙውን ጊዜ “ግርማ” ከንጉሥ ክብር ጋር በተያያዘ መልኩ ትልቅነትንና ውበትን ነው የሚያመለክተው።


ግብዝ፣ ግብዝነት

“ግብዝ” የሚለው ልቡ ክፉና ጠማማ ሆኖ በሰዎች ፊት ግን መልካም ሰው መስሎ ለመታየት የሚሞክር ሰው ነው። “ግብዝነት” መልካምና እውነተኛ መስሎ ለመታየት አንድ ሰው የሚያደርገው ነው።


ግዛት

ግዛት ሰዎችን፣ እንስሳትንና መሬትን የመቆጣጠር፣ የመግዛት ኃይልና ሥልጣንን ያመለክታል።


ጠቢባን

“ጢቢባን” የተሰኘው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የተለየ ዕውቀትና ችሎታ ያላችው ሰዎችን ለማመልከት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሰዎች በንጉሡ አደባባይ ነበር የሚገኙት።


ጴንጠቆስጤ (በዓለ ሃምሳ)፣ የሳምንቶች በዓል

በዓለ ሃምሳ ከፋሲካ ሃምሳ ቀን በኋላ የሚከበረው የአይሁድ በዓል ግሪክኛ ስም ነው።


ጸሐፍት፣ የአይሁድ ሕግ መምሕራን

ጸሐፍት መንግሥታዊ ወይም ሃይማኖታዊ ሰንዶችን በእጅ ጽሑፍ የማርቀቅ ወይም የመገልበጥ ኅላፊነት የነበረባቸው ባለ ሥልጣኖች ናቸው


ጸያፍ


ጸጋ፣ ባለጸጋ

“ጸጋ” የሚለው ቃል ምንም ሳይለፋና ሳይደክም አንድን ሰው መርዳትን ወይም መባረክን ያመለክታል። “ባለ ጸጋ” ሌሎችን ጸጋ የሚያሳይን ሰው ይመለከታል።


ጻድቅ፣ ጽድቅ

“ጻድቅ” እና፣ “ጽድቅ” የእግዚአብሔር ፍጹም መልካምነት፣ ፍትሕ፣ ታማኝነትና ፍቅር ያመለክታል። እግዚአብሔር ጻድቅ ስለሆነ ኀጢአት ላይ መፍረድ አለበት።


ጽዮን፣ የጽዮን ተራራ

መጀመሪያ ላይ፣ “ጽዮን” ወይም፣ “የጽዮን ተራራ” ተብሎ ይጠራ የነበረው ንጉሥ ዳዊት ከኢያቡሳውያን የያዝሰው ምሽግ ወይም መሸሸጊያ ቦታ ስም ነበር። የኢየሩሳሌም ከተማ በተመሠረተችባቸውና የዳዊት መኖሪያ ከሆነው ኮረብቶች አንዱ ላይ ነበር የሚገኘው።


ፈሪሳዊ

ፈሪሳውያን ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ዘመን በጣም ታዋቂ የእስራኤል ሃይማኖት መሪዎች ነበር። አብዛኞቹ መካከለኛ ኑሮ ያላቸው ሠራተኞች ሲሆኑ፣ ጥቂቶቹም ካህናት ነበሩ።


ፈራጅ፣ ፍርድ

ብዙውን ጊዜ፣ “ፈራጅ” ወይም፣ “ፍርድ” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት ከግብረ ገብ አንጻር አንድ ነገር ትክክል መሆን አለመሆኑን በተመለከተ ውሳኔ መስጠት ነው።


ፈተና

“ፈተና” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ብርታትና ድካም ለይቶ የሚያሳይ አስቸጋሪ ወይም አዳጋች ሁኔታ ያመለክታል።


ፋሲካ (ማለፍ)

ፋሲክ እግዚአብሔር አባቶቻቸው እስራኤላውያንን እንዴት ከግብፅ ባርነት እንዳዳናቸው ለማሰብ አይሁድ በየዓመቱ የሚያከብሩት ሃይማኖታዊ በዓል ስም ነው።


ፍርሃት፣ ፈራ፣ የያህዌ ፍርሃት

“ፍርሃት” እና፣ “ፈራ” የሚሉት በእርሱ ወይም በሌሎች ላይ ጉዳት ይመጣል ብሎ ሲያስብ የሚኖረው ደስ የማይል ስሜት ነው።


ፍቅር

አንድን ሰው መውደድ ለዚያ ሰው ማሰብና መጠንቀቅ እንዲሁም ለእርሱ የሚጠቅመውን ነገር ማድረግ ነው። “ፍቅር” የተለያዩ ትርጕሞች አሉት፤ አንዳንድ ቋንቋዎች በተለያዩ ቃሎች ይገልጹታል። 1. ከእግዚአብሔር የሚመጣው ፍቅር ምንም እንኳ ራስን የሚጠቅም ባይሆንም ሌሎችን መጥቀም ላይ ያተኩራል። ምንም ያድርጉ ምን ይህ ፍቅር ለሌሎች ያስባል፣ ለሌሎች ይጠነቃቃል። እግዚአብሔር ራሱ ፍቅር ነው፤ የእውነተኛ ፍቅር ምንጭም እርሱ ነው።

  1. ሌላው የአዲስ ኪዳን ቃል የወንድማማችነት ፍቅርን ወይም ጓደኛን ወይም ቤተ ሰብን ማፍቀርን የሚመለከተው ነው።
  1. “ፍቅር” የሚለው ቃል በወንድና በሴት መካከል ያለውን መሳሳብና ማደድንም ያመለክታል። 4. “ያዕቆብን ወደድሁ (አፈቀርሁ) ኤሳውን ግን ጠላሁ” በሚለው አነጋገር ውስጥ፣ “ወደድሁ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ያዕቆብ ከእርሱ ጋር የኪዳን ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር መምረጡን ነው። ስለዚህ እዚህ ላይ ይህ ቃል፣ “መረጥሁ” ተብሎ መተርጎም ይችላል ማለት ነው። ምንም እንኳ ኤሳውም በእግዚአብሔር ቢበክም፣ ከእርሱ ጋር ኪዳን የማድረግን መብት አላገኘም። “ጠላሁ” የሚለውም ቃል፣ “አልፈለግሁትም” ወይም፣ “አልመረጥሁም” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።

ፓስተር

“ፓስተር” የሚለው ቃል በቃል፣ “እረኛ” ከሚለው ጋር አንድ ነው። የአማኞች ስብስብ መንፈሳዊ መሪ ለሆነ ሰው የሚሰጥ ስም ነው።


Names

ሄሮድያዳ

ሄሮድያዳ መጥምቁ ዮሐንስ ባገለገለበት ዘመን ይሁዳን እየገዛ የነበረው ንጉሥ ሄሮድስ (አንቲጳስ) ሚስት ነበረች።


ሄኖክ

ሄኖክ የሁለት የብሉይ ኪዳን ሰዎች ስም ነው።


ሆሴዕ

ሆሴዕ ከክርስቶስ 750 ዓመት በፊት የእስራኤል ነቢይ ነበር።


ሆሺያ (ሆሴዕ)

ሆሺያ (ሆሴዕ) በይሁዳ ነገሥታት በአካዝና በሕዝቅያስ ግዛት ዘመን ለዘጠኝ ዓመት የእስራኤል ንጉሥ ነበር።


ሉቃስ

ሉቃስ አዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉ ሁለት መጻሕፍት የሉቃስ ወንጌልና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ነው።


ሊባኖስ

ሊባኖስ ከእስራኤል በስተ ሰሜን ሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ የምትገኝ በጣም የምታምር ተራራማ ቦታ ናት። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ይህ አካባቢ ጥቅጥቅ ባሉት ደኖቹም ይታወቅ ነበር።


ላሜሕ

ላሜሕ ዘፍጥረት ውስጥ የተጠቀሱ የሁለት ሰዎች ስም ነው።


ላባን

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ላባን የያዕቆብ አጎትና አማት ነበር።


ሌዋታን

“ሌዋታን” የሚለው ቃል በቀደሙት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የተጠቀሰ በጣም ግዙፍና አሁን የማይገኝ አውሬ ነው።


ሌዋዊ፣ ሌዊ

ሌዋዊ የሌዊ ዘር የሆነ የእስራኤል ማኅበረ ሰብ አባል ነው።


ልስጥራ

ልስጥራ በአንዱ ሐዋርያዊ ጕዞው ጳውሎስ የጎበኛት ታናሽ እስያ ውስጥ የነበረች ከተማ ስም ነው። የምትገኘው የአሁንዋ ቱርክ ባለችበት ሊቃኦንያ አካባቢ ነበር።


ልያ

ልያ ከያዕቆብ ሚስቶች አንኳ ነበረች። የዐሥር ወንዶች ልጆች እናት ስትሆን ዐሥሩ ልጆች ከእስራኤል ነገዶች የተወሰኑት ነበሩ።


ሎጥ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሎጥ የአብርሃም ወንድም ልጅ ነበር።


ሐማት፣ ሌቦ ሐማት

ሐማት ከምድረ ከነዓን በስተ ሰሜናዊ ሶርያ ውስጥ ትገኝ የነበረች በጣም ጠቃሚ ከተማ ናት። በዚህ ዘመን የከተማዋ ስም ሐማ ይባላል።


ሐራን

ሐራን የአብርሃም ታናሽ ወንድምና የሎጥ አባት ነበር።


ሐና

ሐና ከ6-15 ዓ፤ም ከ10 ዓመት በእየሩሳሌም የነበረ አይሁዳዊ ሊቀ ካህን ነው፤ይሁን እንጂ በኋላ ላይ ሮማውያን ከሊቀ ካህንነቱ አንስተውታል፤ያም ሆኖ በአይሁድ ዘንድ የነበርው ተደማጭነት መሪ በመሆን ቀጥሎ ነበር።


ሐና

ሐና ብሉይ ኪዳኑ ውስጥ የነቢዩ ሳሙኤል እናት ናት። ከሕልቃና ሚስቶች አንዷ ነበረች።


ሐጌ

ሐጌ እስራኤል ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ በኋላ የነበረ የይሁዳ ነቢይ ነበር።


ሔዋን

ይህ የመጀመሪያዋ ሴት ስም ነበር። የስሟ ትርጉም፣ “ሕይወት” ወይም፣ “ሕያው” ማለት ነው።


ሕዝቅኤል

ሕዝቅኤል ብዙ አይሁድ ወደባቢሎን በተወሰዱበት የምርኮ ወቅት የነበረ የእግዚአብሔር ነብይ ነው።


ሕዝቅያስ

ሕዝቅያስ 13ኛው የይሁዳ ንጉሥ ነበር። በእግዚአብሔር የሚታመንና ለእርሱ የሚታዘዝ ንጉሥ ነበር።


መልከጼዴቅ

አብርሃም በነበረበት ዘመን መልከጼዴቅ፣ በኋላ፣ “ኢየሩሳሌም” ተብላ የተጠራችው የሳሌም ከተማ ንጉሥ ነበር።


መርዶክዮስ

መርዶክዮስ በፋርስ አገር ይኖር የነበረ አንድ አይሁዳዊ ስም ነው። በኋላ ላይ የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ሚስት የሆነችው የአጎቱ ልጅ የአስቴር ጠባቂ ነበር።


መስጴጦምያ፣ አራም ናሐራይም

መስጴጦምያ በኤፍራጥስና በጤግሮስ ወንዞች መካከል ያለ ምድር ነው። ስፍራው የዘመኑ ኢራቅ ያለችበት ቦታ ነበር።


መቄዶንያ

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን መቄዶንያ ከጥንቱ ግሪክ በስተ ሰሜን የነበረች የሮም አውራጃ ነበረች።


መዓካ

መዓካ የአብርሃም ወንድም ናሆር ከወለዳቸው ልጆች አንደኘው ነው። በብሉይ ኪዳን ሌሎችም ሰዎች ይህ ስም ነበራቸው።


ሙሴ

ሙሴ ለ40 ዓመት የእስራኤል ሕዝብ ነቢይና መሪ ነበር።


ሚልክያስ

ሚልክያስ ወደ እስራኤል ከተላኩት የእግዚአብሔር ነቢያት አንዱ ነው።


ሚሳኤል

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሚሳኤል ተብለው የተጠሩ ሦስት ሰዎች አሉ።


ሚካኤል

ሚካኤል ቅዱሳንና ታዛዦች ከሆኑት የእግዚአብሔር መላእክት ዋናው ነው። የእግዚአብሔር፣ “ሊቀ መልአክ” ተብሎ የተጠራ እርሱ ብቻ ነው።


ሚክያስ

ሚክያስ ነቢዩ ኢሳይያስም በይሁዳ እያገለገለ በነበረ ጊዜ ከክርስቶስ 700 ዓመት በፊት የነበረ የይሁዳ ነቢይ ነበር።


ሚጽጳ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሚጽጳ ተብለው የተጠሩ ጥቂት ቦታዎች አሉ። ትርጕሙ፣ “መመልከቻ ቦታ” ወይም፣ “ቅጥር መጠበቂያ” ማለት ነው።


ማርታ

ማርታ ቢታንያ በተባለ ቦታ ትኖር የነበረ የኢየሱስ ተከታይ ሴት ናት።


ማርያም

ማርያም የአሮንና የሙሴ ታላቅ እኅት ነበረች።


ማርያም (የማርታ እኅት)

ማርያም ቢታንያ በሚባል ቦታ ትኖር የነበረ የኢየሱስ ተከታይ ናት።


ማርያም መግደላዊት

ማርያም መግደላዊት ኢየሱስን መከተል የጀመረችው ሰባት አጋንንት ከእርሷ ካስወጣ በኋላ ነበር።


ማርያም የኢየሱስ እናት

ማርያም የዮሴፍ እጮኛና የኢየሱስ እናት ናት።


ማቴዎስ፣ ሌዊ

ማቴዎስ ለእልፍዮስ ልጅ ለሌዊ የተሰጠ ስም ነው። ማቴዎስ ሐዋርያቱ እንዲሆኑ ኢየሱስ ከመረጣቸው አሥራ ሁለት ሰዎች አንዱ ነበር።


ሜምፊስ

ሜምፊስ ዐባይ ወንዝ መደዳ የምትገኝ ጥንታዊ ግብፅ ውስጥ የነበረች ከተማ ነበረች።


ሜዶን፣ ሜዶናውያን

ሜዶን ከአሦርና ከባቢሎን በስተ ምሥራቅ፣ ከኤላምና ከፋርስ በስተ ሰሜን የነበረ ትንታዊ መንግሥት ነው። የነበረበት ቦታ በአሁኑ ዘመን ቱርክ፣ ኢራን፣ ሶርያ፣ ኢራቅና አፍጋኒስታን ያሉበትን በክፊል ያካትት ነበር።


ምሳሕ

ምሳሕ የኖኅ ልጅ የያፌት ልጅ ነው። ሌላው ሞሳሕ ተብሎ የተጠራ ሰው የኖኅ ልጅ የሴም የልጅ ልጅ ነው።


ምናሴ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ምናሴ ተብለው የተጠሩ አምስት ሰዎች ነበር።


ምድያማዊ፣ ምድያማውያን

ምድያማውያን ከከነዓን በስተ ደቡብ ሰሜናዊው የአረቢያ ምድረ በዳ ይገኙ የነበሩ ሕዝብ ናቸው።


ሞሎክ

ሞሎም ከነዓናውያን ከሚያመልኳቸው ሐሰተኛ አማልክት የአንዱ ስም ነበር።


ሞዓብ፣ ሞዓባዊ፣ ሞዓብዊት

ሞዓብ የኖኅ ታላቅ ሴት ልጅ ልጅ ነበር። ዘሮቹ ሞዓባውያን ሲባሉ የሰፈሩበት ቦታ ሞዓብ ተባለ።


ሠሪ

አጠቃላይ በሆነ አነጋገር፣ “ሠሪ” ነገሮችን የሚፈጥር ወይም የሚሠራ ማለት ነው።


ሣራ፣ ሦራ


ረባት

ረባት በጣም ጠቃሚ የአሞራውያን ከተማ ነበረች።


ረዓብ

ረዓብ እስራኤላውያን ኢያሪኮን ሲያጠቁ እዚያ የነበረች ሴት ነበረች። አመንዝራም ነበረች።


ሩት

ሩት መሳፍንት እስራኤላውያንን እየመሩ በነበረ ዘመን የነበረች ሞዓባዊት ሴት ናት። ጥንታዊ የኢየሱስ ክርስቶስ መገኛ ነበረች


ሪሞን

ሪሞን የአንድ ሰው እና መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሳቸው ጥቂት ቦታዎች ስም ነው። ሪሞን የሚባል ጣዖትም ነበር። ቃል በቃል ትርጉሙ፣ “ሮማን” ማለት ነው።


ራሔል

ራሔል ከያዕቆብ ሚስቶች አንዷ ነበረች። እርሷና እኅቷ ልያ የያዕቆብ አጎት የላባን ልጆች ነበሩ።


ራማ

ራማ ከኢየሩሳሌም በስተ ሰሜን 8 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ጥንታዊ የእስራኤል ከተማ ነበረች።


ራሞት

ራሞት ገለዓድ ተራሮች ላይ የምትገኝ በጣም ጠቃሚ ከተማ ነበረች። ራሞት ገለዓድም ትባላለች።


ርብቃ

ርብቃ ከአብርሃም ወንድም ልጆች አንዷ ነበረች፤ የእርሷ አያት የአብርሃም ወንድም ነበር።


ሮም፣ ሮማዊ

በዚህ ባለንበት ዘመን ሮም የኢጣልያ ዋና ከተማ ናት።


ሮቤል

ሮቤል የመጀመሪያው የያዕቆብ ልጅ ነበር። እናቱ ልያ ትባላለች።


ሮብዓም

ሮብዓም ከንጉሥ ሰሎሞን ልጆች አንዱ ሲሆን፣ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ የእስራኤል ሕዝብ ንጉሥ ሆኗል.


ሰሎሞን

ሰሎሞን ከንጉሥ ዳዊት ልጆች አንዱ ነበር። የእናቱ ስም ቤርሳቤህ ይባል ነበር


ሰማርያ፣ሳምራዊ

ሰማርያ ለእስራኤል ሰሜናዊ አካባቢ ላለው ከተማና አካባቢው የተሰጠ ስም ነው። ይህ አካባቢ በምዕራብ በሳሮን ሜዳማ ቦታና በምሥራቅ በኩል በዮርዳኖስ ወንዝ መካከል ይገኛል


ሰሜኢ፣ ሳሚ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሰሜኢ ተብለው የተጠሩ ጥቂት ሰዎች ነበሩ።


ሰናክሬም

ሰናክሬም ነነዌ ሀብታምና ተፈላጊ ከተማ እንድትሆን ታላቅ የአሦር ንጉሥ ነበር


ሰናዖር

ሰናዖር፣ “የሁለት ወንዞች አገር” ማለት ሲሆን በደቡባዊ ሜሶፖታሚያ ላለው ሜዳ ወይም አካባቢ የተሰጠ ስም ነበር


ሰዶም

ሰዶም የአብርሃም ወንድም ልጅ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር ይኖርበት የነበረ ከከነዓን በስተ ደቡብ አካባቢ ያለ ከተማ ነበር


ሰፎንያስ

ካህንና ነቢይን ጨምሮ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሶፎንያስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ሰዎች ነበር። የሶፎንያስ ትንቢት የሚገኘው ትንቢተ ሶፎንያስ ውስጥነው።


ሱኮት

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሱኮት ተብለው የተጠሩ ሁለት ከተሞች አሉ። ሱኮት “መጠለያ” ወይም፣ “መጠጊያ” ማለት ነው


ሲላስ፣ ስልዋኖስ

ሲላስ በኢየሩሳሌም በነበሩ አማኞች መካከል መሪ ነበር


ሲና፣ የሲና ተራራ

ሲና በአሁኑ ዘመን የሲና ፔኔንሱላ ተብሎ በሚጠራው ደቡባዊ ክፍል የሚገኝ ተራራ ስም ነው


ሲዶን፣ ሲዶናውያን

ሲዶን የከነዓን የመጀመሪያ ልጅ ነበር፤ ሲዶን የምትባል የከነዓናውያን ከተማም አለች


ሳሙኤል

ሳሙኤል የመጨረሻው የእስራኤል መስፍን እና ነቢይ ነበር፤ የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆኑ ሳኦልንና ዳዊትን የቀባው እርሱ ነበር


ሳምሶን

ሳምሶን ከእስራኤል መሳፍንት ወይም ታዳጊ አንዱ ነበር። ሳምሶን ከዳን ነገድ ነበር።


ሳሮን፣ የሳሮን ሜዳ

ሳሮን ከቀርሜሎስ ተራራ በስተ ደቡብ ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ጠፍጣፋና ለም ምድር ነው። “የሳሮን ሜዳ” በመባልም ይታወቃል


ሳባ

በጥንት ዘመን ሳባ ደቡብ አረቢያ አንድ ቦታ የሚገኝ ሥልጣኔ ወይም አካባቢ ነበር


ሳኦል (ብሉይ ኪዳን)

ሳኦል የመጀመሪያው የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን እግዚአብሔር የመረጠው እስራኤላዊ ነበር

ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ ሳኦል የሚሉት ሌላ እስራኤላዊ ነበር፤ በኢየሱስ ካመነ በኋላ እግዚአብሔር ስሙን ጳውሎስ ወደሚል ለወጠው


ሳዶቅ

ሳዶቅ በንጉሥ ዳዊት ዘመን በእስራኤል የነበረ ሁነኛ ሊቀ ካህን ነበር።


ሴሎ

ሴሎ በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን አሸንፈው የያዟት በግንብ የተከበበች የከነዓናውያን ከተማ ነበረች


ሴም

ሴም ከሦስቱ የኖኅ ወንዶች ልጆች አንዱ ሲሆን፣ ኦሪት ዘፍጥረት ውስጥ የተለጸው የጥፋት ውሃ በመጣ ጊዜ ከአባቱ ጋር መርከቡ ውስጥ ገብቶ ነበር


ሴት

ሴት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሰ ሦስተኛው የአዳምና የሔዋን ልጅ ነበር


ሴኬም

ሴኬም ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን 40 ማይል ርቀት ላይ የሚገኝ ከነዓን ውስጥ የነበረ ከተማ ነው። ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሴኬም ተብሎ የተጠራ ሰው ነበር።


ሴዴቅያስ

ሴዴቅያስ የመጨረሻው የይሁዳ ንጉሥ ነው (597-587 ዓቅክ)።


ስምዖን

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስምዖን የተባሉ ጥቂት ሰዎች ነበሩ


ሶርያ

ሶርያ ከእስራኤል ሰሜን ምሥራቅ የሚገኝ አገር ነው። አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን በሮም መንግሥት የሚተዳደር አገር ነው


ቀሬና

ቀሬና ከአፍሪካ ሰሜናዊ ባሕር ዳርቻ ሜዲትራንያን ባሕር ላይ ከቀርጤስ ደሴት ደቡብ ትገኝ የነበረች የግሪክ ከተማ ናት።


ቀርሜሎስ፣ የቀርሜሎስ ተራራ

“የቀርሜሎስ ተራራ” በሜዲትራንያን ባሕር አካባቢ ከሳሮን ሜዳማ ቦታ በስተ ሰሜን የነበረውን የተራራ ተረተር ያመለክታል። በጣም ትልቁ ጫፍ 546 ሜትር ከፍታ አለው።


ቀርጤስ፣ የቀርጤስ ሰው

ቀርጤስ ግሪክ ደቡባዊ ባሕር ዳርቻ ማዶ ትገኝ የነበረች ደሴት ናት። የቀርጤስ ሰው በቀርጤስ የሚኖር ሰው ነው።


ቀናተኛው ስምዖን

ቀናተኛው ስምዖን ከአሥራ ሁለት የኢየሱስ የቅርብ ደቀመዛሙርት አንዱ ነበር


ቀያፋ

ቀያፋ መጥምቁ ዮሐንስና ኢየሱስ ባገለገሉበት ዘመን የእስራኤል ሊቀ ካህን ነበር።


ቂሮስ

ቂቶስ በወታደራው ድል በ550 ዓ.ቅ.ክ. ገደማ የፋርስ መንግሥትን የመሠረተ ነበር። በዓለም ትሪክ ታላቁ ቂሮስ በመባልም ይታወቃል።


ቃና

ቃና ናዝሬት በስተ ሰሜን ዘጠኝ ማይሎች ያህል ርቃ የምትገኝ ገሊላ አውራጃ ውስጥ ያለች መንደር ወይም ከተማ ነበረች።


ቃየን

ቃየንና ታናሽ ወንድሙ አቤል መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ የመጀመሪያ የአዳምና የሔዋን ልጆች ናቸው።


ቃዴስ

ቃዴስ ወይም ቀዴስ በርኔ በአሁኑ ጊዜ ሶርያ በሚባለው ውስጥ የምትገኝ በእስራኤል ታሪክ ውስጥ ጠቃሚ የሆነች ከተማ ነበረች።


ቃዴስ

ቃዴስ ወደ ምድር ከነዓን በገቡ ጊዜ እስራኤላውያን የወሰዷት ከነዓናዊ ከተማ ነበረች።


ቄሳር

“ቄሳር” የተሰኘው ቃል ብዙዎቹ የሮም ገዦች የሚጠቀሙበት ስም ወይም መጠሪያ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ መጠሪያ ሦስት ገዦችን ያመለክታል።


ቄሳርያ፣ ፊልጶስ ቂሳርያ

ቂሳርያ ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ፣ ከቀርሜሎስ ተራራ 39 ኪ.ሜ. ርቃ ትገኝ የነበረች በጣም ጠቃሚ ከተማ ነበረች። ፊልጶስ ቂሳርያ ከእስራኤል ሰሜን ምሥራቃዊ ክፍል አርሞንዔም ተራራ አጠገብ ያለች ከተማ ነበረች።


ቄዳር

ቄዳር የእስማኤል ሁለተኛ ልጅ ሲሆን፣ ከእርሱ ዘሮች ብዙ ሕዝብ ያለው ነበር። ቄዳር የምትባል ታውቂ ከተማም አለች።


ቅፍርናሆም

ቅፍርናሆም ከገሊላ ባሕር ዳርቻ ሰሜን ምዕራብ የምትገኝ ዓሣ የሚጠመድባት ቦታ ናት።


ቆላስይስ፣ የቆላስይስ ሰዎች

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ቆላስይስ ፍርግያ በምትባለው የሮማውያን ግዛት ውስጥ የነበረች ከተማ ስትሆን በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው ከቱርክ ደቡብ ምዕራብ ባለው አካባቢ ነው። የቆላስይስ ሰዎች ቆላስይስ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ናቸው።


ቆሬ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ቆሬ በትንሹ የሁለት ሰዎች ስም ነው።


ቆርኔሌዎስ

ቆርኔሌዎስ በትውልድ አይሁድ ያልሆነ የሮም ወታደሮች ባለ ሥልጣን ነበር።


ቆሮንቶስ፣ የቆሮንቶስ ሰዎች

ቆሮንቶስ ከአቴና በስተ ምዕራብ 50 ማይል ርቃ የምትገኝ የግሪክ ከተማ ነበረች። የቆሮንቶስ ሰዎች በቆሮንቶስ የሚኖሩ ሕዝብ ናቸው።


ቆጵሮስ

ቆጵሮስ ከዘመኑ ቱርክ በስተ ደቡብ 64 ኪሎ ሜትር ላይ ትገኝ የነበረች ሜዲትራንያን ባሕር ላይ ያለች ደሴት ናት።


በለዓም

በለዓም ወደ ከነዓን ምድር ለመግባት በሰሜናዊ ሞዓብ ሰፍረው በነበረ ጊዜ እስራኤልን እንዲረግም ንጉሥ ባላቅ ቀጥሮት የነበር አረማዊ ነብይ ነበር።


በርባን

በርባን ኢየሱስ በተያዘ ጊዜ ኢየሩሳሌም ውስጥ የነበር እስረኛ ነበር


በርቶሎሜዎስ

በርተሎሜዎስ ከአስራ ሁለት የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር


በርናባስ

በርናባስ በሐዋርያት ዘመን የነበረ ከጥንት ክርስቲያኖች አንዱ ነበር


በናያስ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ መናያስ በሚል ስም የሚታወቁ ጥቂት ሰዎች ነበሩ


በኣል

“በኣል” ፦ “ጌታ” ወይም፥ “አለቃ” ማለት ሲሆን፥ ከነዓናውያን ከሚያመልኳቸው ዋነኞቹ ጣዖቶች የአንዱ ስም ነበር።


ቢታንያ

ቢታንያ ከኢየሩሳሌም ምሥራቅ 2ማይል ርቀት ላይ ከደብረ ዘይት ተራራ ምሥራቅ ባለው ተዳፋት ግርጌ የምትገኝ ከተማ ነበረች


ባሕሩ፣ ታላቁ ባሕር፣ የምዕራብ ባሕር

መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ታላቁ ባሕር” ወይም፣ “የምዕራብ ባሕር” የሚለው በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን የነበሩ ሰዎች ከሚያውቁት ባሕር ትልቁ የነበረው፣ ሜዲትራንያን ባሕርን ነው።


ባሮክ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ባሮክ በመባል የሚታወቁ የተለያዩ ሰዎች አሉ


ባሳን

ባሳን ከገሊላ ባሕር በስተምስራቅ አካባቢ ያለ ቦታ ነው። በአሁኑ ዘመን የሶርያ አካል የሆነውን አካባቢና የጎላን ኮረብታን ይሸፍናል


ባቢሎን፥ ባቢሎናዊ

የባቢሎን ከተማ የጥንት ባቢሎንያ አካባቢ ዋና ከተማ ሲሆን፥ የባቢሎን መንግሥት ግዛት አካልም ነበር


ባቤል

ባቤል ከመሰጵጦምያ በስተደቡብ በነበረችው ሰናዖር በምትባል አካባቢ ዋነኛ ከተማ ነበረች በኋላ ላይ ሰናዖር ባቢሎን ተብላለች


ባቱኤል

ባቱኤል የአብርሃም ወንድም የናኮር ልጅ ነበር


ባኦስ

ባኦስ እስራኤል ሐሰተኛ አማልክትን እንዲያመልኩ ካደረጉ የእስራኤል ነገሥታት አንዱ ነበር


ቤርሳቤህ

ቤርሳቤህ በዳዊት ሰራዊት ውስጥ ወታደር የነበርው የኦርዮን ሚስት ነበረች። ኦርዮን ከተገደለ በኋላ የዳዊት ሚስትና የሰሎሞን እናት ሆናለች


ቤርሳቤህ (ቤርሼባ)

ብሉይ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ቤርሳቤህ አሁን ኔጌቭ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለው በረሐ ውስጥ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምዕራብ 45 ማይሎች ላይ የምትገኝ ከተማ ነበረች


ቤርያ

አዲስ ኪዳን ውስጥ ቤርያ ከመቄዶንያ ደቡብ ምስራቅ ከተሰሎንቄ በስተደቡብ 80 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ በጣም ሀብታም የግሪክ ከተማ ነበርች።


ቤተልሔም ኤፍራታ

ቤተልሔም ኢየሩሳሌም ከተማ አጠገብ የምትገኝ አንዲት ትንሽ የእስራኤል ከተማ ነበረች። “ኤፍራታ” በመባልም ትታወቃለች፤ ምናልባት የመጀመሪያ ስሟ ይህ ሳይሆን አይቀርም


ቤቴል

ቤቴል ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን ከነዓን ምድር ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነበረች። የቀድሞ ስሟ “ሎዛ” ነበር


ቤትሳሚስ

ቤትሳሚስ ከኢየሩሳሌም በስተምዕራብ በግምት 30ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ከነዓናዊት ከተማ ስም ነው


ብንያም

ብንያም ከያዕቆብና ከሚስቱ ከራሔል የተወለደ የመጨረሻው ልጅ ነው። የስሙ ትርጉም ፥ “የቀኝ እጄ ልጅ” ማለት ነው።


ብዔልዜቡል

ብዔልዜቡል የአጋንንት አለቃ ሲሆን፥ የሰይጣን ወይም የድያብሎስ ሌላ ስም ነው


ቦዔዝ

በዔዝ የሩት ባል፣ የንጉሥ ዳዊት አያትና ኢየሱስ የተገኘበት ዘር ዋና ግንድ የነበረ እስራኤላዊ ነበር።


ተርሴስ

ተርሴስ የኖኅ ልጅ የያፌት ልጅ ልጅ ስም ነው


ተሰሎንቄ፣ የተሰሎንቄ ሰዎች

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ተሰሎንቄ በጥንቱ የሮም ግዛት ውስጥ የነበረችው የመቄዶንያ ዋና ከተማ ነበረች። በዚያ ከተማ የነበሩ፣ “የተሰሎንቄ ሰዎች” ይባላሉ።


ቲርዛ

ቲርዛ በጣም ጠቃሚ የከነዓናውያን ከተማ ነበረች፤ በኋላም የሰሜናዊው የእስራእል መንግሥት ጊዜያዊ ዋና ከተሞች አንዷ ሆና ነበር።


ቲቶ

ቲቶ ሐዋርያው ጳውሎስ ያስተማረው የጥንት ቤተ ክርስቲያን መሪ ነበር።


ቲኪቆስ

ቲኪቆስ ከጳውሎስ ጋር የወንጌል አገልጋዮች ከነበሩት አንዱ ነው።


ታላቁ ሄሮድስ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሄሮድስ የሚባሉ ጥቂት ገዦች ነበር። ኢየሱስ በተወለደ ዘመን ሄሮድስ አይሁድ ያልሆነ የይሁዳ ንጉሥ ነበር።


ታራ

ታራ የኖኅ ልጅ የሴም ዘር ነው። የአብርሃም፣ የናኮርና የካራን አባት ነበር።


ትዕማር

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ትዕማር ተብለው የተጠሩ በርካታ ሴቶች ነበሩ። ትንቢተ ሕዝቅኤል ውስጥ ትዕማር የተባለ ቦታ ተጠቅሷል


ቶማስ

ቶማስ ደቀ መዛሙርቱ እንዲሆኑ ኢየሱስ ከመረጣቸው ሰዎች አንዱ ነበር (ሐዋርያት ተብለዋል)።


ቶቤል

ቶቤል የኖኅ ልጅ የያፌት ልጅ ነው።


ነህምያ

ነህምያ የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ በባቢሎናውያን በምርኮኝነት በተወሰዱ ጊዜ ባቢሎን መንግሥት ውስጥ ይኖር የነበረ እስራኤላዊ ነው።


ነነዌ፣ የነነዌ ሰዎች

ነነዌ የአሦር ዋና ከተማ ነበረች። የነነዌ ሰዎች ነነዌ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ናቸው።


ናሆም

ናሆም ክፉው ንጉሥ ምናሴ እየገዛ በነበረበት ዘመን ያገለገለ የእግዚአብሔር ነቢይ ነበር።


ናቡከደነፆር

ናቡከደነፆር የባቢሎን መንግሥት ንጉሥ ነበር። የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥታት በነበሩበት ዘመን ባቢሎን ገናና መንግጥ ነበረች።


ናታን

ናትን ዳዊት የእስራኤል ንጉሥ በሆነበት ዘመን የኖረ ታማኝ የእግዚአብሔር ነቢይ ነው።


ናኮር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ናኮር ተብለው ከተጠሩ ሁለት ሰዎች አንደኛው የአብርሃም አያት ሲሆን፣ ሁለተኛው የአብርሃም ወንድም ነበር።


ናዝሬት፣ ናዝራዊ

ናዝሬት በሰሜናዊ እስራኤል ገሊላ አውራጃ ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነች።


ኔጌብ

ኔጌብ በደቡባዊ እስራኤል የሚገኝ በረሃማ አካባቢ ነው።


ንዕማን

ንዕማን የእስራኤል ጠላቶች አንዱ የነበረው የሶርያ ጦር አዛዥ ነበር።


ንፍታሌም

ንፍታሌም ስድስተኛው የያዕቆብ ልጅ ነው። የእርሱ ዘሮች ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ የሆነውን የንፍታሌም ነገድ አስገኝተዋል።


ኖኅ

ኖኅ በዓለም የነበሩ ክፉ ሰዎችን ለማጥፋት እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ የሚያዳርስ ጎርፍ በላከበት ጊዜ ከ4000 ዓመት በፊት ይኖር የነበረ ሰው ነው። ጎርፉ ምድርን በሚሸፍንበት ጊዜ እርሱና ቤተ ሰቡ የሚኖሩበት ግዙፍ መርከብ እንዲሠራ እግዚአብሔር ለኖኅ ነገረው።


አልዓዛር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልዓዛር የበርካታ ስሞች ስም ነበር።


አልዓዛር

አልዓዛር ኢየሱስ ከሞት ያስነሣው ወዳጁ ነበር።


አማሌቅ፣ አማሌቃዊ

አማሌቃዊ ከኔጌብ ምድረ በዳ አንሥቶ እስከ አረብ አገር ድረስ ባለው የከነዓን ደቡባዊ ክፍል በሙሉ የሚኖሩ ዘላን ሕዝብ ነበሩ።እነዚህ ሰዎች የኤሳው ልጅ ልጅ የአማሌቅ ዘሮች ናቸው።


አሜስያስ

አባቱ ንጉሥ አዩአስ ከተገደለ በኋላ አሜስያስ የይሁዳ ንጉሥ ሆነ።


አምኖን

ከአኪናሆም የተወለደ የዳዊት ታላቅ ልጅ ነው፤፤


አሞራዊ

አሞራውያን ከኖህ የልጅ ልጅ ከከነዕን የተገኘ ሃያል ህዝብ ነበሩ፤


አሞን፣አሞናውያን፣አሞናዊት

“የአሞን ሕዝብ” ወይም ፣ “አሞናውያን” ከነዓን ውስጥ ከነበሩት ሕዝቦች አንዱ ናቸው።ሎጥ ከትናሿ ልጁ የወለደው የቤን አሚ ዘር ናቸው።


አሞጽ

አሞጽ በይሁዳ ንጉስ በዕዝያን ዘመን የነበረ እስራኤላዊ ነብይ ነበር፤


አሞጽ

የነቢዩ ኢሳይያስ አባት አሞጽ ይባል ነበር።


አሦር፥ አሦራዊ፥ የአሦር መንግሥት

አሦር እስራኤል በከነዓን ምድር ይኖሩ በነበሩበት ዘመን በጣም ኅያል መንግሥት ነበር። የአሦር መንግሥት በአሦር ንጉሥ ይተዳደሩ የነበሩ አገሮች ናቸው።


አረቢያ፤ አረባዊ

አረቢያ፥3000000 ስኩዬር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የዓለማችን ትልቁ ባሕር ገቡ፤አካባቢ ነው ከእስኤል ደቡብ ምስራቅ ያለ ቦታ ሲሆን ከቀይ ባሕር ከአረቢያ ባሕርና ከፋርስ ባሕር ሰላጤ ጋር ይዋስናል።


አራም፤አራማዊ ፤አራማይክ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ አርም የሁለት ሰዎች ስም ነው፤የአሁኑ ሲሪያ ያለችበት ከከነዓን ሰሜን ምስራቅ ያለው አካባቢ ስም ነው፤


አራራት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “አራራት” ለአንድ አካባቢ፥ ለአንድ መንግሥትና የተራራ ሰንሰለት የተሰጠ ስም ነው።


አርሞንዔም ተራራ

አርሞንዔም ተራራ እስራኤል ውስጥ ካሉ ተራሮች በጣም ረጁም ነው።


አርጤክስስ

አርጤክስስ ሃያ ዓመት የጥንቱን ፋርስ/ኢራቅ የገዛ ንጉሥ ነበር።


አርጤክስስ

አርጤክስስ ከ 464-424 ዓቅክ የፋርስን መንግሥት ሲገዛ የነበረ ንጉሥ ነው


አሮን

አሮን የሙሴ ታላቅ ወንድም ነበር። የእስራኤል ሕዝብ የመጀመሪያ ሊቀ ካህን እንዲሆን እግዚአብሔር አሮንን መረጠ።


አሳ

አሳ ክ913-873 አቅክ ድረስ ለአርባ ዓመት የይሁዳን መንግሥት የገዛ ንጉሥ ነበር


አሳፍ

አሳፍ ሌዋዊ ካህን ሲሆን፥ ለንጉሥ ዳዊት መዝሙሮች ሙዚቃ ያዘጋጀ ጥሩ ስጦታ ያለው ሙዚቀኛ ነበር። አሳፍ የራሱን መዝሙሮችም ጽፎአል


አሴር

አሴር የያዕቆብ ስምንተኛ ልጅ ነው። የእርሱ ዘሮች ከአሥራ ሁሉቱ የእስራኤል ነገድ አንዱ ሆኑ፤ ዘሮቹም “አሴር” ተብለው ይጠራሉ።


አስቀሎና

በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን አስቀሎና ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ የምትገኝ ዋና የፍልስጥኤማውያን ከተማ ነበርች። ዛሬም እስራኤል ውስጥ ትገኛለች።


አስቆሮቱ ይሁዳ

የአስቆሮቱ ይሁዳ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር። ለአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠ እርሱ ነበር።


አስቴር

አይሁድ በባቢሎን በምርኮ በነበሩበት ዘመን የፋርስ መንግሥት ልዕልት የሆነች አይሁዳዊት ሴት ናት።


አስጢን

ከመጽሐፈ አስቴር እንደምንመለከተው አስጢን የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ሚስት ነበረች።


አሼራ፥ የአሼራ ምስል፥ አስታሮት

አሼራ በብሉይ ኪዳን ዘመን ከነዓናውያን ያመልኳት የነበሩ ጣዖት ነበረች። “አስታሮት” ሌላው የአሼራ ስም ነው፥ ወይም ደግሞ ተመሳሳይ የሆነች ሌላ ጣዖት ስም ሊሆን ይችላል።


አሽዶድ አዛጦን

አሽዶድ ከአምስቱ በጣም ጠቃሚ የፍልስጥኤም ከተሞች አንዷ ነበረች። ሜድትራኒያን ባሕር አጠገብ ከከነዓን ደቡብ ምዕራብ፥ በጋዛና በኢዮጴ መካከል ግማሽ ርቀት ላይ ነበር የምትገኘው


አቂላ

አቂላ ከጥኩር በቀር ደቡባዊ ባሕር ዳርቻ ከነበረው ጻንጦስ አውራጃ የነበረ አየሁዳዊ ነበር፤


አቃሮን

አቃሮን የፍልስጥኤማውያን ዋነኛ ከተማ ሲሆን የሚገኘው ከሜድትራንያን ባሕር ዘጠኝ ማይል ገባ ብሎ ያለ ቦታ ላይ ነበር።


አቢሜሌክ

አብርሃምና ይስሐቅ በከነዓን ምድር በሚኖሩበት ዘመን አቢሜሌክ በጌራራ አካባቢ የነገሠ ንጉስ ነበር ።


አቢያ

ከ 915- 913 ዓቅክ ነግሦ የነበር የይሁዳ ንጉሥ ስም ነው እርሱ የንጉሥ ሮብዓም ልጅ ነበር። ብሉይ ኪዳን ውስጥ አቢያ የሚል ስም የሚታወቁ ሌሎች ጥቂት ሰዎችም ነበሩ።


አቤል

አቤል የአዳምና የሔዋን ሁለተኛ ልጅ ነበር። እርሱ የቃየል ታናሽ ወንድም ነበር።


አቤሴሎም

አቤሴሎም የዳዊት ሦስተኛ ወንድ ልጅ ነበር። በቁንጅናውና በቁመናው እንዲሁም በጣም ቅብጥብጥ በመሆኑ ይታወቃል።


አቤኔር

አቤኔር የንጉሥ ሳኦል አጎት ልጅ ነበር።


አብርሃም፣ አብራም

አብራም የእስራኤላውያን አባት እንዲሆን እግዚአብሔር የመረጠው ከዑር ከተማ የመጣ ከለዳዊ ነበር። በኋላ ላይ እግዚአብሔር “አብርሃም” በማለት ስሙን ለውጦታል።


አብያታር

በንጉሥ ዳዊት ዘመን አብያታር የእስራኤል ሕዝብ ሊቀ ካህን ነበር።


አብድዩ

አብድዩ በንጉሥ ሕዝቅያስ ዘመን ከነበሩ የእስራኤል ነቢያት አንዱ ነበር።


አናንያ

ከትንቢተ ዳንኤል እንደምንመለከተው አናንያ በምርኮ ዘመን ወደ ባቢሎን ተወስደው ስለነበሩ አስተዋይ አይሁዳውያን ወጣቶች አንዱ ነበር። ይበልጥ የሚታወቀው ሲድራቅ በተሰኘው ስሙ ነው።


አንጾኪያ

አዲስ ኪዳን ውስጥ አንጾኪያ የሁለት ከተሞች ስም ነበር፤አንደኛው ሜድትርያን ባሕር ዳርቻ አጠገብ በሶሪያ ነበር፤ሌላው ግን ቆላስያስ ከተማ አጠገበ በነረው ጺስዲያ ነበር።


አኪያ

አኪያ ብሉይ ኪዳን ውስጥ የተለያዩ ሰዎች ስም ነው። የሚከተሉት ከእነዚህ ሰዎች ጥቂቶቹ ናቸው፣


አካዝ

አካዝ ከ732 ዓቅከ - 716 ዓክከ የይሁዳን መንግሥት የገዛ በጣም ክፉ ንጉሥ ነበር። ይህ ይሆነው በእስራኤልና በይሁዳ የነበሩ ብዙ ሰዎች በምርኮ ወደ ባቢሎን ከመወሰዳቸው 140 ዓመት በፊት ነበር።


አካዝያስ

አካዝያስ የሁለት ንጉሦች ስም ነው፤አንደኛው የእስራኤል መንግሥት ስገዛ ሌላው የይሁዳን መንግሥት ገዛ።


አክዓብ

አክዓብ ከ 875-854 ዓቅክ ስሜናዊ የእስራኤል መንግሥት ላይ ነግሦ የነበረ በጣም ክፉ ንጉሥ ነው።


አዛርያስ

በብሉይ ኪዳን ውስጥ አዛርያስ በሚባል ስም የታወቁ ሰዎች ነበሩ


አዳም

አዳም እግዚአብሔር የፈጠረው የመጀመሪያ ሰው ነው።እርሱና ሚስቱ ሔዋን በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ተፈጥረዋል።


አዶንያስ

አዶንያስ የንጉሥ ዳዎት አራተኛ ልጅ ነው።


አጋር

አጋር የሦራ አገልጋይ ነበረች።


አጽሎስ

አጽሎስ ግሪክ ዉስጥ ከነበረው እስክንድሪያ የመጣ ስለ እየሱስ ለሰወች ለማስተማር ልዩ ችሎታ የነበረው አይሁዳዊ ነበር።


አፍራታ፥ የኤፍራታ ሰው

አፍራታ በሰሜኑ የእሥራኤል ክፍል የሚገኝ የአንድ ከተማ ስም ነበር።


ኢሳይያስ

ኢሳይያስ የእግዚአብሔር ነቢይ ነበር።


ኢቆንዮን

ኤቄንዮን ደቡብ ማዕከላዊ እስያ ውስጥ (አሁን ቱርክ ያለችበት) የምትገኝ ከተማ ነበረች።


ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያዊ

ኢትዮጵያ ከግብፅ በስተደቡብ ያለች አፍሪካዊት አገር ስትሆን፣ በስተምዕራብ የአባይ ወንዝ፣ በስተምሥራቅ ደግሞ ከቀይ ባሕር ጋር ትዋሰናለች። ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ ሰው ኢትዮጵያዊ ይባላል።


ኢየሩሳሌም

ኢየሩሳሌም በኋላ እጅግ ተፈላጊ የሆነች በመጀመሪያ የከነዓናውያን የነበረች ጥንታዊት ከተማ ነበረች። አሁንም ኢየሩሳሌም የዘመናዊት ኢየሩሳሌም ዋና ከተማ ነች።


ኢዩ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዩ ተብለው የሚጠሩ ሁለት ሰዎች አሉ።


ኢያሪኮ

ኢያሪኮ በተስፋው ምድር በከነዓን የነበረች በጣም ኅያል ከተማ ነበረች።


ኢያሱ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢያሱ በመባል የሚታወቁ በርካታ ሰዎች አሉ። በጣም ታዋቂው የነዌ ልጅና የሙሴ ረዳት የነበረው በኋላም የእግዚአብሔር ሕዝብ ሁነኛ መሪ የሆነው ኢያሱ ነበር።


ኢያቡሳዊ

ኢያቡሳውያን፤ ያቡስ ከሚባል ሰው የተወለዱ በከነዓን የነበሩ ነገድ ናቸው።


ኢይዝራኤል

ኢይዝራኤል ከጨው ባሕር ደቡብ ምዕራብ ነገድ ክልል ውስጥ የነበረች በጣም ጠቃሚ የእስራኤል ከተማ ስም ነው። ጥቂት የእስራኤል ንጉሦች ቤተመንግሥታቸውን የሠሩት እዚያ ነበር።


ኢዮራም

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮራም ተብለው የሚጠሩ ሁለት ንጉሦች ነበሩ።


ኢዮራም

ኢዮራም የእስራኤል ንጉሥና የአክዓብና የኤልዛቤል ልጅ ነበር።


ኢዮርብዓም

የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም ከ900-910 ዓቅክ ገደማ የሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት የመጀመሪያው ንጉሥ ነበር። ኢዮርብዓም የሚባል ሌላው ንጉሥ የኢዮአስ ልጅ ሲሆን ከ120 ዓመት በኋላ እስራኤልን ገዝቷል። አንዳንዴ፣ “ቀዳማዊ ኢዮርብዓም” እና “ዳግማዊ ኢዮርብዓም” ይባላሉ።


ኢዮሳፍጥ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮሳፍጥ ቢያንስ የሁለት ሰዎች ስም ነበር።


ኢዮስያስ

ኢዮስያስ ለሰላሳ እንደ ዓመት የይሁዳን መግሥት የገዛ እግዚአብሔርን የሚፈራ ንጉሥ ነበር። ሕዝቡ በንስሐ እንዲመለሱና ያህዌን እንዲያመልኩ ለማበረታታት ብዙ ነገሮች አድርጓል።


ኢዮብ

ኢዮብ፣ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅና በደል የሌለበት እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገርለት ሰው ነው። የበለጠ የሚታወቀው ታላቅ ስቃይና ሐዘን ቢደርስበትም በእግዚአብሔር በነበረው እምነት በመጽናቱ ነበር።


ኢዮአስ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮአስ ተብለው የሚጠሩ ጥቂት ሰዎች ነበሩ።


ኢዮአቄም

ኢዮአቄም የይሁዳን መንግሥት ከገዙ ንጉሦች አንዱ ነበር።


ኢዮአቄም

ኢዮአቄም ከ60 ዓቅክ ጀምሮ በይሁዳ መንግሥት ላይ የነገሠ በጣም ክፉ ነጉሥ ነበር። እርሱ የንጉሥ ልጅ ነበር። መጀመሪያ ላይ ኤልያቄም ይባል ነበር።


ኢዮአብ

ኢዮአብ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ የንጉሥ ዳዊት ሁነኛ የጦር መሪ ነበር።


ኢዮአታም

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮአታም ተብለው የሚጠሩ ሦስት ሰዎች አሉ።


ኢዮኤል

ኢዮኤል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለውን ትንቢተ ኢዮኤል የጻፈ ነብይ ነበር፤ ትንቢተ ኢዮኤል የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ክፍል ከሆኑት አሥራ ሁለት አጫጭር ትንቢቶች አንዱ ነው።


ኢዮጴ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ኢዮጴ ከተማ ከኢየሩሳሌም ሰሜናዊ ምዕራብ 30 ማይሎች ርቃ ሜድትራንያን ባሕር ላይ የምትገኝ በጣም ጠቃሚ የንግድ ባሕር ወደብ ነበረች።


ኤላም

ኤላም የሴም ልጅ፣ የኖኅ የልጅ ልጅ ነው።


ኤልሳቤጥ

ኤልሳቤጥ የመጥምቁ ዮሐንስ እናት ናት። የባልዋ ስም ዘካርያስ ነበር።


ኤልሳዕ

ኤልያስ አክዓብን፣ አካዝያን፣ ኢዮራምን፣ ያሑን፣ ኢዮአስንና ዮአስን በመሳሰሉ በርካታ የእስራኤል ነገሥታት ዘመን ነበር ያገለገለው።


ኤልዛቤል

ኤልዛቤል ዐመፀኛዋ የእስራኤል ንጉሥ የአክአብ ሚስት ነበረች።


ኤልያስ

ኤልያስ በጣም ታዋቅ ከሆኑት የያህዌ ነቢያት አንዱ ነበር። ንጉሥ አክዓብን ጨምሮ ኤልያስ በተለያዩ የእስራኤል ወይም የይሁዳ ነገሥታት ዘመን ነበር ያገለገለው።


ኤልያቄም

ኤልያቄም የሁለት የብሉይ ኪዳን ሰዎች ስም ነው።


ኤሞር

ኤሞር አይሁዳዊ ያልነበረ የያዕቆብ ጎረቤት የነበረ ሰው ነው።


ኤርምያስ

ኤርምያስ በይሁዳ መንግሥት የእግዚአብሔር ነብይ ነበር።


ኤሳው

ኤሳው ይስሐቅ ከርብቃ ከወለደቻቸው መንታ ልጆች ታላቁ ነበር፣ መንታ ወንድሙ ያዕቆብ ነበር።


ኤዊያውያን

ምድሪቱን እንዲወርሱ ኢያሱ እስራኤላውያንን እየመራ በወሰደ ጊዜ ኤዊያውያን በከነዓን ምድር ከነበሩ ሰባት ዋና ዋና ሕዝቦች አንዱ ነበሩ።


ኤደን፣ ኤደን ገነት

በጥንት ዘመን ኤደን እግዚአብሔር የመጀመሪያውን ወንድና ሴት ያኖረበት የአትክልት ቦታ ያለው አካባቢ ነበር።


ኤዶም፣ ኤዶማዊ፣ ኤዶሚያ፣ ሴይር፣ ቴማን

ኤዶም፣ የኤሳው ሌላው ስም ሲሆን፣ ኤዶማውያን የእርሱ ዘሮች ናቸው። የኤዶም አገር ኤዶምያ ወይም ሴይር በመባልም ይታወቃል።


ኤፌሶን

ኤፌሶን በአሁኑ ዘመን ቱርክ በምትባለው አገር ምዕራባዊ ባሕር ዳርቻ የነበረች ጥንታዊ የግሪክ ከተማ ነበረች።


ኤፍራጥስ

ኤፍራጥስ በኤደን የአትክልት ቦታ ውስጥ ያልፉ ከነበሩ አራት ወንዞች አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተደጋጋሚ የተጠቀሰ ወንዝ ነው፣ አንዳንዴ፣ “ወንዙ” በመባል በአጭር ቃል ተጠርቷል።


ኤፍሬም

ኤፍሬም የዮሴፍ ሁለተኛ ልጅ ነው። የእርሱ ዘር የሆኑት ኤፍሬማውያን አስራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ከተሰባሰቡባቸው አንዱ ሆኗል።


እሴይ

እሴይ የቦዔዝ የልጅ ልጅና የንጉሥ ዳዊት አባት ነው።


እስማኤል

እስማኤል የአብርሃምና የሥራ አገልጋይ የነበረችው የአጋር ልጅ ነው።


እስያ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፥ “እስያ” የሮም መንግሥት አውራጃ ስም ነበር። በአሁኑ ጊዜ ቱርክ ከሚባለው አገር ምዕራባዊ ክፍል ነበር የሚገኘው።


እስጢፋኖስ

እስጢፋኖስ የመጀመሪያው ክርስቲያን ሰማዕት ማለትም በኢየሱስ በማመኑ የተገደለ የመጀመሪያ ሰው በመሆኑ ይበልጥ ይታወቃል። ሕይወቱንና አሟሟቱን የሚያመለክት ዝርዝር ሐዋርያት ሥራ የተሰኘው መጽሐፍ ውስጥ ተጽፏል


እንድርያስ


ኦርዮን

ኦርዮን ጻድቅ ሰውና ከንጉሥ ዳዊት ምርጥ ወታደሮች አንዱ ነበር።


ከለድ፣ ከለዳዊ

ከለድ የመስጶጤምያ ወይም የባቢሎን ደቡባዊ ክፍል የነበረ ቦታ ነበር። በዚህ ቦታ የነበሩ ስዎች ከለዳውያን ይባሉ ነበር።


ከሊታውያን

ከሊታውያን ምናልባት የፍልስጥኤም አካል የነበሩ ሕዝብ ነበሩ።


ከነዓን፣ ከነዓናዊ

ከነዓን የኖኅ ወንዶች ልጆች አንዱ የነበረው የካም ልጅ ነበር። ከነዓናውያን የከነዓን ዘሮች ናቸው።


ኩሽ

ኩሽ የኖኅ ልጅ ካም ትልቁ ልጅ ነበር። የናምሩድ ጥንተ አባትም ነበር። ሁለቱ ወንድሞቹ ግብፅና ከነዓን ነበር።


ኪልቅያ

ኪልቅያ አሁን የዘመኑ ቱርክ ካለችበት ደቡብ ምሥራቃዊ ክፍል የነበረች አነስተኛ የሮማውያን አውራጃ ነበረች። ከኤጂያን ባሕር ጋር ይዋሰናል።


ካሌብ

ካሌብ የከነዓንን ምድር እንዲሰልሉ ሙሴ ከላካቸው አሥራ ሁለት እስራኤላውያን አንዱ ነበር።


ካም

ካም ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከተጠቀሱት ሦስቱ የኖኅ ልጆች ሁለተኛው ነው።


ኬልቅያስ

ኬልቅያስ በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን የነበረ ሊቀ ካህን ስም ነው።


ኬብሮን

ኬብሮን ከኢየሩሳሌም ደቡብ 20 ማይሎች ርቀት ላይ ያለች ከፍታ ያለው ዐለታማ ኮረብታላይ የምትገኝ ከተማ ናት።


ኬጢያዊ

ኬጢያውያን በልጁ በከነዓን በኩል የካም ዘሮች ነበር። በአሁኑ ዘመን ቱርክ በሚባለውና ከፐስቲና በስተ ሰሜን ባለው አካባቢ ታላቅ መንግሥት ሆነው ነበር።


ኮሬብ

የኮሬብ ተራራ አሥሩ ትእዛዞች የተጻፈባቸው ሁለት የድንጋይ ጽላቶችን እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠበት የሲና ተራራ ሌላ ስም ነው።


ዐባይ ወንዝ፣ የግብፅ ወንዝ

ዐባይ ወንዝ በሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ በጣም ረጅምና ሰፊ ወንዝ ነው።


ዑር

ዑር በጥንቱ ከለድያ አካባቢ ኤፍራጥስ ወንዝ ዳር የነበረ ጠቃሚ ከተማ ሲሆን የሚገኘው በዚህ ዘመን ኢራቅ በሚባለው አገር ውስጥ ነው።


ዓረባ

በብሉይ ኪዳን ዘመን ዓረባ የሚለው አገልላለጽ በዮርዳኖስ ወንዝ ዙሪያ በስትደቡብ ወደ ሰሜናዊ የቀይ ባህር ጫፍ የሚዘረጋ የነበረውን ሸለቆ ጨምሮ በጣም ስራ በረሐ ለጥ ያለ ሜዳ ያመለክታል።


ዓይንጋዲ

ዓይንጋዲ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምሥራቅ ይሁዳ ምድረ በዳ ላይ የምትገኝ ከተማ ስማ ነው።


ዕንባቆም

ዕንባቆም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት የነበረ የብሉይ ኪዳን ነቢይ ነው።


ዕዝራ

ዕዝራ እስራኤላዊ ካህንና የአይሁድ ሕግ ሊቅ ነበር፤ ለ70 ዓመት በባቢሎን ምርኮ ከኖሩ በኋላ ወደኢየሩሳሌም የተመለሱ እስራኤላውያንን ታሪክ በጽሁፍ ያሰፈረ እርሱ ነበር።


ዖምሪ

ዖምሪ በኋላ ስድስተኛው የእስራኤል ንጉሥ የሆነ የጦር አዛዥ ነበር።


ዖዝያ፣ አዛርያስ

በ800 ዓቅክ ዖዝያ በ16 ዓመቱ የይሁዳ ንጉሥ ሆነ፤ ለ52 ዓመት በኢየሩሳሌም ነገሠ፤ ይህ በጣም ረጅም ዘመን ነበር። ዖዝያ “አዛርያስ” ተብሎም ይጠራል።


ዘሩባቤል

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዘሩባቤል ተብለው የተጠሩ ሁለት ሰዎች ነበር።


ዘብዴዎስ

ዘብድዎስ ዓሣ አጥማጅ የገሊላ ሰው ነበር። ያዕቆብና ዮሐንስ የተባሉ ሁለት ልጆቹ አብረውት ይሠሩ ነበር። በኋላ ግን ሥራቸውን ትተው ሁለቱም የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ።


ዘካርያስ - (አዲስ ኪዳን)

ዘካርያስ በኋላ መጥምቁ ዮሐንስን የወለደ የአይሁድ ካህን ነበር።


ዘካርያስ (ብሉይ ኪዳን)

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዘካርያስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ሰዎች ነበሩ። ከእነርሱም ዋና ዋናዎቹ፣


ዘኬዎስ

ዘኬዎስ የኢያሪኮ ሰው ሲሆን፣ በጣም የሚታወቀው ኢየሱስን ለማየት ዛፍ ላይ በመውጣቱ ነው።


ዘዓር

ዘዓር እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን ሲያጠፋ ሎጥ ሮጦ ያመለጠባት ትንሽ ከተማ ነበረች።


ዛብሎን

ዛብሎን የያዕቆብና የልያ የመጨረሻ ልጅ ሲሆን፣ ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች የአንዱ ስም ነበር።


የእስራኤል መንግሥት

ንጉሥ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ እስራኤላውያን በሁለት መንግሥታት ተከፈሉ። የእስራኤል መንግሥት አሥሩን ነገዶች የያዘው ሰሜናዊ መንግሥት ነበር።


የእግዚአብሔር ሰው

የእግዚአብሔር ሰው የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር የያህዌ ነቢይ በአክብሮት የሚጠራበት ቃል ነው።


የዳዊት ቤት

“የዳዊት ቤት” የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር የንጉሥ ዳዊትን ቤተ ሰብ ወይም ዘር ያመለክታል።


የዳዊት ከተማ

“የዳዊት ከተማ” የኢየሩሳሌምና የቤተልሔም ሌላው ስም ነው።


የገሊላ ባሕር

የገሊላ ባሕር ምሥራቃዊ እስራኤል ያለ ሐይቅ ነው። የገሊላ ባሕር በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ወደ ደቡብ ከዚያም ወደ ሙት ባሕር ይፈስሳል።


የጨው ባሕር፣ ሙት ባሕር

ሙት ባሕር ተብሎም የሚጠራው የጨው ባሕር የሚገኘው በምዕራብ በኩል ከእስራኤል በስተደቡብና በምሥራቅ በኩል ከሞአብ መካከል ነው


ያዕቆብ (የኢየሱስ ወንድም)

ያዕቆብ የማርያምና የዮሴፍ ልጅ ሲሆን፣ ከኢየሱስ ግማሽ ወንድሞች አንዱ ነበር።


ያዕቆብ (የእልፍዮስ ልጅ)

የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር።


ያዕቆብ (የዘብዴዎስ ልጅ)

የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር። ዮሐንስ የሚባል ታናሽ ወንድም የነበሩት ሲሆን፣ እርሱም ከኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር።


ያዕቆብ፣ እስራኤል

ያዕቆብ የይስሐቅና የርብቃ ታናሹ መንታ ልጅ ነው።


ያፌት

ያፌት ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከተጠቀሱት ሦስቱ የዮኅ ልጆች አንዱ ነው።


ይሁዳ

ይሁዳ የያዕቆብ አራተኛ ልጅ ነው እናቱ ልያ ትባላለች።


ይሁዳ

“ይሁዳ” የሚለው ቃል የመጣው ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ከነበረው ይሁዳ ከሚለው ስም ነው። ጠበብ ባለና ሰፋ ባለ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

ተርጓሚዎቹ ልዩነቱን በጣም ግልጽ ማድረግ ከፈለጉ፣ ሰፋ ባለ መልኩ የቀረበውን ይሁዳ (ለምሳሌ ሉቃስ 1፥5) “የይሁዳ አገር” በማለት መተርጎም ይችላሉ፤ ጠበብ ባለ መልኩ (ለምሳሌ ሉቃስ 1፥39) ጥቅም ላይ ከዋለ፣ ይህ ቦታ መጀመሪያ የይሁዳ ነገድ የነበረበት የጥንቱ የእስራኤል ምድር አካል ስለነበር፣ “የይሁዳ ክፍለ ሀገር” በማለት መተርጎም ይቻላል።


ይሁዳ፣ የያዕቆብ ልጅ

የያዕቆብ ልጅ ይሁዳ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ደቀመዛሙርት አንዱ ነበር። ይኸኛው ከአስቆሮቱ ይሁዳ የተለየ መሆኑን ልብ በሉ።


ይሁዳ፣ የይሁዳ መንግሥት

የአይሁድ ሕዝብ የሚለማመደውን ሃይማኖት ማለትም የአይሁድ ሃይማኖትን ለማመልከት አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ዘመን አንስቶ እስከዚህ ዘመን ድረስ፣ “ይሁዲ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።


ይሳኮር

ይሳኮር የያዕቆብ ማለትም የእስራኤል ዘጠነኛ ልጅ ነው።


ይስሐቅ

ምንም እንኳ በጣም ያረጁ ቢሆኑም ለእነርሱ እንደሚሰጣቸው እግዚአብሔር ለአብርሃምና ለሣራ ቃል የገባላቸው ልጅ ነው።


ዮሐንስ (ሐዋርያው)

ዮሐንስ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት እንዱ ነበር፤ ከኢየሱስ የቅርብ ወዳጆችም አንዱ ነበር።


ዮሐንስ (መጥምቁ)

ዮሐንስ የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ነበር። ዮሐንስ የተሰኘው ስም በጣም የተለመደ ከመሆኑ የተነሳ ሐዋርያው ዮሐንስን ከመሳሰሉ ዮሐንስ ከተባሉ ሌሎች ሰዎች እርሱን ለመለየት፣ “መጥምቁ ዮሐንስ” ተብሏል።


ዮሐንስ (ማርቆስ)

ዮሐንስ ማርቆስ በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር ከተጓዙ ሰዎች አንዱ ሲሆን፣ ማርቆስ ተብሎ ይጠራል።


ዮርዳኖስ ወንዝ

ዮርዳኖስ ወንዝ ከሰሜን ወደደቡብ፣ ከነዓን ተብሎ ይጠራ ከነበረው ምድር ምሥራቃዊ ድንበር ይፈስ የነበረ ወንዝ ነው።


ዮሴፍ (ብሉይ ኪዳን)

ዮሴፍ የያዕቆብ አሥራ አንደኛ ልጅ ሲሆን፣ ለራሔል ደግሞ የመጀመሪያ ልጇ ነበር።


ዮሴፍ (አዲስ ኪዳን)

ዮሴፍ የማርያም እጮኛ የነበረ ሲሆን፣ እንደ አባት ኢየሱስን አሳድጓል።


ዮቶር፣ ራጉኤል

ዮቶር እና ራጉኤል የተሰኙት ስሞች የሚያመለክቱት የሙሴን ሚስት የሴፎራን አባት ነው። ራጉኤል የጎሳው ስም ሊሆን ይችላል።


ዮናስ

ዮናስ በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ እስራኤላዊ ነቢይ ነበር።


ዮናታን

ዮናታን ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል። ትርጉሙ፣ “ያህዌ ሰጥቷል” ማለት ነው።


ዮዳሔ

ዮዳሔ ንጉሥ ለመሆን እስከበቃበት ድረስ የንጉሥ አካዝያስን ልጅ ኢዮአስን ደብቆ ያቆየውና የተከላከለለት ካህን ነበር።


ዮፍታሔ

ዮፍታሔ የእስራኤል መስፍን ወይም ገዢ በመሆን ያገለገለ ከገለአድ የመጣ ጦረኛ ነበር።


ደሊላ

ደሊላ ሚስቱ ባትሆንም ሳምሶን ወዶአት የበረች ፍልስጥኤማዊት ናት።


ደማስቆ

ደማስቆ ሶርያ የሚባለው አገር ዋና ከተማ ነው። ዛሬም ቢሆን መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የነበረበት ቦታ ላይ ነው ያለው።


ደብረ ዘይት ተራራ

ደብረ ዘይት ተራራ ከኢየሩሳሌም ከተማ በስተ ምሥራቅ በኩል ያለ ተራራ ወይም ረጅም ኮረብታ ነው። ይህን ስሙን ያገኘው በብዛት እዚያ ከሚገኙት የወይራ ዛፎች ሊሆን ይችላል።


ደንገል፣ ቄጤማ

“ደንገል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ውሃ ውስጥ፣ ብዙውን ጊዜም ወንዝ ወይም ምንጭ ዳር የሚበቅል ረጅም አገዳ ያለው ተክል ነው።


ዳርዮስ

ዳርዮስ የበርካታ የፋርስ ነገሥታት ስም ነው። “ዳርዮስ” የማንነት መገለጫ እንጂ መጠሪያ ስም አይደለም።


ዳን

ዳን አምስተኛው የያዕቆብ ልጅ ሲሆን ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ነበር። የዳን ነገድ ይኖርበት የነበረው ሰሜናዊው የከነዓን ክፍል በዚህ ስም ይጠራል።


ዳንኤል

ዳንኤል ገና ወጣት እያለ በ600 ዓቅክ በባቢሎን ነጉሥ ናቡከደነፆር በምርኮ የተወሰደ እስራኤላዊ ነቢይ ነበር።


ዳዊት

ዳዊት እግዚአብሔርን በመውደዱና እርሱን በማገልገሉ የታወቀ ሁለተኛው የእስራኤል ንጉሥ ነው። የመዝሙራት መጽሐፍ ዋናው ጸሐፊም እርሱ ነው።


ገለዓድ

ገለዓድ የጋድ፣ የሮቤልና የምናሴ ነገዶች የነበሩበት ከዮርዳኖስ ወንዝ ምሥራቅ የነበረ ተራራማ አካባቢ ስም ነው።


ገሊላ፣ ገሊላዊ

ገሊላ ከሰማርያ እንኳ በጣም ርቆ ሰሜናዊ የእስራኤል ጫፍ አካባቢ ነበረች።


ገላትያ

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ገላትያ በአሁኑ ዘመን ማዕከላዊ ቱርክ የሚባለው ቦታ ላይ ትገኝ የነበረች የሮም ከተማ ነበረች።


ገባኦን፣ ገባኦናውያን

ገባኦን፣ ገባኦናውያን የሚኖሩባት ምድረ ከነዓን ውስጥ የነበረች ከተማና አካባቢ ናት።


ገብርኤል

ገብርኤል ከእግዚአብሔር መላእክት የአንዱ ስም ነው።


ጊብዓ

ጊብዓ ከኢየሩሳሌም በስተ ሰሜንና ከቤቴል በስተ ደቡብ የነበረ ከተማ ስም ነው።


ጋዛ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጋዛ የሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ፣ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምዕራብ 77 ኪሎ ሜትር፣ ከአሽዶድ በስተ ሰሜን 38 ኪሎ ሜትር ላይ ትገኝ የነበረች በጣም አስፈላጊ የፍልስጥኤማውያን ከተማ ነበረች።


ጋይ

በብሉይ ኪዳን ዘመን ጋይ ከቤቴል በስተ ደቡብ ከኢያሪኮ ሰሜን ምዕራብ 8 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የምትገኝ የከነዓናውያን ከተማ ስም ነበረች።


ጋድ

ጋድ ከያዕቆብ ማለትም ከእስራኤል ልጆች የአንዱ ስም ነው። የጋድ ቤተሰብ ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ሆነዋል።


ጌልጌላ

ጌልጌላ ከኢያሪኮ በስተ ሰሜን ያለች አገር ስትሆን፣ ወደ ከነዓን ለመግባት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ወንዝ ከተሻገሩ በኋላ የሰፈሩባት የመጀመሪያ ቦታ ናት።


ጌሣም

ጌሣም ከግብፅ ሰሜናዊ ክፍል አካባቢ የሚገኝ ቦታ ስም ነበር።


ጌራራ

ጌራራ ምድረ ከነዓን ውስጥ የነበረ ከተማና አካባቢ ሲሆን፣ ከኬብሮን ደቡብ ምዕራብና ከቤርሳቤህ ሰሜን ምዕራብ ይገኝ ነበር።


ጌርሳውያን

ጌርሳውያን የኖኅ ልጅ የካም ልጅ የሆነው የከነዓን ዘሮች ይኖሩበት በነበረው ምድረ ከነዓን የነበሩ ነገድ ናቸው።


ጌሹር

በንጉሥ ዳዊት ዘመን ጌሸር ከገሊላ ባሕር በስተ ምሥራቅ በኩል፣ በእስራኤልና በአራም አገሮች መካከል የነበረች ታናሽ መንግሥት ነበረች።


ጌቴሴማኒ

ጌቴሴማኒ ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ ከቄድሮን ሸለቆ ማዶ፣ ደብረ ዘይት ተራራ አጠገብ ያለ የወይራ ዛፎች የነበሩበት አትክልት ቦታ ነው።


ጌት

ጌት ከአምስቱ የፍልስጥኤም ዋና ዋና ከተሞች አንዷ ነበረች። የምትገኘው ከአቃሮን በስተ ሰሜንና ከአሾዶድና ከአስቄሎና በስተ ምሥራቅ ነበር።


ጌዴዎን

ጌዶዎን እስራኤልን ከጠላቶቻቸው እንዲያድን እግዚአብሔር ያስነሣው እስራኤላዊ ነው።


ግሪክ

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ግሪክ የሮም መንግሥት ግዛት ውስጥ ያለች አገር ነበረች።


ግሪክ፣ ግሪካዊ፣ የግሪክ ባሕል

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ግሪክኛ በግሪክና በመላው የሮም መንግሥት ብዛት መግባቢያ ቋንቋ ነበር፤ የመጀመሪያው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት በግሪክኛ ነበር።


ግብፅ፣ ግብፃዊ

ግብፅ ከአፍሪካ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል፣ ከምድር ከነዓን ደቡብ ምዕራብ የምትገኝ አገር ነች።


ጎልያድ

ጎልያድ ዳዊት በወንጭፍ ድንጋይ የገደለው ግዙፍ ፍልስጥኤማዊ ወታደር ነበር።


ጎልጎታ

“ጎልጎታ” ኢየሱስ የተሰቀለበት ቦታ ስም ነው። ቃሉ የመጣው፣ “የራስ ቅል” ወይም፣ “የራስ ቅል ቦታ” ከተሰኙ የአረማይክ ቃል ነው።


ጎሞራ

ጎሞራ ከባቢሎንያ አካባቢ በስተ ምሥራቅ ባለው በጣም ለም ሸለቆ ውስጥ አንድ ቦታ ላይ የነበረች ከተማ ነበረች።


ጎቶልያ

ጎቶልያ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮራም ሚስት ስትሆን፥ በጣም ክፉ ሴት ነበርች። በክፋቱ የታወቀው የእስራኤል ንጉሥ የዘምሪ የልጅ ልጅ ነበረች


ጠርሴስ

ጠርሴስ በአሁኑ ዘመን ማዕከላዊ ደቡብ ቱርክ ባለበት የሮም ኪልቂያ አውራጃ ውስጥ የነበረች ጥንታዊ ሀብታም ከተማ ናት


ጢሞቴዎስ

ጢሞቴዎስ እርሱ በነበረበት ልስጥራ ከተማ ጳውሎስ ባገለገለ ጊዜ በክርስቶስ ያመነ ወጣት ሰው ነበር። በኋላም ጳውሎስ ባደረገው በርካታ ሐዋርያዊ ጉዞ አብሮት ነበር፤ የአዲስ አማኞች ማኅበረ ሰብ መጋቢ በመሆንም አገልግሏል።


ጢሮስ

ጢሮስ በአሁኑ ዘመን ሊባኖስ በሚባለው ሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ ላይ የነበረች ጥንታዊ የከነዓናውያን ከተማ ናት። የከተማዋ አንድ ክፍል ከባሕሩ ዳርቻ አንድ ኪሎ ሜትር ወደ ውስጥ ገባ ካለው ደሴት ጋር ይያያዛል።


ጢሮአዳ

የጢሮአዳ ከተማ በጥንቱ የሮም እስያ አውራጃ ሰሜን ምዕራብ ባሕር ዳርቻ ትገኝ የነበረች ወደብ ናት።


ጤባርዮስ ቄሳር

ጤባርዮስ ቄሳር ኢየሱ ባገለገለበት ዘመን ይሁዳን እየገዛ የነበረ ሮማዊ ነው። ምንም እንኳ በእርግጥ ንጉሥ ባይሆንም አንዳንዴ “ንጉሥ ሄሮድስ” እየተባለ ይጠራል።


ጲላጦስ

ጲላጦስ ኢየሱስ እንዲገደል የፈረደ ሮማዊ ባለ ሥልጣን ነበር።


ጳርቴ፣ ጳንጦስ

ጳርቴ ወይም ጳንጦስ በሮም መንግሥትና በጥንት ቤተ ክርስቲያን ዘመን የሮም አውራጃ ነበረች። የምትገኘው በአሁኑ ዘመን ቱርክ በሚባለው ሰሜናዊ ክፍል ጥቁት ባሕር ዳርቻ ነበር።


ጳውሎስ፣ ሳውል

ጳውሎስ ለሌሎች ብዙ ሕዝቦች የምሥራቹን ቃል እንዲያደርስ ኢየሱስ የላከው የጥንት ቤተ ክርስቲያን መሪ ነበር።


ጴጥሮስ፣ ስምዖን ጴጥሮስ፣ ኬፋ

እነዚህ ስሞች ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ የነበረው የጴጥሮስ መጠሪያዎች ናቸው። በጥንት ቤተ ክርስቲያን ታዋቂ መሪ ነበር።


ጴጥፍራ

ያዕቆብና ሚስቶቹ እንዲሁም ልጆቹ በከነዓን ምድር በነበሩ ጊዜ ጴጥፍራ የግብፅ ፈርዖን ከፍተኛ ባለ ሥልጣን ነበር። ጴጥፍራ የዘቦች አለቃ ነበር።

ኀይል፣ ኀይላት “ኀይል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብዛኛውን ጊዜ በታላቅ ብርታት ነገሮችን ማድረግን ወይም ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ችሎታን ነው። “ኀይላት” የሚያመለክተው ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ታላቅ ችሎታ ያላቸው ሰዎችን ወይም መናፍስትን ነው።


ጵርስቅላ

ጵርስቅላ ከባልዋ ከአቂላ ጋር በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር አብራ ትሠራ የነበረች የመጀመሪያው መቶኛ ዓመት አይሁዳዊት ክርስቲያን ነበረች።


ፈርዖን፣ የግብፅ ንጉሥ

በጥንት ዘመን ግብፅን ይገዙ የነበሩ ንጉሦችን ፈርዖን ነበር።


ፊልጵስዩስ

ፊልጵስዩስ በጥንቷ ግሪክ ሰሜናዊ ክፍል ትገኝ የነበረች ከተማ ናት።


ፊልጶስ (ሐዋርያው)

ሐዋርያው ፊልጶስ ከመጀመሪያዎቹ አሥራ ሁለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ነበር።


ፊልጶስ (ወንጌላዊው)

በኢየሩሳሌም በነበረችው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ፊልጶስ ለድኾችና ችግረኛ ክርስቲያኖች በተለይም ለመበለቶች ጥንቃቄ እንዳይደርጉ ከተመረጡ ሰባት መሪዎች አንዱ ፊልጶስ ነበር።


ፊንሐስ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ፊንሐስ ተብለው የተጠሩ ሁለት ሰዎች አሉ።


ፊንቂያ

በጥንት ዘመን ፊንቂያ ሜዲትራንያን ባሕር ዳር የምትገኝ በጣም ሀብታም ከተማ ነበረች። የአሁኗ ሊባኖስ ካለችበት ምዕራብ አካባቢ ነበር የምትገኘው።


ፋራን

የፋራን በረሐ ከግብፅ በስተምሥራቅና ከምድረ ከንዓን በስተደቡብ የሚገኝ ምድረበዳ ነበር። ፋራን የሚባል ተራራም ነበር፤ ምናልባትም ይህ ስም የሲና ተራራ ሌላ ስም ሊሆን ይችላል።


ፋርስ፣ ፋርሳውያን

ፋርስ በ550 ዓቅክ ታላቁ ቂሮስ የመሠረተው መንግሥት ነው። ማዕከሉ የነበረው የአሁኗ ዘመን ኢራን ያለችበት ቦታ ላይ ነበር። የፋርስ ነዋሪዎች፣ “ፋርሳውያን” ይባላሉ።


ፌርዛውያን

ፌርዛውያን በፓለስቲና ከነበሩ እስራኤላውያን ጋር ብዙ ውጊያ ያደረጉ፣ “ብሔር” ነበሩ። ስለ ማንነታቸው ወይም የት ይኖሩ እንደ ነበር ምንም ገለጻ አልተሰጠም።


ፌጎር፣ ፌጎር ተራራ፣ ፌጎር በአል

ፌፎር ከጨው ባሕር በስተ ምሥራቅ ሞዓብ ምድር ውስጥ የሚገኝ ተራራ ስም ነው። የሮቤል ነገድ የሚኖረው እዚህ ነበር።


ፍልስጥኤማውያን

ፍልስጥኤማውያን ፍልስጥኤም በመባል በሚታወቀው የሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ የሚኖሩ ሕዝብ ናቸው። የስማቸው ትርጕም፣ “የባሕር ሰዎች” ማለት ነው።


ፍልስጥኤም

ፍልስጥኤም ምድረ ከነዓን ውስጥ በጣም ሰፊ የነበረው አካባቢ ስም ሲሆን፣ የምትገኘው በሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ ነበር።


ፔዳን አራም (ሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ)

ፔዳን አራም ወደ ምድረ ከንዓን ከመሄድ በፊት የአብርሃም ቤተሰብ የነበረበት ቦታ ነው።


Other

ለምጽ፣ ለምጻም

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ለምጽ” የተለያዩ የቆዳ በሽታዎችን ያመለክት ነበር። አንድ ሰው ከእነዚህ የቆዳ በሽታዎች በአንዱ ከተያዘ ርኵስ ተብሎ ይቆጠር ነበር።


ላም፣ ጥጃ፣ ወይፈን፣ ከብት

“ከብት” የሚለው ሳር የሚበሉ በዋነኛነት ደረጃ ለሚሰቱት ሥጋና ወተት ሰዎች የሚያረቧቸው ባለ አራት እግር የእርሻ እንስሳት ናቸው። እንዲህ ካሉት እንስሳት እንስቷ “ላም” ስትባል፣ ተባዕቱ፣ “ወይፈን” ከእነርሱ የሚወለደው፣ “ጥጃ” ይባላል።


ላከ፣ መላክ

“ላከ” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ወደ ሌላ ቦታ እንዲሄድ ማድረግ ማለት ነው። አንድን ሰው፣ “መላክ” አንድን ነገር እንዲያደርግ ወይም አንድን ተልዕኮ እንዲፈጽም መናገር ወይም ማዘዝ ማለት ነው


ሌባ፣ ሌቦች፣ ወንበዴ

“ሌባ” ወይም፣ “ወንበዴ” ገንዘብ ወይም ንብረት ከሌሎች የሚሰርቅ ሰው ነው። በብዙ ቁጥር ሲሆን፣ “ሌቦች” ይሆናል።


ልሳን

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ልሳን” በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞች አሉት።


ልዑል፣ ልዕልት

“ልዑል” የሚባለው የንጉሥ ልጅ ነው። ሌሎችን መሪዎች ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል። “ልዕልት” የንጉሥ ልጅ ናት።


ልዕልት

የአንድ አገር ሴት ገዢ ወይም የንጉሥ ልጅ ልትሆን ትችላለች። ማዳፈን “ማዳፈን” የሚለው ቃል አንድ ነገር ማጥፋት ወይም መርካት የሚፈልግን ነገር ማስቆም ማለት ነው።


ሐሜት

ሐሜት ከሰዎች በስተጀርባ ሆነው እነርሱ በተመለከተ የሚናገሩት አፍራሽና አሉታዊ ቃል ነው። ብዙውን ጊዜ በእንዲህ ያለ መልኩ የተነገረው እውነት ሆኖ አይገኝም።


ሐምራዊ

“ሐምራዊ” የሰማያዊና የቀይ ቅልቅል የሆነ ቀለም ስም ነው። ልብስን በዚህ ቀለም ማቅለም በጣም ውድና ሰፊ ጊዜ የሚጠይቅ በመሆኑ ሐምራዊ ልብስ የሀብት፣ የከበሬታና የንጉሣዊነት ምልክት ተደርጎ ይወሰድ ነበር።


ሐሤት

ሐሤት በደስታን በፍስሐ መሞላት፣ እጅግ በጣም ደስ መሰኘት ማለት ነው፥


ሐሰተኛ ነብይ

ሐሰተኛ ነብይ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ከእግዚአብሔር ያልተቀበለውን መልእክት ከእግዚአብሔር እንደተቀበለ የሚናገር ሰው ነው።


ሕልም

ሕልም ሰዎች ተኝተው እያለ የሚያዩት ወይም አእምሮአቸው ውስጥ የሚለማመዱት ነገር ነው።


ሕዝብ

ሕዝብ የሚባለው በአንድ ዐይነት መንግሥታዊ አስተዳደር የሚመራ የሰዎች ስብስብ ነው። ብዙውን ጊዜ በዘር፣ በነገድ፣ በቋንቋና በሌሎችም ባሕርዮች የሚመሳሰሉ ሰዎችን ያካትታል።


ሕጋዊ

ሕጋዊ የሆነ ነገር አሳሪ ከሆነው ደንብ ወይም ሕግ መሠረት የተደረገ ወይም ከእርሱ ጋር የሚስማማ ማለት ነው።


ሕግ፣ ሥርዐት (መርሕ)

ሕግ ሆን ተብሎ በጽሑፍ የሰፈረና ሥልጣን ባለው አምላክ የሚያስፈጽመው መደበኛ መመሪያ ነው። ሥርዐት (መርሕ) ውሳኔዎችን ለማድረግ መመሪያ ወይም መመዘኛ ነው።


ሕግ፣ አፍራሽ፣ ዐመፃ

“ዐመፃ” ለማንኛውም ሕግ ወይም ደንብ አለመታዘዝ ማለት ነው። ሕግ አፍራሽነት፣ “ዐመፃ” ሊባል ይችላል።


መለመን፣ ልመና

“መለመን” አንድ ነገር እንዲደረግ ወይም እንዲሰጥ አጥብቆ መጠየቅ ማለት ነው። “ልመና” የሚለው የሚያመለክተው የመለመንን ተግባር ነው።


መለመን፥ ለማኝ

“መለመን” አንድን ነገር አጥብቆ መጠየቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ገንዘብ ወይም እንጀራ መጠየቅን ይመለከታል።


መለከት

“መለከት” ሙዚቃ ለመጫወት ወይም ዐዋጅ ለማሰማት ወይም ሕዝብን ለስብሰባ ለመጥራት ጥቅም ላይ የሚውል መሣሪያ ነው።


መለየት፣ የመለየት ችሎታ

“መለየት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድን ነገር መረዳትን በተለይም ያ ነገር ትክክል ወይም ስሕተት መሆኑን በሚገባ መረዳትን ነው።


መልበስ፣ ለበሰ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ከዋ፣ “ለበሰ” አንድ ነገር፣ “ተቀዳጀ” ወይም አንድ ነገር ታጠቀ ወይም በአንዳች ሁኔታ ዝግጁ ሆነ ማለት ነው። አንድ ነገር፣ “መልበስ” አንድ ዐይነት ፀባይ ወይም ባሕርይ አዳበረ ማለት ነው።


መልእክተኛ

መልእክተኛ የሚባለው ለሌሎች የሚናገረው ወይም የሚያደርሰው ነገር የተሰጠው ሰው ነው።


መሐላ

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት አንዳች ነገር ለማድረግ የሚሰጥ ውል ያለው ተስፋ ቃል ነው። መሐላ የሚያደርግ ሰው የሰጠውን ተስፋ የመፈጸም ግዴታ አለበት።


መመለስ

“መመለስ” ወደ ኋላ መመለስ፣ ወይም አንድን ነገር መልሶ መስጠት ማለት ነው።


መመለስ፣ ተመለሰ፣ ወደ ኋላ አለ


መመላለስ

መመላለስ የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ከዋለ፣ “መኖር” ማለት ነው።


መመሪያ

መመሪያ በተወሰነ ማኅበረሰብ ውስጥ ያሉ ሰዎች የሚያከብሩት ሕዝባዊ ደንብ ወይም ትእዛዝና መመሪያ የሚሰጥ ሕግ ነው።


መመደብ፥ ተመደበ

“መመደብ” ወይም፥ “መደበ” የሚለው ቃል የተወሰነ ተግባርን እንዲፈጽም አንድን ሰው መሾምን ያመለክታል


መምራት፣ መመሪያ

“መምራት” እና፣ “መመሪያ” የተሰኙ ቃሎች የሚያመለክቱት አንድን ነገር እንዴት ማድረግ እንደሚቻል ወይም መታዘዝ የሚገባ ሕግን አስመልክቶ ግልጽ የሆነ አቅጣጫ መመልከት ማለት ነው።


መምሰል፣ አምሳል

እርስ በርስ የሚመሳሰሉ ሰዎች ወይም ነገሮች እርስ በርስ የሚጋሩዋቸው ነገሮች ይኖሯቸዋል።


መምሰል፣ አምሳል

እርስ በርስ የሚመሳሰሉ ሰዎች ወይም ነገሮች እርስ በርስ የሚጋሩዋቸው ነገሮች ይኖሯቸዋል።


መምከር

“መምከር” ጠንከር አድርጎ ማስጠንቀቅ ወይም ምክር መስጠት ማለት ነው።


መሠረት፣ መሠረተ

“መሠረተ” የሚለው ግሥ አንድ ነገር ላይ ሠራ ወይም ገነባ ማለት ነው። መሠረት አንድ ሕንፃ የሚያርፍበት ከታች ያለው አካል ነው።


መሣሪያ


መሥዋዕት፣ ቁርባን

“ቁርባን” (ስጦታ) የሚለው ለእግዚአብሔር ወይም ለጣዖት የተሰጠ ማንኛውንም ነገር የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ነው። መሥዋዕት በብዙ መልኩ ይመሳሰላል፤ ሆኖም በተለምዶ ከተገደሉ በኋላ ለእግዚአብሔር ወይም ለጣዖት የሚሰጡ ነገሮችን ያመለክታል


መርዳት፣ የተረዳ

“መረዳት” መረጃ መስማት ወይም መቀበልና ምን ማለት እንደሆነ መገንዘብ ማለት ነው።


መሰናከል

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “መሰናከል” እየተራመዱ ወይም እየሮጡ እያል የመውደቅ ያህል መንገዳገድ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ በአንድ ነገር መደናቀፍን ያመለክታል


መሰናከያ፣ መሰናከያ ዐለት

“መሰናከያ” ወይም፣ “መሰናከያ ድንጋይ” አንድ ሰው ተደናቅፎ እንዲወድቅ የሚያደርግ ነገርን ያመለክታል


መሳም

አንድ ሰው ከንፈሮቹን አጥብቆ ሌላው ሰው ጉንጮች ወይም ከንፈሮች ላይ በማድረግ ፍቅሩን የሚገልጥበት ሁኔታ ነው፥


መሳት፥ ሳተ፥ ወደ ስህተት ተመራ

“መሳት” እና “ሳተ” በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ መመፅ ማለት ነው። “ወደ ስህተት መመራት” ሌሎች ሰዎች ወይም ሁኔታዎች ለእግዚአብሔር ወዳለመታዘዝ እንዲመራቸው መፍቀድ ማለት ነው


መስቀል

አንድን ነገር መስቀል ያንን ነገር ከመሬት በላይ ማንጠልጠል ማለት ነው።


መስበክ

ስለ እርሱ ለማስተማርና ለእርሱ እንዲታዘዙ ለማሳሰብ ለተወሰኑ ሰዎች መናገር ማለት ነው።


መስከር፣ ሰካራም

መስከር የአልኮል መጠጥ አብዝቶ በመጠጣት አእምሮን መሳት ወይም ከተለመደው የተለየ ፀባይ ማሳየት ማለት ነው።


መስጠት (መፈጸም)፣ የተሰጠ (ፈጸመ)፣ ስጦታ

በዚህ አግባብ መሠረት፥ “መስጠት” ሲባል አንድን ነገር ለማድረግ መወሰን ወይም ቃል መግባት ማለት ነው።


መሸከም

ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “መሸከም” አንድን ነገር ራስ ላይ መጫን ማለት ነው። ይህ ቃል በርካታ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።


መሸፈኛ

“መሸፈኛ” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ራስን ለመሸፈን የሚያገለግለውን በጣም ስስ ልብስ ሲሆን፣ ራስና ፊት እንዳይታይ ይከልላል።


መሾም (ዕውቅና መስጠት)

መሾም ሲባል ወግ ባለው ሁኔታ ለተለየ ተግባር ወይም ድርሻ አንድን ሰው መለየት ማለት ነው። በዐዋጅ ደረጃ ሕግን ወይም ደንብን ማሳወቅ ማለትም ይሆናል።


መቀበል

“መቀበል”የሚለው ቃል ለአንድ ሰው ወይም ሁኔታ ተገቢ ዕውቅና ወይም ይሁንታ ሲሰጠው ማለት ነው።


መቀበል

“መቀበል” የተሰጠ ወይም የቀረበ ነገርን ተቀብሎ የራስ ማድረግ ማለት ነው።


መቀደስ፣ ቅድስና

መቀደስ ለአንድ ራሱን ለቻለ ዓላማ ወይም ተግባር አንድን ነገር መለየት ወይም መስጠት ማለት ነው።


መቀጣት፤ቁጣ

‘’መቀጣት’’ ወይም ‘’ቁጣ’’አንድ ነገር ወይም ሰወ ላይ ደስ አለመሰኘት፤መበሳጫትና መናደድ ማለት ነው፤


መቁረጥ

“መቁረጥ” የሚለው ቃል ማግለልን፣ ማስወገድን ወይም ከዋው ወገን መነጠልን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውል የነበረ ፈሊጣዊ ቃል ነው። ከኀጢአት የተነሣ በመልኮታዊ ፍርድ መገደልን ሊያመለክትም ይችላል።


መቃብር፣ የቀብር ቦታ

“መቃብር” እና፣ “የቀብር ቦታ” ሰዎች የሞተውን ሰው አካል የሚያኖሩበት ስፍራ ነው።


መቃተት

“መቃተት” የሚለው ቃል ከአካላዊ ወይም ስሜታዊ ሕመም የተነሣ ከጥልቅ የሚወጣ አጭር ድምፅ ነው። ብዙውን ጊዜ መቃተት የሚገለጠው ያለ ምንም ቃል ነው።


መቃን

አንድን በር ደግፎ የሚይዝ በሩ ግናራ ቀኝ ላይ ያለ ቀጥ ያለ ጣውላ ነው።


መቅለጥ

“መቅለጥ” የሚለው ቃል ሙቀት ሲነካው የአንድ ነገር ፈሳሽ መሆንን ያመለክታል። ምሳሌያዊ በሆነ መልካም ጥቅም ላይ ይውላል።


መቅሠፍት

መቅሠፍት የሚባለው ብዙ ሕዝብ ላይ ጉዳት ወይም ሞት የሚያስከትል በሽታ ወይም ሌላ ሁኔታ ነው።


መቅበር፣ ቀበረ፣ ቀብር፣ መቀበሪያ

“መቅበር” የሞተ ሰውን አካል ጉድጓድ ውስጥ ወይም ሌላ መቀበፊያ ቦታ ውስጥ ማኖርን ያመለክታል። “ቀብር” የሚለው ቃል አንድ ነገር የመቅበር ሥራ ሲሆን፣ አንድን ነገር ለመቅበር የሚያገለግል ቦታንም ያመለክታል።


መቅጣት፣ ቅጣት

“ቅጣት” ከፈጸመው ጥፋት የተነሣ አንድ ሰው ላይ አሉታዊ ውጤቶች ማድረስ ማለት ነው።


መበልጸግ/መከናወን፣ ብልጽግና፣ የበለጸገ

“መበልጸግ” አንድ ሰው ወይም ሕዝብ በሕይወታቸው ሲከናወኑ ወይም የተሳካላቸው ሲሆኑ ማለት ነው። ይህ መከናወን ቁሳዊ ወይም መንፈሳዊ ሊሆን ይችላል። “ብልጽግና” ሀብታምና ደኅና የመሆን ሁኔታ ነው።


መበቀል፥ በቀል፥ ብቀላ

“መበቀል” ወይም፥ “በቀል” እርሱ ላደርሰው ጉዳት ለመክፈል ሲባል አንድን ሰው መቅጣት ማለት ነው። የመበቀያ ወይም በቀል የተፈጸመበት ተግባር “ብቀላ” ይባላል


መበታተን፣ የተበተነ

መበታተን የሰዎችን ወይም የነገሮችን በተለያዩ አቅጣጫ መበታተን ያመለክታል።


መብላት፣ መዋጥ፣ ጨርሶ ማቃጠል

ይህ ቃል የሚያመለክተው በአደገኛ ሁኔታ መብላትን ወይም ጨርሶ ማቃጠልን ነው።


መብራት

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ሰዎች ይጠቀሙበት የነበረው መብራት በሚነድበት ጊዜ ብርሃን የሚሰጥ ብዙውን ጊዜ እንደ ኀይል ሰጪ የሚያገለግል ዘይት የያዘ ዕቃ ነበር።


መብራት መያዣ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መብራት መያዣ” ክፍሉ ውስጥ ሁሉ እንዲያበራ መብራቱ የሚቀመጥበት ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ዕቃ ነው።


መብዛት

“መብዛት” የሚለው በከፍተኛ ደረጃ በቁጥርና በመጠን ማደግን ያመለክታል።


መተርጎም፣ ትርጉም

“መተርጎም” እና፣ “ትርጉም” የተሰኙት ግልጽ ያልሆነ ነገርን መርዳትና ያንን ግልጽ ማድረግን ያመለክታል።


መተኛት፥ ተኛ፣ አንቀላፋ

እነዚህ ቃሎች ከሞት ጋር የሚያያዝ ምሳሌያዊ ትርጉም አላቸው


መታሰቢያ፣ የመታሰቢያ ቁርባን

መታሰቢያ የሚለው ቃል አንድ ሰው ወይም አንድ ሁኔታ እንዲታሰብ የሚያደርግ ተግባር ወይም ነገር ማለት ነው።


መታወቅ፣ የታወቀ

“የታወቀ” የሚለው ቃል ሰፊ ተቀባይነት ማግኘትፍንና ስመ ጥሩ የሆነ ሰውን ያመለክታል።


መታዘዝ፣ ታዛዥ፣ ታዛዥነት

“መታዘዝ” ሥልጣን ያለው ሰው የሚፈልገውን ወይም እንዲደረግ የሚያዝዘውን መፈጸም ማለት ነው። “ታዛዥ” የተነገረውን ወይም የታዘዘውን የሚፈጽም ሰው ነው።


መታደግ፣ ታዳጊ (የሚታደግ)

አንድን ሰው መታደግ እርሱን ማዳን ማለት ነው። ታዳጊ ከባርነት፣ ከጭቆና ወይም ከሌላ አደጋ ሰዎችን የሚታደግ ወይም ነጻ የሚያወጣ ነው።


መታገሥ፣ ትዕግሥት (ጽናት)

መታገሥ ረጅም ጊዜ መቆየት ወይም አስቸጋሪ ነገርን መቋቋም ማለት ነው።


መታጠቂያ

“መታጠቂያ” የሚለው ቃል አንዳች ነገር ዙሪያ የሚታሰር ነገርን ነው። ብዙ ጊዜ የሚያመለክተው ቀሚስ ወይም እጀ ጠባብ ወደ መሬት እንዳይወርድ ወገብ ላይ ለማሰር የሚያገለግል ቀበቶ ወይም ሻሽን ነው።


መነሣት፣ ተነሣ

በአጠቃላይ፣ “መነሣት” – “ብድግ ማለት” ወይም፣ “ወደ ላይ መውጣት” ማለት ነው።


መነፋት

“መነፋት” የሚለው ፈሊጣዊ ቃል የሚያመለክተው ትዕቢተኛ ወይም ዕብሪተኛ መሆንን ነው።


መናቅ

“መናቅ” አንድ ሰው ወይም አንድን ነገር ለመቀበል አለመፈለግ ማለት ነው። እግዚአብሔርን መናቅ ለእርሱ መታዘዝ አለመፈለግ ነው።


መንቀጥቀጥ

“መንቀጥቀጥ” ከፍርሃት ወይም ከከባድ ጭንቀት የተነሣ መናወጥ ወይም፣ መንዘፍዘፍ ማለት ነው።


መንጋ

“መንጋ” በጎችንና ፍየሎችን ወይም በሬዎችንና ላሞችን ወይም አሳማዎችን ያመለክታል


መንግሥት

መንግሥት በንጉሥ የሚገዛ የሰዎች ቡድን ነው። ንጉሥ ወይም ሌሎች ገዦች የሚቆጣጠሩትና በሥልጣን የሚያስተዳድሩትንም አካባቢ ወይም ፖለታካዊ አገርንም ያመለክታል።


መንጠቅ፣ ነጠቀ

ብዙውን ጊዜ፣ “መንጠቅ” የሚለው ቃል ተአምራዊ በሆነ መንገድ እግዚአብሔር በድንገት አንድን ሰው ወደ ሰማይ ሲወስድ ነው።


መንጠቅ፣ ንጥቂያ

“መንጠቅ” የሚያመለክተው አንድን ነገር፣ ብዙውን ጊዜ ደግሞ ለምግብ የሚሆን እንስሳን ማደንን ነው።


መከራ

“መከራ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው መከራና ጭንቀት ያለበት አዳጋች ጊዜን ነው።


መከራ ማድረስ፣ መከራ

“መከራ ማድረስ” አንድን ሰው ማሰቃየት ወይም መጉዳት ማለት ነው። “መከራ” ከዚህ የሚመጣ ሕመም፣ ስሜታዊ ሐዘን ወይም ሌላ ዐይነት ጉዳት ነው።


መከራ፣ መከራ መቀበል

“መከራ” እና፣ “መከራ መቀበል” የተሰኙት ቃሎች በሽታን፣ ስቃይን ወይም ሌሎች አዳጋች ነገሮችን የመሳሰሉ አስከፊ ነገሮች ማለት ነው


መከር

“መከር” የሚለው ቃል እህል፣ ፍራፍሬ ወይም አትክልት መሰብሰብን ያመለክታል።


መካን(መኻን)

“መካን” መሆን ልጅ አለመውለድ ወይም ፍሬያማ አለመሆን ማለት ነው


መካከለኛ

መካከለኛ የሚባለው ሁለት ወገኖች አለመግባባትን አስወግደው ዕርቅ እንዲያደርጉ የሚረዳ ሰው ነው።


መክሰስ፣ክስ፣ከሳሽ

“መክሰስ”እና “ክስ” የተሰኙት ቃሎች በደል በማስረጉ አንድን ሰው መወቀስን ያመለክታል።ሌሎችን የሚከስ ሰው ከሳሽ ይባላል።


መክበብ፣ ከበበ

“መክበብ” የሚለው ቃል አጥቂ ሰራዊት ከተማን ሲከብና ምግብም ሆነ መጠጥ ወደዚያ እንዳይገባ ማድረግን ያመለክታል። አንድን ከተማን መክበብ እንቅስቃሴዋን መቆጣጠር ማለት ነው


መወሰን፣ ፍጻሜ

“መወሰን” የሚለው ቃል ወደ ፊት ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ያመለክታል። አንድ ሰው አንዳች ነገር እንዲያደርግ፣ “ተወስኖ” ከሆነ ያ ሰው ወደ ፊት የሚያደርገውን እግዚአብሔር ወስኖታል ማለት ነው።


መዋረድ፣ ውርደት

“ማረድ” አንድ ሰው እንዲያፍር ወይም እንዲሸማቀቅ ማድረግ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ይህ የሚደረገው ሰዎች ፊት ነው።


መዋረድ፣ ውርደት

“ማረድ” አንድ ሰው እንዲያፍር ወይም እንዲሸማቀቅ ማድረግ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ይህ የሚደረገው ሰዎች ፊት ነው።


መዋረድ፥ ውርደት

“መዋረድ” ክብርንና ተቀባይነት ማጣትን ያመለክታል።


መውቂያ፣ መውቃት

“መውቂያ” እና፣ “መውቃት” የተሰኙት ቃሎች የስንዴን ዘር ከተቀረው የስንዴው ክፍል የመለየት ሥራን ያመለክታሉ።


መውጋት

“መውጋት” ስለት ባለው ሹል ነገር መውጋት ማለት ሲሆን፣ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ሰውን በጣም ማሳዘንን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።


መያዝ

“መያዝ” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር በኅይል መያዝ ማለት ነው። ማሸነፍ ወይም ከቁጥጥር ሥር ማድረግ ማለትም ይሆናል


መያዝ፣ ያዘ

“መያዝ” ሰው ላይ ወይም አንዳች ነገር ላይ ተቆጣጣሪ መሆን ማለት ነው። አብዛኛውን ጊዜ አንድ ነገር አሳድዶ መያዝንም ይጨምራል።


መደምሰስ፣ ደመሰሰ

“መደምሰስ” እና፣ “ደመሰሰ” የሚለው ቃል ሰዎችን ወይም ነገሮችን ጨርሶ ማስወገድ ወይም ማጥፋትን የሚያመለክት ፈሊጣዊ ቃል ነው።


መደረቢያ

መደረቢያ ከትከሻ እስከ ወገብ ወይም ጉልበት የሚደርስ ልብስ ነው።


መደነቅ፣ መገረም

እነዚህ ቃሎች “አንድ የተለየ ነገር በመደረጉ መደነቅን” ነው የሚያመለክቱት።


መደነቅ፥ አክብሮት፥ አስፈሪ

“አክብሮት” የሚለው የመደነቅ ስሜትንና ታላቅነትን፥ ኅያልነትንና ባለ ግርማነትን በማየት የሚመጣ ጥልቅ አክብሮትን ያመለክታል


መደፋት

“መደፋት” የሚለው ቃል ፊትን ወደ መሬት በማድረግ መዘርጋት ማለት ነው። በድንገት በጣም ዝቅ ብሎ ማጎንበስ ማለት ነው።


መገሠጽ

መገሠጽ በቃል ጠበቅ ያለ እርማት መስጠት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እንዲህ የሚደረገው ያንን ሰው ከኀጢአት ለመመለስ ነው።


መገዛት፣ በመገዛት

ብዙውን ጊዜ፣ “መገዛት” የሚለው ቃል ፈቅዶና ወዶ ራስን በሌላው ሰው ሥልጣን ወይም መንግሥት ሥር ማድረግ ማለት ነው


መጋረጃ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን “መጋረጃ” የሚያመለክተው መገናኛው ድንኳንንና ቤተ መቅደሱን ለመሥራት ጥቅም ላይ ይውል የነበረውን ወፍራምና በጣም ከባድ ጨርቅ ነበር።


መግዛት

መግዛት በአንድ አገር ወይም በአንድ መንግሥትና ሕዝቡ ላይ ንጉሥ መሆን ማለት ነው። አንድ ንጉሥ የሚገዛው እርሱ በሕይወት እስካለ ድረስ ነበር።


መግፋት

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “መግፋት” ጉልበት በመጠቀም አንድን ነገር ማስወገድ ማለት ነው። የተለያዩ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።


መጠበቂያ ግንብ

“መጠበቂያ ግንብ” ጠባቂዎች እዚያ ላይ ሆነው ማንኛውንም አደጋ የሚመለከቱበት ቦታ እንዲሆን የተሠራ ረጅም ግንብ ነው። እነዚህ ግንቦች አብዛኛውን ጊዜ የሚሠሩት ከድንጋይ ነው።


መጠየቅ

“መጠየቅ” መረጃ የሚጠይቅ ማለት ነው።


መጠጊያ

“መጠጊያ” የሚለው ቃል ዋስትናና ጥበቃ ያለበትን ቦታን ወይም ሁኔታን ያመለክታል። “መጠቢያ” ከዝናብ ወይም ከአደጋ የሚከልል ነገር ነው።


መጠጊያ፥ መጠለያ

“መጠጊያ” የሚለው ቃል ዋስትናና ጥበቃ ያለበትን ቦታን ወይም ሁኔታን ያመለክታል። “መጠለያ” ከዝናብ ወይም ከአደጋ የሚከልል ነገር ነው።


መጥረቢያ


መጥረግ፣ ጠረገ

“መጥረግ” እና፣ “ጠረገ” የሚሉት ቃሉች አብዛኛውን ጊዜ የሚያመለክቱት መጥረጊያ በመጠቀም ቆሻሻና የማይፈለግ ነገር ማስወገድ በፍጥነት መንቀሳቀስን ነው። እነዚህ ቃሎች ማሳሌያዊ ትርጉምም አላቸው


መጨረስ

ቃል በቃል ሲወሰድ እስኪያልቅ ድረስ አንድን ነገር መጠቀም ማለት ሲሆን በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም ይኖሩታል።


መጨቆን፣ ጭቆና፣ ጭቋኝ

“መጨቆን” እና፣ “ጭቆና” በከፍተኛ ደረጃ ሰዎችን መበደልን ያመለክታል። “ጨቋኝ” ሰዎችን የሚጨቁን ሰው ነው።


መጮኽ

“መጮኽ” እንባ አውጥቶ ማልቀስ ወይም ጭንቅ ውስጥ ያለ ሰው የሚያሰማው ጥሪ ሊሆን ይችላል።


መጽናት፣ ጽናት

መጽናት፣ ምንም እንኳ ረጅም ጊዜ ቢወስድና በጣም አስቸጋሪም ቢሆን በእምነት ወይም የተሰጠውን ሥራ በመፈጸም መቀጠል ማለት ነው።


መጽደቅ፣ ጽድቅ

“መጽደቅ” እና፣ “ጽድቅ” የተሰኙት ቃሎች በደለኛውን ሰው ምንም በደል እንዳልፈጸመ አድርጎ መቀበል ማለት ነው። ሰዎችን ማጽደቅ የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው።


መፅነስ፣ ፅንስ

ብዙዎን ጊዜ “መፅነስ” እና፣ ፅንስ” የተሰኙ ቃሎች የሚያመለክቱት ልጅ ማርገዝን ነው። ያረገዙ እንስሳትን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።


መፈለግ፣ ፈለገ

“መፈለግ” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር መሻት ማለት ነው። ኅላፊው ግሥ፣ “ፈለገ” የሚለው ነው። አንድን ነገር ለማድረግ “አጥብቆ መሞከር” ወይም፣ “ከባድ ጥረት ማድረግ” ማለትም ይሆናል


መፈወስ፣ ፈወሰ

መፈወስ የሰው ቁስል፣ ሕመም ወይም ዕዐይነ ስውርነትና የመሳሰሉ ጉድለቶች ከእንግዲህ እንዳይኖሩ ማደረግ ነው። ወይም የታመመውን ወይም ዐቅም ያጣውን ሰው እንደ ገና ጤነኛ ማድረግ ነው።


መፋታት፣ ፍቺ

መፋታት ጋብቻ የሚቋረጥበት ሕጋዊ አሠራር ነው። ፍቺ ያደረጉ ባልና ሚስት ከእንግዲህ ትዳር ውስጥ አይደሉም ማለት ነው።


መፍረስ፣ ፍርስራሽ

አንድ ነገር፣ “ማፍረስ” ያንን ነገር ማበላሸት፣ ማጥፋት፣ መደምሰስ፣ ወይም ከጥቅም ውጪ ማድረግ ማለት ነው። “ፍርስራሽ” እንዲፈርስ ከተደረገው ነገር የቀረ ክምር ነው።


መፍጠር፣ ፍጥረት፣ ፈጣሪ

“መፍጠር” አንድን ነገር ማድረግ ወይም ሕልውና እንዲኖረው ማድረግ ማለት ነው። የተፈጠረ ነገር “ፍጥረት” ይባላል። በመላው አጽናፍ ያለውን ወደ ሕልውና ያመጣ እርሱ በምሆኑ እግዚአብሔር፣ “ፈጣሪ” ይባላል።


ሙሽራ (ሙሽሪት)

ሙሽሪት የወደፊት ባልዋ ከሚሆነው ሙሽራ ጋር ለመጋባት የጋብቻ ሥርዓት ላይ ያለች ሴት ናት።


ሙሽራ (ወንድ)

ጋብቻ ሥርዓት ላይ ያለ ሙሽራ ሙሽራዪቱን የሚያገባው ሰው ነው።


ማልቀስ፣ ለቅሶ

“ማልቀስ” እና፣ “ለቅሶ” የተሰኙት ቃሎች ጥልቅ የሐዘን መገለጫዎች ሲሆኑ፣ ብዙውን ጊዜ የሚያያዙት ሰው ሲሞት ከሚደረግ ሐዘን ጋር ነው። ብዙ ባሕሎች ሐዘንና ትካዜያቸውን የሚገልጡበት ውጫዊ እንቅስቃሴን ይጨምራል።


ማሕፀን

“ማሕፀን” እናቱ ውስጥ ያለ ሕፃን የሚኖርበት ነው።


ማመፅ፣ ዐመፀኛ

ማመፅ ሥልጣን ላይ ላለ ሰው አለመገዛት ማለት ነው። ለአለቃ አለመታዘዝ ማለትም ነው።


ማረሻ

“ማረሻ” አንድን ቦታ ለዘር ለማዘጋጀት መሬቱን ሥርዓት ባለው መልኩ ለመቆፈር የሚያገለግል የእርሻ መሣሪያ ነው።


ማረድ፣ ታረደ

“ማረድ” ሰውን ወይም እንስሳን መግደል ማለት ነው። ብዙ ጊዜ ግን በኅይል ወይም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደልን ነው የሚያመለክተው


ማረድ፣ ታረደ

“ማረድ” ሰውን ወይም እንስሳን መግደል ማለት ነው። ብዙ ጊዜ ግን በኅይል ወይም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደልን ነው የሚያመለክተው


ማር፣ የማር እንጀራ

ማር ንቦች ከአበባ የሚሠሩት ጣፋጭና ሙጫነት ያለው የሚበላ ነገር ነው። የማር እንጀራ ንቦቹ ማሩን የሚያኖሩበት እንደ ሰም ያለው ቅርጽ ነው።


ማርከስ

“ማርከስ” ቅዱስ የሆነ ነገርን ማቆሸሽ፣ መበከል ወይም አለማክበር ማለት ነው።


ማርከስ፣ መርከስ

“ማርከስ” እና፣ “መርከስ” የተሰኙት ቃሎች መበከልን ወይም በከፍተኛ ደረጃ መቆሸሽን ያመለክታሉ። አንድ ነገር ከአካላዊ፣ ከግብረ ገባዊ ወይም ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ርኵስ ተብሎ ሊጠራ ይችላል።


ማርከስ፣ ማጉደፍ

ለአምልኮ ጥቅም ላይ ማዋል በማይቻልበት ሁኔታ የተቀደሰ ቦታን ወይም ነገርን መጉዳት ወይም መበከል ማለት ነው።


ማሰላሰል

“ማሰላሰል” የሚለው ቃል ጊዜን ወስዶ ስለ አንድ ነገር በጥንፍቃቄና በጥልቀት ማሰብ ነው።


ማሳሳት፣ መሳት፣ ስሕተት፣ አሳሳች

“ማሳሳት” እውነት ያልሆነ ነገር እንዲታመን ማድረግ ነው። ሌሎችን የማሳሳት ተግባር “ማሳት” ይባላል።


ማሳደድ፣ ስደት

አንድን ሰው ማሳደድ ደጋግሞ ማጥቃት ወይም እርሱ ላይ የጭካኔ ተግባር መፈጸም ነው።


ማስተማር፣ አስተማሪ

“ማስተማር” ከዚያ በፊት የማያውቁትን መረጃ ለሰዎች መናገርን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ መረጃው የሚሰጠው ወግ ባለው ወይም ስልታዊ በሆነ መንገድ ነው


ማስጠንቀቂያ/መሸበር

ማስጠቀቂያ የሚጎዳቸውን ነገር አስመልክቶ ሰዎችን ማሳሰብ ማስጠንቀቅ ማለት ነው።መሸበር አደገኛ ወይም ስጋት ያለውን ነገር በተመለከተ በጣም መጨነቅና መፍራት ማለት ነው።


ማቅ

ማቅ ከፍየል ወይም ከግመል ጠጉር የሚሠራ ልብስ ነው። ይህ ዐይነቱ ልብስ ሻካራና የሚኮሰኩስ ነበር።


ማበረታታት

መበረታታት የሚለው የሚያመለክተው በቃልም ሆነ በተግባር ሌሎች እንዲጽናኑ፣ ተስፋ እንዲኖራቸው፣ ድፍረትና ጽናት እንዲኖራቸው ማድረግን ነው።


ማበራየት፣ ማበጠር

“ማበራየት” እና፣ “ማበጠር” ለምግብ የሚሆነውን እህል ከማይፈልጉ ነገሮች መለየት ማለት ነው። ስሞችን መለየትን ወይም መክፈልን አስመልክቶ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁለቱም ቃሎች በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ውለዋል።


ማባከን፣ ጠፍ ምድር

አንድን ነገር ማባከን በቸልታ መወርወር፣ ወይም ያለ አግባብ መጠቀም ማለት ነው። “የባከነ” የጠፋ ወይም ከጥቅም ውጪ የሆነ ነገርን ያመለክታል።


ማነሣሣት፣ መተንኮስ

“ማነሣሣት” ወይም፣ “መተንኮስ” አንድ ሰው አሉታዊ ምላሽ እንዲሰጥ ወይም አሉታዊ ስሜት እንዲያድርበት ማድረግ ማለት ነው።


ማክበር

አንድ ሰው ወይም ነገር ምን ያህል ታላቅና አስፈላጊ መሆኑን ማሳየት ወይም መናገር ማለት ነው። ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ክብር መስጠት” ማለት ነው።


ማወቅ፣ ዕውቀት፣ ማሳወቅ

“ማወቅ” አንድን ነገር መረዳት ወይም አንድን ሐቅ መገንዘብ ማለት ነው። “ማሳወቅ” አንድን መረጃን ለሌሎች መናገር ማለት ነው።


ማወጅ፣ ዐዋጅ

“ማወጅ” እና “ዐዋጅ” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት ሰው ሁሉ እንዲያውቀው ተፈልጎ በግልጽ በአደባባይ ለሕዝብ የሚነገር ሲሆን፣ እንዲህ የሚደረገው ለጉዳዩ አጽንዖት ለመስጠት ታስቦ ነው።


ማወጅ፣ ዐዋጅ

አንድን ነገር በሕዝብ ፊት እና በድፍረት መናገር ወይም ማሳወቅ ማወጅ ይባላል።


ማውደም፣ ውድመት

“ማወደም” ወይም፣ “ውድመት” የተባለው ቃል ንብረትን፣ ምድርን ወይም ሌላ ጠቃሚ ነገርን ጨርሶ ማጥፋትን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ በዚያ ምድር የሚኖሩ ሰዎችን መቆጣጠርን ወይም ጨርሶ ማጥፋትንም ይጨምራል።


ማውጣት፣ ማባረር

አንድ ነገር ወይም አንድን ሰው፣ “ማውጣት” ወይም፣ “ማባረር” ያ ነገር ወይም ሰው ከዚያ እንዲሄድ ማስገደድ ማለት ነው።


ማዳፈን

“ማዳፈን” የሚለው ቃል አንድ ነገር ማጥፋት ወይም መርካት የሚፈልግን ነገር ማስቆም ማለት ነው።


ማድላት፣ አድልዎ

“ማድላት እና፣ “አድልዎ” የተሰኙ ቃሎች፣ አንዳንድ ሰዎችን ከሌሎች የበለጠ ማቅረብ ወይም ከሌሎች የተለየ ነገር ማድረግን ያመለክታል።


ማገለገል፣ አገልግሎት

አንድን ሰው ማገለገል ለእርሱ የሚጠቅመውን ማድረግ ማለት ነው። አንድ ሰው ሌላውን የሚያገለግለው፣ ተገድዶ ወይም ማገልገል ስለፈለገ ብቻ ሊሆን ይችላል


ማጎንበስ፣ ጎንበስ ማለት

ማጎንበስ ለአንድ ሰው ክብርን ለማሳየት በትሕትና ከወገብ እጥፍ ማለት ነው። “ጎንበስ ማለት” በጣም መታጠፍ ወይም በጣም ዝቅ ብሎ መንበርከክ ማለት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ ግንባርንና እጆችን መሬት ላይ ማድረግንም ይጨምራል።


ማጨድ፣ አጫጅ

ማጨድ እህልን የመሳሰሉ ነገሮች ማምረት ማለት ነው። እህል የሚያመርት ሰው አጫጅ ይባላል።


ማጽናት፣ ማረጋገጥ፣ ማጽኛ

“ማጽናት” የሚለው ቃል አንድ ነገር እውነት ወይም እርግጥ ወይም አስተማማኝ መሆኑን መናገር ወይም መመልከት ማለት ነው።


ማጽናናት፣ አጽናኝ

“ማጽናናት” እና “አጽናኝ” የተሰኙት ቃሎች አካላዊም ይሁን ጉዳት ያደረሰባቸው ሰዎች መርዳትን፣ አይዞአችሁ ባይነትን ነው የሚያመለክተው።


ማፌዝ፣ መቀለድ፣ መዘበት።

“ማፌዝ” “መቀለድና” እና፣ “መዘበት” የተባሉት ቃሎች ሁሉ የሚያመለክቱት በሚጎዳ መልኩ ሌሎችን መሳቂያ መሳለቂያ ማድረግን ነው።


ምሕረት፣ ይቅርታ ማድረግ

“ምሕረት” ይቅር ማለትና ስል ተፈጸመው ኀጢአት አለመቀጣት ማለት ነው።


ምሥጢር፣ የተደበቀ እውነት

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፣ “ምሥጢር” የማይታወቅ ወይም ለመረዳት የሚያዳግት አሁን ግን እግዚአብሔር የገለጠውን ነገር ያመለክታል።


ምርመራ፣ ፈተና

“ምርመራ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው፣ “ማጣራትን” ወይም፣ መፈተንን ነው። አንድ ሰው በደለኛ ወይም ንጹሕ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚደረግ የማጣራት ወይም፣ የምርመራ ተግባር ነው። ምርመራ ወይም ፈተና ለመቋቋም የሚያዳግት ሁኔታ ሲሆን፣ ለዚያ በሚሰጠው ምላሽ አንድ ሰው ለተፈለገው ነገር ተገቢ ሊሆን ወይም ላይሆንን ይችላል።


ምርኩዝ(በትር)

ምርኩዝ ሰዎች ሲራመዱ የሚጠቀሙበት ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ከዘራ ወይም በትር ነው


ምርኮ፣ ምርኮኛ

“ምርኮ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከአገራቸው ርቀው ሌላ ቦታ እንዲኖሩ የተገደዱ ሰዎችን ያመለክታል።


ምርኮኛ፣ ምርኮ

“ምርኮና” እና፣ “ምርኮ” የተሰኙ ቃሎች መኖር በማይፈልጉበት የባዕድ አገር እንዲኖሩ ሰዎችን መያዝ ወይም ማስገደድን ያመለክታሉ።


ምሳሌ

ምሳሌ ጥበብ ወይም እውነት የያዘ አጭር ዐረፍተ ነገር ነው።


ምስል፥ የተቀረጸ ምስል፥ የተቀረጸ ቅርጽ፥ በብረት የተሠራ ምስል

እነዚህ ቃላት በጠቅላላ ሀሰተኛን አምላክ ለማምለክ የተቀረጹን ጣኦታትን ለማመልከት የምንጠቀምባቸው ናቸው።


ምስክር፣ የዓይን ምስክር

“ምስክር” የሆነውን ነገር በግል የሚያውቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ምስክር የሚባለው እውነት መሆኑን የሚያውቀውን የሚናገር ሰው ነው። “የዓይን ምስክር” እዚያ የነበረና የሆነውን ሁሉ በዓይኑ የተመለክተ ሰው ነው።


ምስጋና

አንድ ሰው ማመስገን ለዚያ ሰው ያለንን አድናቆትና ክብር መግለጥ ማለት ነው።


ምሽግ፣ መከላከያ፣ የተመሸገ

“ምሽግ” ወይም፣ “መከላከያ” የጠላት ወታደሮችን ጥቃት መከለከል እንዲቻል በሚገባ የታጠረ ወይም ከለላ ያለው ቦት ማለት ነው። “የተመሸገ” ከተባለ አንድን ከተማ ወይም ምሽግ ለመከላከል በጠንካራ ግንቦች ዐለቶችና ሌሎች ጠንካራ ነገሮች ማጠርን ያመለክታል


ምንጭ

ምንጭ በተፈጥሮው ከመሬት የሚፈልቅ ወይም የሌላ ዓይነት ወራጅ ውሃ መነሻ ቦታ ነው።


ምክር፣ መካሪ፣ አማካሪ

ምክር ማለት አንድ ሰው ማስተዋል ያለበት ውሳኔ እንዲያደርግ ተገቢውን ሐሳብ መስጠት ማለት ነው። መልካም “መካሪ” ወይም፣ “አማካሪ” ሰዎች ትክክልኛ ምርጫ ማድረግ እንዲችሉ አስፈላጊ ሐሳብ ይሰጣል።


ምድር፣ ምድራዊ

“ምድር” ሕይወት ያላቸው ሌሎች ነገሮችን ጨምሮ የሰው ልጆች የሚኖሩበትን ዓለም ያመለክታል።


ምድጃ

ምድጃ መንደድ ያለበት ነገር የሚቀጣጠልበትና የሚነድበት ትልቅ ማንደጃ ነው።


ምጽዋት

“ምጽዋት” የሚለው ቃል ድኾችን ለመርዳት የሚሰጥ ገንዘብን፣ምግብን ወይም ሌሎች ነገሮችን ያመለክታል።


ሞት፣ መሞት፣ ሞተ

እነዚህ ቃሎች አካላዊንም ሆነ መንፈሳዊ ሞትን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላሉ። አካላዊ በሆነ መልኩ የሰውየው አካል መሥራትን ማቆሙን ያመለክታል። በመንፈሳዊ አንጋገር በኀጢአታቸው ምክንያት ሰዎች ከቅዱሱ እግዚአብሔር መለየታቸውን ያመለክታል።


ሟርት፣ ሟርተኛ፣ ሟርተኝነት

ሟርት እና ሟርተኛ የሚለው ቃል ልዕለ ተፈጥሮአዊ ከሆነው የመናፍስት ዓለም መረጃ ለማግኘት የሚደረግ መከራን ያመለክታል። ይህን የሚለማመድ ሟርተኛ ይባላል።


ሟርት፣ ጥንቆላ

“ሟርት” ወይም “ጥንቆላ” አስማት በመጠቀም በክፉ መናፍስት ርዳታ አስደናቂ ነገሮችን ማድረግን ያመለክታል። በእነዚህ አስማታዊ ኅይሎች አስደናቂ ነገሮች የሚያደርገው ሰው ሟርተኛ ይባላል


ሥራ፣ ሠራተኛ

ማንኛውም ጉልበትን የሚጠቅይ ከባድ ልፋት ሥራ ይባላል።


ሥርዓት

ሥርዓት ሰዎች የሚኖሩበት መመሪያ የሚሆን በውል ጽሑፍ ላይ የሰፈረ ሕግ ነው


ሩጫ፣ መሮጥ

ሩጫ፣ መሮጥ ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ሩጫ” ከመራመድ ባለፈ በፍጥነት መንቀሳቀስ ማለት ነው


ራስ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ራስ” በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞች አሉት።


ራስን መግዛት

ራስን መግዛት ኅጢአትን ላለማድረግ የራስን ፀባይና ሁለንተና የመቆጣጠር ችሎታ ማለት ነው


ራእይ

“ራእይ” የሚለው ቃል አንድ ሰው የሚያየውን ያመለክታል። በተለይ ደግሞ የሚያመለክተው መልእክት ለመስጠት ባልተለመደ ወይም ልዕለ ተፈጥሮአዊ መንገድ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚያሳየውን ያመለክታል።


ርግብ፣ ዋኖስ

ርግብና ዋኖስ በጣም የሚመሳሰሉ የተለያየ መልክ ያላቸው ትናንሽ ወፎች ናቸው። ርግብ በምጠኑ ፈካ ያለች ስትሆን ወደ ነጭነት ትጠጋለች።


ሮማን

ሮማን በሚበላ ቀይ ነገር የተሸፈኑ ብዙ ፍሬዎች ያሉት ጥብቅና ጠንካራን ሽፋን ያለው የፍራፍሬ ዐይነት ነው።


ሰላም፣ ሰላማዊ

ሰላም ምንም ዓይነት ግጭት ወይም ስጋት አለመኖር ማለት ነው።


ሰረገላ

በጥንት ዘመን ሰረገሎች በፈረሶች የሚጎተቱ ቀለል ያለ ክብደት ያላቸው ባለ ሁለት ተሽከርካሪ (ጎማ) መጓጓዣ ነበሩ።


ሰኮና

ሰኮና ግመልን፣ ላምና በሬን፣ ፈረሶችን፣ አህዮችን፣ በጎችና ፍየሎችን የመሳሰሉ አንዳንድ እንስሳት ታችኛውን የእግራቸውን ክፍል የሚሸፍን ጠንካራ ነገር ነው።


ሰዓት

አንድ ነገር የተፈጸመው ምቼና እንዴት እንደ ነበር ከማመልከት በተጨማሪ፣ “ሰዓት” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለቻቸው በርካታ ምሳሌያዊ መንገዶች አሉ።


ሰይፍ

ሰይፍ ለመቁረጥ ወይም ለመውጋት የሚያገለግል ጠፍጣፋ ስለት ያለ የጦር መሣሪያ ነው መያዣና ረጅም፣ ሾጠጥ ያለና ጫፉ ላይ ስለት አለው


ሳንደል

ሳንደል ከእግር ታችኛው ክፍልና ከቁርጭምጭሚት ጋር በክር የሚታሰር ሰለል ያለ ጫማ ነው። ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ይጠቀሙበት ነበር


ሴላ

ሴላ ብዙውን ጊዜ መዝሙር መጽሐፍ ውስጥ የሚገኝ የዕብራይስጥ ቃል ነው በርካታ ትርጉሞች ይኖሩት ይሆናል


ስቃይ

‘’ስቃይ” የሚለው ቃል ከባድ ህመምን ወይም ጭንቀትን ያመለክታል።


ስቃይ

“ስቃይ” የሚያመለክተው ከፍተኛ መከራን ነው። አንድን ሰው ማሰቃየት ብዙውን ጊዜ በጭካኔ ከባድ መከራ እንዲደርስበት ማድረግ ነው።


ስብሰባ(ጉባኤ)፥ መሰብሰብ

“ስብሰባ(ጉባኤ)” የሚለው ቃል ችግሮች ላይ ለመወያየት፥ ምክር ለመስጠትና ውሳኔ ለማሳለፍ በአንድነት የተሰበሰቡ ሰዎችን ያመለክታል


ስንዴ

ስንዴ ሰዎች ለምግብ የሚያመርቱት እህል ነው።


ሸንጎ፣ ምክር

ሸንጎ በጣም አስፈላጊ ጉዳዮችን በተመለከት ለመወያየት፣ ምክር ለመስጠትና ውሳኔ ለማሳለፍ የተሰበሰቡ ሰዎች ማለት ነው።


ሸክም

ሸክም ከባድ ጫና ነው። ቃል በቃል የጥንት እንስሳት የሚሸከሙትን ሸክም ያመልክታል። “ሸክም” የሚለው ቃል በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።


ሽማግሌ

ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር ሕዝብ መሐል መንፈሳዊና ተግባራዊ መሪነት ኀላፊነት ያላቸው መንፈሳዊ ማስተዋል ያላቸው ስሞች ናቸው።


ሽብር፣ ማሽበር

“ሽብር” የሚለው ቃል በጣም የመፍራትና የመደንገጥ ስሜት ወይም አንድን ሰው ወይም ነገር በጣም መጥላት ማለት ነው።


ሽብር፣ ተሸበረ

“ሽብር” የሚለው ቃል ከፍተኛ የፍርሃት ወይም የድንጋጤ ስሜት ያመለክታል። ሽብር የሚሰማው ሰው፣ “ተሸበረ” ይባላል።


ቀረጥ

“ቀረጥ” ሰዎች እነርሱ ላይ ሥልጣን ላይ ላለው መንግሥት የሚከፍሉት ገንዘብ ወይም ዕቃ ነው


ቀረጥ ሰብሳቢ

የቀረጥ ሰብሳቢ ሥራ ከሰዎች የተቀበለውን ገንዘብ ለመንግሥት ማስተላለፍ ነበር


ቀስተኛ


ቀንበር

“ቀንበር” ሁለት በሬዎች በአንድነት እንዲሠሩ ለማጣመር የሚረዳ ነገር ነው። “ቀንበር መሸከም” አንድ ዓይነት ኀላፊነት መሸከም ማለት ነው።


ቀንድ፣ ቀንዶች

ቀንዶች ላምና በሬ፣ በጎችና ፍየሎች የመሳሰሉ እንስሳት ራስ ላይ የሚበቅል ቋሚና ሹል ነገር ነው። ብርታትን፣ ኀይልን፣ ሥልጣንና ንጉሥነትን ለማመልከትም “ቀንድ” በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።


ቃል

“ቃል” አንድ ሰው የተናገረውን ያመለክታል።


ቃል መግባት

“ቃል መግባት” አንድ ነገር ለማድረግ ወይም ለመስጠት ተስፋ መስጠት ማለት ነው።


ቃርሚያ፣ መቃረም

ቃርሚያ አጫጆች የተዉትን ፍራ ፍሬ ወይም እህል ለመሰብሰብ እርሻ ወይም አትክልት ቦታ ውስጥ መሄድ ማለት ነው።


ቅርጫት

“ቅርጫት” እርስ በርስ ከተጠላለፉ ነገሮች የሚሠራ መያዣን ያመለክታል


ቅርጽ ማውጫ

ቅርጽ ማውጫ የሚባለው ከወርቅ፣ ከብርና ከሌሎች ፈሳሽ መሆን ከሚችሉ ነገሮች አንዳንድ ነገሮችን ለመሥራት የቅርጽ ማውጫውን ይዘው እንዲወጡ ለማድረግ ከእንጨት ቁራጭ፣ ከብረት ወይም ከሸክላ ተፈልፍሎ የሚሠራ ነገር ነው።


ቅናት፣ መመኘት

ቅናት ያ ሰው ካለው ሀብት የተነሣ ወይም የሚደነዙ ችሎታዎች በለቤት ከመሆኑ የተነሣ ሌላውን ሰው መመቅኘት ማለት ነው። “መመኘት” ያ ሰው ያለውን ነገር ለራስ ለማድረግ አጥብቆ እስከ መፈለግ ድረስ በቅናት መነሣሣት ማለት ነው።


ቅን፣ ቅንነት

“ቅን” እና፣ “ቅንነት” የእግዚአብሔርን ሕግ እየተከተሉ መኖርን ያመለክታል።


ቅድስት ከተማ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ቅድስት ከተማ” የሚያመለክተው የኢየሩሳሌም ከተማን ነው።


ቆጠራ

“ቆጠራ” የሚለው ቃል ሥርዓት ባለው መልኩ በአገሩ ወይም በመንግሥቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች መቊጠርን ያመለክታል።


በለስ

በለስ የበለስ ዛፍ ላይ የሚበቅል ትንሽና ጣፋጭ ፍሬ ነው። ሰዎች ትኩሱን፣ ቀቅለው ወይም አድርቀው በለስ መብላት ይችላሉ፣ ወይም ይከትፏቸውና እንደቂጣ አድርገው ይበሏቸዋል።


በረሐ፣ ምድረ በዳ

በረሐ ወይም ምድረ በዳ በጣም ጥቂት ተክሎችና ዛፎች ብቻ የሚያድጉበት ደረቅና ጠፍ ቦታ ነው።


በረዶ

“በረዶ” ተራሮችን በመሳሰሉ ከፍታ ቦታዎች ወይም የዓለማችን ሰሜን ወይም ደቡብ ጫፍ ላይ የሚወርድ ውሃ አዘል ጠጣር ነገር ነው


በሬ፣ በሬዎች

በሬ በተለይ ለእርሻ ስራ የተገራ የከብት ዓይነት ነው። ብዙ ቁጥስ ሲሆን፣ “በሬዎች” ይባላል። በሬ የሚያገለግለው ለተባዕቱ ብዙውን ጊዜ እንዲኮላሹ ይደረጋል።


በሮች፣ የበር ሳንቃ

“በር” ቤት ወይም ከተማ አጥር ወይም ግድግዳ ላይ ያለ ወደ ቤት የሚገባበት ላይ የተያያዘ ከለላ ነው። “የበር ሳንቃ” በርን ለመዝጋት መንቀሳቀስ የሚችል ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ጣውላ ነው።


በስኬት መደሰት

?


በትረ መንግሥት

“በትረ መንግሥት” አንድ ንጉሥ ወይም የአገር አስተዳዳሪ የሚይዘው ጌጠኛ በትር ወይም ዱላ ነው


በትር

በትር ቀጭን፣ ጠንካራና በተለያየ መንገድ ጥቅም ላይ የሚውል ከዘራ መሰል ነገር ነው። ምናልባትም በትንሹ አንድ ሜትር ያህል ሊረዝም ይችላል።


በኣል

አጠቃላይ በሆነ መልኩ በኣል የማኅበረሰቡ ሰዎች በአንድነት የሚያከብሩት ሁኔታ ነው።


በኩራት

“በኩራት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በእያንዳንዱ መከር ወቅት ከሚሰበሰበው እህል ሆነ አትክልት የመጀመሪያውን ፍሬ ነው።


በኩር

“በኩር” የሚለው ቃል መጀመሪያ የሚወለደውን የሰውም ሆነ የእንስሳትን የመጀመሪያ ልጅ ነው።


በዓል

በዓል ሰዎች በአንድነት ተሰብስበው በመመገብ የሚይሳልፉት ሁኔታ ሲሆን፣ እንዲህ የሚደረገው አንድን ሁኔታ አብሮ ለማክበር ሊሆን ይችላል። “በዓል ማድረግ” በልዩ አይነት ሁኔታ የተዘጋጀ ምግብ በብዛት መመገብን ያሳያል።


በደል፣ መበደል፣ መጉዳት

በደል፣ በመደልና መጉዳት ሌላው ሰው ላይ አካላዊ፣ ስሜታዊና ሕግን ተገን በማድረግ ጉዳት ማድረስ ማለት ነው።


በገና

በገና ባለ ገመድ የሙዚቃ መሣሪያ ሲሆን፣ ቀጥ ያሉ ክሮች ወይም ገመዶች ይኖሩታል።


በግ፣ አውራ፣ እንስት በግ

በግ አካሉ ላይ የሱፍ መሥሪያ ጠጉር ያለው መጠነኛ ቁመት ያለው ባለአራት እግር እንስሳ ነው። ወንዱ በግ አውራ ሲባል ሴቷ እንስት በግ ትባላለች


ባለሟል

“ባለሟል” የተመረጠና ከፍ ያለ ደረጃ ያለውን ሰው፣ በፖለቲካና በማኅበረ ሰቡ ውስጥ ሁነኛ ቦታ ያለውን ሰው ያመለክታል።


ባልንጀራ

“ባልንፈራ” እንደ ጓደኛ ወይም እንደ የትዳር አጋር ከአንድ ሰው ጋር አብሮ መሆንን ወይም ኅብረት ማድረግን ያመለክታል።


ባሕል

ባሕል የሚያመለክተው ለረጅም ዘመን የተያዘና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ ወግ ወይም ልማድ ነው።


ባርያ ማድረግ፣ ባርነት

አንድን ሰው ባርያ ማድረግ ያ ሰው ለጌታ እንዲገዛ ማስገደድ ወይም አንድን መግዛት ማለት ነው። ባርነት በሰዎች ወይም በነገሮችና በሁኔታዎች ቁጥጥር ሥር መሆን ማለት ነው።


ባርያ፣ ባርነት

አገልጋይ በውዴታ ወይም በግዴታ ለሌላው የሚሠራ ሰው ነው። “ባርያ” የሚለው ቃል “አገልጋይ” ማለትም ይሆናል። ከዐውዱ ጋር ይበልጥ የሚስማማው የትኛው ቃል እንደሆነ ብዙ ጊዜ ምንባቡ ግልጽ ያደርጋል


ባዕድ፣ መጻተኛ

“ባዕድ” ወይም “መጻተኛ” የሚለው ከራሱ አገር ውጪ የሚኖርን ሰው ያመለክታል። በተለይም ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከራሱ ሕዝብ መካከል ወጥቶ ሌላ ሕዝብ ጋር የሚኖር ሰው ማለት ነው።


ባድማ፣ ወና ማድረግ

“ባድማ” ወይም “ወና ማድረግ” መኖሪያ የነበረውን ከእንግዲህ መኖሪያ እስከማይሆን ድረስ አንድ ቦታ ማጥፋት መደምሰስ ማለት ነው።


ቤተ መቅደስ

ቤተ መቅደስ እስራኤል ለጸሎትና ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ የሚሰበሰቡበት ዙሪያውን በተከበበ አደባባይ ውስጥ ያለ ሕንፃ ነው። ቤተ መቅደስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ባለው የሞሪያ ተራራ ነበር።


ቤተ መንግሥት

“ቤተ መንግሥት” ከቤተሰቡና ከአገልጋዮቹ ጋር ንጉሥ የሚኖርበት ሕንፃ ወይም ቤት ማለት ነው።


ቤተሰብ

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቤተሰብ በዚህ ዘመን፣ “የሩቅ” ቤተሰብ የምንለውን ጨምሮ በጋብቻ ወይም በመወለድ የተዛመዱ ሰዎች መኅበረሰብ ነው።


ቤተሰብ

“ቤተ ሰብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የቤተ ሰብ አባሎችንና ያሉዋቸውን አገልጋዮች ጨምሮ አንድ ቤት ውስጥ አብረው የሚኖሩ ሰዎችን ሁሉ ነው።


ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ፣ “ቤት” ጥቅም ላይ የዋለው በምሳሌያዊ መልኩ ነው።


ብልሹ፣ ብልሽት

“ብልሹ” እና፣ “ብልሽት” የሰዎችን ክፋትና ግብረ ገባዊ ዝቅጠት ያመለክታል።


ብልት፣ ክፍል

ብልት ወይም ክፍል የአንድ ሕንፃ፣ አካል ወይም ቡድን አንድን ክፍል ያመለክታል።


ብልጥ

“ብልጥ” በተለይ ተግባራዊ በሆኑ ነገሮች በጣም ብልህና አስተዋይ ሰው ነው


ብሔር፣ ሕዝብ

“ብሔር” አብዛኛውን ጊዜ የሚያመለክተው ከአንድ ቅድመ አባት የተገኙትን ትውልዶችንና ተመሳሳይ ቋንቋና ባሕል ያላቸው ሰዎች ነው።


ብር

ብር ሳንቲሞችን፣ ጌጣጌጦችን፣ ዕቃዎችንና ማስዋቢያዎችን ለመሥራት የሚያገለግል አንጸባራቂ ነጭ/ግራጫ መልክ ያለው የከበረ ድንጋይ ነው


ብርሃን

መጽሐፍ ቅዱስ “ብርሃን” የሚለውን ቃል በተለያዩ ምሳሌያዊ ገለጻዎች ይጠቀምበታል። ብዙውን ጊዜ ጻድቃን፣ ቅድስናንና እውነትን ለማመልከት እንደ ተለዋጭ ዘይቤ ያገለግላል።


ብርቱ፣ ብርታት


ብርታት፣ ማበርታት

“ብርታት” የሚለው ቃል አካላዊ፣ ስሜታዊ ወይም መንፈሳዊ ጥንካሬን ነው። ማበርታት አንድን ሰው ወይም ነገር ጠንካራ ማድረግ ማለት ነው


ብቁ፣ ብቁ መሆን

“ብቁ” የሚለው ቃል የተወሰኑ ጥቅሞችን ለመቀበል ወይም የተለያዩ ሙያዎች ባለቤት የመሆንን ዕውቅትና ማግኘት ማለት ነው።


ተመስጦ

ተመስጦ የሚባለው ሰውየው እንቅልፍ ላይ ባይሆንም፣ አንድ ሌላ ነገር እየተመለከተ ወይም እየተለማመደ ከመሆኑ የተነሣ በዙሪያው ስላለው ነገር ግንዛቤ የሚያጣባት የአእምሮ ዝንባሌ ነው።


ተኩላ

ተኩላ አደገኛ ሥጋ በል አውሬ ሲሆን፣ ከቀበሮ ጋር ይመሳሰላል።


ተዋጊ፣ ወታደር

ሁለቱም ሰራዊት ውስጥ ሆኖ መዋጋትን የሚያመለክቱ በመሆናቸው፣ “ተዋጊ” እና፣ “ወታደር” ትርጕማቸው ተመሳሳይ ነው። ያም ሆኖ ግን፣ መጠነኛ ልዩነትም አላቸው።


ተገዢ፣ የተገዛ፣ መገዛት

“ተገዢ” የሚለው በሌላው ሰው ሥልጣን ሥር መሆንን ያመለክታል፥ “መገዛት” – “ለሌላው ሰው ሥልጣን” ታዛዥ መሆን ማለት ነው


ታማኝነት

ይህ ቃል የሚያመለክተው ቅንነትን ሲሆን፣ ሰው ባያይ እንኳ በጠንካራ ግብረ ገባዊ መርሕና ፀባይ በመነሣሣት ታማኝ ሆኖ መገኘትን ነው።


ታጋሽ፣ ትዕግሥት

“ታጋሽ” እና፣ “ትዕግሥት” የሚለው ቃል አስቸጋሪ የሆነ ሁኔታ መቋቋምን ወይም በዚያ ውስጥ በጽናት መኖርን ያመለክታል። አብዛኛውን ጊዜ ትዕግሥት መጠበቅንም ይጨምራል።


ትልቅ ማድረግ፣ ማጉላት

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ትልቅ ማድረግ” ታዋቂነት እንዲያገኝ በማሰብ ወደ አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር የሌሎችን ትኵረት መሳብ ማለት ነው።


ትውልድ

ትውልድ የሚባለው በአንድ ዘመን የተወለደና በአንድ ዘመን የነበረ የሰዎች ስብስብ ነው።


ችጋር

ችጋር በመላው አገር ወይም አካባቢ የምግብ እጥረትን የሚጨምር ጥፋት ሲስፋፋ ማለት ነው።


ችግር፣ መከራ፣ ሁከት

“ችግር” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በጣም አዳጋችና አስጨናቂ የሕይወት ልምምድን ነው። “ሁከት” ከአንዳች ንገር የተነሣ መረበሽ ወይም መጨነቅ ማለት ነው።


ኀላፊ፣ ባለ ዐደራ

መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ኀላፊ” ወይም “ባለ ዐደራ” የሚለው የጌታውን ንብረትና የሥራ እንቅስቃሴን በተመለከተ ሙሉ ኀላፊነት የተሰጠውን አገልጋይ ለማመልከት ነው።


ነቀፋ

ነቀፋ የአንድን ሰው ፀባይና አኗኗር መብቶች ወይም ይሁንታ መንፈግ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ነቀፋ ሰውየውን በተመለከተ አሉታዊ ቃል መሰንዘር ነው።


ነብር

ነብር ጥቁርና ነጭ ዝንጉርጉር መልክ ያለው ትልቅ ድመት መሰል የዱር አውሬ ነው።


ነገድ

ነገድ ብዙውን ጊዜ ከአንድ ቀዳሚ አባት የተገኙ ሰዎች ስብስብ ማለት ነው።


ነጻ ማድረግ

“ነጻ ማድረግ” አንድ ሰው ከተከሰሰበት በደል ወይም ርኩሰት ነጻ መሆኑን በግልጽ መናገር ወይም ማወጅ ማለት ነው።


ናስ (ነሐስ)

“ናስ” - መዳብናን ቆሮቆሮን አብሮ በማንጠር የሚሠራ አንድ ዐይነት ብረት መሳይ ነገር ነው። ጥቁር ቡኒ መልክ ቢኖረውም በመጠኑ ወደ ቀይም ወሰድ ያደርገዋል።


ንስር

ንስር እንደ ዓሣ፣ አይጥ፣ እባብና ጫጩት የመሳሰሉ ትንንሽ እንስሳትን የሚመገብ በጣም ግዙፍና ብርቱ ወፍ ነው።


ንቀት፣ የተናቀ

“ንቀት” አንድ ሰው ለሌላው ሰው ወይም ለሌላው ነገር ክብር መንፈጉን የሚያሳይበት መንገድ ነው። ክብር የተነፈገው፣ “የተናቀ” ይባላል።


ንብረት ማድረግ፣ ንብረት

“ንብረት ማድረግ” እና፣ “ንብረት” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት የአንዳች ነገር ባለቤት መሆንን ነው። አንድን ነገር ወይም አካባቢን መቆጣጠርንም ያመለክታል። አብዛኛውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉት በዚህ መልክ ነው።


ንዴት

ንዴት ከቁጥጥር የወጣ ቁጣ ነው። አንድ ሰው ከተናደደ፣ አጥፊ በሆነ ሁኔታ ቁጣውን እየገለጸ ነው ማለት ነው።


ንጉሣዊ

“ንጉሣዊ” የሚለው ቃል ከንጉሥ ወይም ከልዕልት ጋር የተያያዙ ሰዎችንና ነገሮችን ማለትም ዙፋናቸውን፣ ቤተ መንግሥታቸውን፣ ልብሶቻቸውንና ልጆቻቸውን ይመለክታል።


ንጉሥ

ንጉሥ የአንድ ነጻ ከተማ፣ መንግሥት ወይም አገር መሪ ነው።


ንጹሕ ያልሆነ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ንሑሕ ያልሆነ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር የሚያመለክተው ሕዝቡ ሊነካው፣ ሊበላው ወይም መሥዋዕት ሊያቀርበው እንደማይገባው እግዚአብሔር የተናገረለት ነገርን ነው።


አህያ፣ በቅሎ

አህያ ከፈረስ የሚያንስና ትላልቅ ጆሮዎች ያሉ ፈረስን የሚመስል ባለ አራት እግር አገልጋይ እንስሳ ነው።


አለመታዘዝ፣ የማይታዘዝ

“አለመታዘዝ” ሥልጣን ላይ ያለ ሰው ትእዛዝን ወይም መመሪያን አለመቀበል ማለት ነው። ይህን የሚያደርግ ሰው የማይታዘዝ ይባላል።


አለቃ፣ ዋና

“አለቃ” የሚለው ቃል በተወሰኑ አካል ላይ ከፍ ያለ ሥልጣን ያለውን ወይም በጣም አስፈላጊ መሪን ያመለክታል።


አለአግባብ፣ አግባብ ያልሆነ፣ ፍትሕ ማጉደል

“አለ አግባብ” እና፣ “አግባብ ያልሆነ” የተሰኙት ቃሎች ሰዎችን መግፋት፣ ማሳዘን፣ ብዙውን ጊዜ በጣም በሚጎዳ ሁኔት መበደል ማለት ነው።


አማኝ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “አማኝ” ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ መሆኑን የሚያምንና የሚደግፍ ማለት ነው


አሥረኛ፣ አሥራት

“አሥረኛ” ወይም፣ “አሥራት” የተሰኙት ቃሎች የአንድን ሰው ገንዘብ፣ እህል፣ የቤት እንስሳት ወይም ሌሎች ንብረቶች አንድ አሥረኛ ክፍል ያመለክታል።


አሥሩ ትእዛዞች

እግዚአብሔር ለሙሴ እስራኤል ሊታዘዟቸው የሚገባ ብዙ ትእዛዞች ሰጥቶታል። ከእነዚህ ትእዛዞች አሥሩን በሁለት የድንጋይ ጽላቶች ላይ ጽፏቸዋል።


አሥራ ሁለት የእስራኤል ነገዶች

አሥራ ሁለት የእስራኤል ነገዶች የተባሉት የያዕቆብ ልጆችና የእነርሱ ዘሮች ናቸው።


አረማዊ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “አረማዊ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ያህዌን ሳይሆን ሐሰተኛ አምላኮችን የሚያመልኩ ሰዎች ለማመልከት ነበር።


አሳልፎ መስጠት (መካድ)፣ አሳልፎ ሰጪ (ካጂ)

“አልፎ መስጠት” (መካድ) ሌላውን ሰው የሚያሳስትና የሚጎዳ ተግባር ነው። “አሳልፎ ሰጪ” (ካጂ) የተማመነበትን ወድጁን አሳልፎ የሚሰጥ ወይም የሚክድ ሰው ነው።


አስማት፣ አስማተኛ

“አስማት” ከእግዚአብሔር ከሚመጣው ውጪ ልዕለ ተፈጥሮአዊ ኀይል መለማመድ ወይም መጠቀም ነው። አስማት የሚለማመድ ሰው አስማተኛ ይባላል።


አስቀድሞ ማወቅ

ቃሉ የሚያማለክተው ገና ከመሆኑ በፊት አንድን ነገር ማወቅን ነው።


አስተማሪ

አስተማሪ ለሌሎች ሰዎች አዲስ መረጃ የሚሰጥ ሰው ነው። አስተማሪዎች ሰዎች ዕውቀትና ሙያ እንዲያገኙ ይረዳሉ


አስተምህሮ

ቃል በቃል ሲወሰድ አስተምህሮ ትምህርት በተለይም ሃይማኖታዊ ትምህርት ማለት ነው።


አስተዳደር፣አስተዳዳሪ

“አስተዳደር” እና “አስተዳዳሪ” የተሰኙት ቃሎች የአንድ አገር ሰዎች ሥርዓት ባለው መንገድ እንዲኖሩ መምራትን ወይም ማስተዳደርን ያመለክታል።


አባት፣ ጥንተ አባት

ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “አባት” የአንድ ሰው ወንዱ ወላጅ ማለት ነው። ይህን ቃል በተመለከተ በርካታ ምሳሌያዊ አነጋገሮች አሉት።


አባቶች (ርዕሳነ አበው)

ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “አባቶች” ለሚለው ቃል የሚያመለክተው የአይሁድ ሕዝቡ መሥራች የሆኑትን አባቶች (ርዕሳነ አበው) በተለይም አብርሃም፣ ይስሐቅንና ያዕቆብን ነው።


አንበሳ

አንበሳ እጁ የገባውን የሚገድልበትና የሚግነጣጥልበት ጥርሶችና ጥፍሮች ያሉት ባለ አራት እግር ትልቅ የዱር አውሬ ነው።


አንበጣ

“አንበጣ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንዳንዴ እጅግ በብዛት የሚመጡ፣ ያገኙትን ሁሉ የሚበሉ በጣም አጥፊ ትልቅ በራሪ ፌንጣዎች ናቸው።


አንገተ ደንዳና፣ ግርት

“አንገተ ደንዳና” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ለእግዚአብሔር ባለ መታዘዝ የዳኑትንና ተግሣጹን የማይቀበሉ ሰዎችን ያመለክታል። እነዚህ ትዕቢተኞች ናቸው።


አእምሮ (ልብ)

አእምሮ የሚያስብና ውሳኔ የሚያደርግ የሰው ተፈጥሮ ክፍል ነው።


አክሊል፣ አክሊል መድፋት (መጫን)

አክሊል ንጉሦችና ልዕልታትን የመሳሰሉ መሪዎች ራሳቸው ላይ የሚያደርጉት ክብ ቅርጽ ያለው ጌጥ ነበር። አክሊል መድፋት አንድ ሰው ራስ ላይ አክሊል ማኖር ማለት ሲሆን፣ በምሳሌያዊ ትርጕሙ፣ “ማክበርን” ያመለክታል።


አክብሮት

“አክብሮት” ለአንድ ሰው ወይም አንዳች ነገር ጥልቅ ስሜትና ክብር ያመለክታል።


አውራጃ

አውራጃ አንድ ወረዳ ወይም የአገር ክፍል ነው።


አውሬ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ስለሌላ “እንስሳ” ለመናገርም ጥቅም ላይ ይውል ነበር


አዛዥ፣ እዝ

“አዛዥ” የተወሰኑ ወታደሮችን የመምራትና የማዘዝ ኃላፊነት ያለውን የሰራዊት መሪ ያመለክታል።


አደባባይ፣ ችሎት

“አደባባይ” ዙሪያውን የተከበበና ከላይ በኩል ክፍት የሆነ ገላጣ አካባቢ ነው።


አዲስ ኪዳን

“አዲስ ኪዳን” የሚለው አገላለጽ የሚያመለክተው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ መሥዋዕት በኩል እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያደረገውን ስምምነት ወይም ውል ነው።


አዲስ ጨረቃ

“አዲስ ጨረቃ” የሚባለው ጨረቃ በመሬት ምሕዋር ዙሪያ ስትጓዝ የሚኖራት የመጀመሪያው ገጽታዋ ነው። በዚህ ጊዜ ጨረቃ ፍጹም ጨለማ መስላ ትታያለች ወይም ጫፏ ላይ ትንሽ ማጭድ መሰል ቅርጽ ያለው ብርማ ብርሃን ይኖራታል።


አጋዘን

አጋዘን ጫካዎች ውስጥ ወይም ተራሮች ላይ የሚኖር ግዙፍና የሚያምር ባለ አራት እግሮች እንስሳ ነው። ወንዱ አጋዘን በጣም ትላልቅ ቀንዶች አሉት።


አጥፊ

ቃል በቃል ሲወስድ፣ “አጥፊ” የሚለው ቃል፣ “የሚያጠፋ ሰው” ማለት ነው።


እህል

ብዙውን ጊዜ፣ “እህል” የሚያመለክተው እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ማሽላ ወይም ሩዝን የመሳሰሉ ለምግብ የሚሆኑ እህል ዘሮችን ነው። አንዳንዴ ዘሩ ራሱን ያመለክታል።


እምነት የሌለው፣ የማያምን

“እምነት የሌለው” የማያምን ወይም ማመን የማይፈልግ ማለት ነው።


እምነት፣ መተማመን

“እምነት” እኛ “መተማመን” አንድ ነገር እውነት መሆኑንና ያም ነገር በእርግጥ የሚፈጸም መሆኑን እርግጠኛ መሆንን ያመለክታሉ። በድፍረትና በልበ ሙሉነት መንቀሳቀስንም ያመለክታሉ።


እረኛ

እረኛ በጎችንና እነርሱን የመሳሰሉ እንስሳትን የሚጠብቅ ሰው ነው


እርሾ፣ የቦካ

እርሾ ሊጥ ኩፍ እንዲል የሚያደርግ ነገር ነው። እርሾ የገባበት ሊጥ የቦካ ይባላል።


እርድ

ብዙውን ጊዜ “ጭፍጨፋ” በአንድ ጊዜ ብዙ እንስሳት ወይም ሰዎችን መግደል ወይም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደል ነው። ማረድ በሚለው ቃል ከተጠቀምን ደግሞ ለመብል እንዲሆኑ ጥቂት እንስሳትን መግደልም ይሆናል


እሳት

እሳት አንድ ነገር ሲቃጠል የሚገኝ ሙቀት፣ ብርሃንና ነበልባል ነው።


እስር ቤት፣ እስረኛ

እስር ቤት የሚያመለክተው በጥፋታቸው እንዲቀቱ ወንጀለኞች የሚጠበቁበትን ቦታ ነው። እስረኛ እስር ቤት ውስጥ የሚጠበቅ ሰው ነው።


እስትንፋስ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “እስትንፋስ” የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ ሕይወትን ለመስጠት ወይም በሕይወት መሆንን ለማመልከት በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ውሏል።


እበት፣ ማዳበሪያ

እበት የእንስሳ እዳሪ ሲሆን፣ መሬትን ለማለስለስ ወይም ለማዳበር በሚውልበት ጊዜ ማዳበሪያ ይባላል።


እባብ

እባብ የዘንዶ ሌላ ስም ነው። በኤደን አትክልት ቦት ከሔውን ጋር በተናገረ ጊዜ ሰይጣን በዚህ ስም ነበር የተጠራው


እብሪት


እኅት

እኅት የምትባለው ቢያንስ በአንዱ ወላጅ ከሌላው ጋር የምትጋራ እንስት ናት


እኔ፣ ያህዌ

ብዙውን ጊዜ ብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ስለ ራሱ ሲናገር በተውላጠ ስም ከመጠቀም ይልቅ፣ በራሱ መጠሪያ ስም ይጠቀማል።


እንከን፣ ነውር

“እንከን” ወይም ነውር አንድ እንስሳ ወይም ሰው ላይ ያለ ጉድለትን ወይም ሙሉ ያለመሆንን ያመለክታል። ሰዎች ላይ ያለ በደልን ወይም መንፈሳዊ ጉድለትንም ያመለክታል።


እንደራሴ(አምባሳደር)፣ተወካይ

እንደ ራሴ(አምባሳደር)ሀገሩን በይፋ በመወከል ለውጪ አገሮች ጋር ግንኙነት እንዲያደርግ የሚመረጥ ሰው ነው፥ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን አንዳንዴ ጠቅለል ባለ ሁኔታ፣ “ተወካይ” ተብሎም ይተረጎማል።


እንጀራ፣ ዳቦ

እንጀራ ውሃና ዘይት ተቀላቅሎ ከተቦካ ዱቄት ሊጥ ይሠራል። ከዚያ ሊጡ የእንጀራውን ወይም የዳቦውን ቅርጽ እንዲይዝ ተደርጎ ይጋገራል።


እጅ፣ ቀኝ እጅ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “እጅ” የሚለው ቃል በምሳሌያዊ አነጋገር በበርካታ ቦታዎች ጥቅም ላይ ውሏል።


ከንቱ፣ ከንቱነት

“ከንቱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ምንም ጥቅም ወይም ዓላማ የሌለውን ነገር ነው። ከንቱ ነገሮች ባዶና እርባነ ቢስ ናቸው።


ከፍታ ቦታዎች

“ከፍታ ቦታዎች” የሚለው ሐረግ የጣዖት አምልኮ መሠዊያና ማምለኪያ ቤት የሚሠራባቸው ኮረብቶች ወይም ተራሮች ላይ ያሉ ቦታዎችን ያመለክታል።


ከፍታ፣ በከፍታ

“ከፍታ” እና “በከፍታ” የተሰኙ ቃሎች ሰማይን የሚያመለክቱ ፈሊጣዊ አነጋገር ናቸው።


ኪሩቤል፣ ኪሩብ

“ኪሩብ” እና “ኪሩቤል” በመባል በብዙ ቊጥር የሚጠሩት እግዚአብሔር የፈጠራቸው የተለዩ ዓይነት ሰማያዊ አካሎች ናቸው። ኪሩቤል ክንፎችና የእሳት ነበልባል እንዳላቸው መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል።


ካባ

ካባ ወንዶችም ሆነ ሴቶች የሚለብሱት እጅጌ ረጃጅም ከውጭ የሚደረብ ልብስ ነው። ከኮት ጋር ይመሳሰላል።


ክራር፣ መሰንቆ

ክራርና መሰንቆ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ለማምለክት የሚጠቀሙባቸው ትናንሽ ባለ ገመድ የሙዚቃ መሣሪያዎች ናቸው።


ክብር

“ክብር” የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ከሀብትና መልክ ጋር የሚያያዝ የላቀ ውበትና ግርማ ያመለክታል


ክፉ አድራጊ

“ክፉ አድራጊ” ኀጢአትና ዐመጻን የሚያደርጉ ሰዎች አጠቃላይ መገለጫ ነው።


ወራሽ

ወራሽ የሚባለው የአንድ የሞተ ሰው ንብረት ወይም ገንዘብ የመቀበል ሕጋዊ ዕውቅና የተሰጠው ሰው ነው።


ወሬ

“ወሬ” አንድን ሁኔታ አስመልክቶ በቃል ወይም በጽሑፍ አንዱ ለሌላው የሚናገረው ነው።


ወርቅ

ወርቅ ቢጫ መልክ ያለው በጣም ውድ ነገር ነው። በጥንት ዘመን ወርቅ ከማንኛውም የበለጠ ውድ ነገር ነበር።

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጣዖቶች፣ ጌጣጌጦች፣ መሠዊያዎች፣ የቃል ኪዳኑ ታቦት የተወሰነ ክፍልና መገናኛው ድንኳን ወይም ቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ነገሮች የሚሠሩት ከወርቅ ነበር። አንዳንዴ፣ “ወርቅ” የሚባለው ወርቅ የተለበጠ እንጂ እውነተኛ ወርቅ ላይሆን ይችላል። በዚህ ጊዜ፣ “ወርቃማ” ወይም፣ “ወርቅ የተለበጠ” በተሰኙ ሐረጎች እንጠቀማለን።


ወርካ

ወርካ ረጅም፣ ትልቅ ግንድና ጥላ የሚሆኑ ሰፋፊ ቅርንጫፎች ያሉት ዛፍ ነው።


ወሲባዊ እርኩሰት

ወሲባዊ እርኩሰት የሚለው ኃረግ በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የከጋብቻ ውጪ የሚፈጸም ወሲብን ያመለክታል። ይህ ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር ይቃረናል።


ወንጀል፣ ወንጀለኛ

“ወንጀል” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው የአንድ አገርን ወይም መንግሥትን ሕግ የማፍረስ ኃጢአትን ነው። እንዲህ ያለውን በደል የፈጸመ ሰው ወንጀለኛ ይባላል።


ወይን መርገጫ

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ወይን መርገጫ የወይን ጠጅ ለመሥራት የወይኑ ፍሬ የሚረገጥበት ቦታ ነው።


ወይን ጠጅ

ወይን ጠጅ ከወይን ፍሬ ጭማቂ የሚሠራ የተብላላ መጠጥ ነው። ያልተብላላው የወይን ፍሬ ጭማቂም በዚሁ ስም ይጠራል።


ወይን ጠጅ ኀላፊ

በብሉይ ኪዳን ዘመን፣ “ወይን ጠጅ ኀላፊ” ለንጉሡ ወይን በጽዋ የሚያቀርብ ሰው ሲሆን፣ ወይኑ ያልተመረዘ መሆኑን ለማረጋገጥ ብዙውን ጊዜ ኀላፊው መጀመሪያ እንዲቀምስ ይደረግ ነበር።


ወዳጅ (አፍቃሪ)

“ወዳጅ” የሚለው ቃል፣ “የሚወድ ሰው” ማለት ሲሆን ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ግብረ ሥጋዊ ግንኙነት ያላቸው ሰዎችን ነው።


ወገብ

ወገብ በታችኛው ጎድንና በዳሌ አጥንት መካከል የሚገኝ የሰው ወይም የእንስሳ አካል ክፍል ነው፣ አንዳንዴ ታችኛው የሆድ ዕቃም ይባላል።


ወጥመድ፣ አሽከላ

“ወጥመድ” እና፣ “አሽከላ” የተሰኙት ቃሎች እንስሶችን ለመያዝና ከዚያ እንዳያመልጡ ለመድረግ ጥቅም ላይ የሚውሉ ነገሮች ናቸው። የሚጠመደውን እንስሳ በድንገት እንደያዘው ብዙውን ጊዜ ወጥመዱ ወይም አሽክላው ድብቅ ቦታ ላይ ይቀመጣል


ዋሽንት

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ዋሽንት ከአጥንትና ከእንጨት የሚሠራ የሙዚቃ መሣሪያ ሲሆን ድምፅ እንዲያወጣ መተላለፊያዎች ይሠሩለትም ነበር።


ዋጋ፣ ሽልማት

ይህ ቃል የሚያመለክተው መልካምም ሆነ ክፉ አንድ ሰው ላደረገው የሚቀበለውን ነገር ነው። “ዋጋ መስጠት” የሚያመለክተው የሚገባውን ነገር ለሰው መስጠትን ነው።


ውሃ፣ ውሆች

ከመጀመሪያው ትርጕሙ በተጨማሪ፣ “ውሃ” - እንደ ውቅያኖስ፣ ባሕር፣ ሐይቅ ወይም ወንዝን የመሳሰሉ የውሃ አካል ይጨምራል።


ውድ፣ የተወደደ፣ ክቡር

“ውድ” የሚለው ቃል በጣም የተወደዱ፣ በጥቂቱ የሚገኙ ወይም ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸውን ሰዎች ወይም ነገሮችን ያመለክታል።


ዐመድ

“ዐመድ” የሚለው የሚያመለክተው እንጨት ከተቃጠለ በኋላ የሚቀረውን ግራጫ ዱቄት መሳይ ነገርን ነው። ዋጋ ቢስ ውይም ጥቅም የሌለውን ነገር ለማመልከት ምሳሌያዊ በሆን መልኩ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።

የትርጉም ሥራው ፕሮጀክት በሚጠቀምበት ቃል ተጠቀሙ


ዐምድ፣ ምሰሶ

“ዐምድ” ጣራ ወይም ሌላውን የሕንጻ ክፍል ደግፎ ለመያዝ የሚያገለግል ቀጥ ብሎ የሚቆም ነገር ነው። “ምሰሶ” የዐምድ ሌላ ስም ነው።


ዐዋጅ

ዐዋጅ የሚባለው ሕግን ወይም መምሪያን ለሰዎች በአደባባይ በግልጽ መናገር ነው።


ዐይነት፣ ዐይነቶች

“ዐይነት” እና “ዐይነቶች” የሚባሉት ባሕርያትን በመጋራት የተያያዙ ነገሮች ቡድን ወይም ምድብ ናቸው።


ዓሣ አጥማጆች

ዓሣ አጥማጆች ለመግብ የሚሆናቸውንና ሸጠው ገንዘብ የሚያገኙበትን ዓሣ ከባሕር የሚያጠምዱ ሰዎች ናቸው። አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ዓሣ አጥማጆች ዓሣ የሚያጠምዱት በመረብ አማካይነት ነበር።


ዓሣማ፣ እሪያ

ዓሣማ ሰዎች ለምግብነት የሚያረቡት ባለ አራት እግርና ሸኾና ያለው እንስሳ ነበር። ሥጋው የዓሣማ ሥጋ ይባላል።


ዕረፍት

“ዕረፍት” የሚለው ቃል ዘና ለማለትና ኀይልን ለማደስ የሚሠሩትን ማቆም ማለት ነው።


ዕቁባት

ዕቁባት ቀድሞውኑ ሚስት ያለችው ወንድ ሁለተኛ ሚስት ናት። ብዙውን ጊዜ ዕቁባት የሰውየው ሕጋዊ ሚስት አትሆን።


ዕቡይ

ዕቡይ ሰው ከሚገባው በላይ ስለ ራሱ ከፍ ያለ ግምት አለው።

ከ . . . ጋር ግንኙነት፣ ከ . . . ጋር መተኛት፣ አብሮ ተኛ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እነዚህ ቃሎች በተዘዋዋሪ ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን የሚያመለክቱ ናቸው።


ዕቡይ/ትዕቢተኛ፣ ትዕቢት፣ ኩራት፣ ኩሩ

“ትዕቢተኛ” እና፣ “ትዕቢት” ስለ ራሱ ከፍ ያለ ሐሳብ ያለውንና ከሌሎች የበለጠ እንደ ሆነ የሚያስብን ሰው ያመለክታል።


ዕጣ፣ ዕጣ መጣል (ማውጣት)

“ዕጣ” አድልዎ የሌለበት ምርጫ ወይም ውሳኔ ለማድረግ ሲታሰብ ሰዎች ምልክት የተደረገባቸው ተመሳሳይ ነገሮችን ይጥላሉ ወይም ከሌሎች ተመሳሳይ ነገሮች መካከል አንዱን ማንሣት ማለት ነው። እግዚአብሔር ምን እንዲያድረርጉ እንደሚፈልግ ማወቅ የሚፈልጉ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ዕጣ በመጣል ዕጣ በማውጣት ይጠቀሙ ነበር።


ዕጣን

ዕጣን ከዛፍ ሙጫ የሚገኝ ጣፋጭ ሽታ ያለው ቅመም ነው። ሽቱኑ ሌላም ጣፋጭ መዓዛ ያለው ነገር ለመሥራት ያገለግላል።

ነጻ መሆን፣ ነጻነት፣ አርነት “ነጻ መሆን” ወይም፣ “ነጻነት” ባርያ አለመሆንን በምንም ዓይነት ቀንበር ሥር አለመሆንን ያመለክታል።


ዕጣን

ዕጣን እሳት ላይ በሚደረግበት ጊዜ ደስ የሚል ሽታ የሚሰጥ ጣፋጭ መዓዛ ያላቸው ቅመሞድ ድብልቅ ነው። እነዚህ ቅመሞች ከዕፅዋት ክፍሎች የተገኙ ሲሆኑ፣ በጣም ጥቃቅን እስኪሆኑ ድረስ ይደቅቃሉ።


ዕፍረት፣ አሳፋሪ፣ አፈረ

ዕፍረት አንድ ሰው ወይም ሌላው ካደረገው መጥፎ ወይም ተገቢ ያልሆነ ነገር የተነሣ የሚደርስ ውርደት ወይም ጥሩ ስሜት እንዳይኖር የሚያደርግ ሕመም ነው


ዘላለም

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ዘላለም” የሚያመለክተው ፍጻሜ የሌለውን ጊዜ ነው። አንዳንዴ፣ በታም ረጅም ጊዜን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።


ዘመን/ዕድሜ

“ዘመን/ዕድሜ” አንድ ሰው የኖረበት ዓመት ቁጥር ያመለክታል አጠቃላይ በሆነ መልኩ ጊዜን ወይም ወቅትን ያመለክታል።


ዘመድ

“ዘመድ” በሥጋና በደም የቅርብ ግንኙነት ያለው ሰው ነው።


ዘራ፣ ዘሪ

መዝራት ተክል ለማግኘት ዘሮችን ምድር ውስጥ ማኖር ማለት ነው። ይህን የሚያደርግ ሰው፣ “ዘሪ” ይባላል


ዘር

ዘር እርሱን የመሳሰሉ ብዙ ዘሮች እንዲገኙ መሬት ላይ የሚዘራ ወይም የሚተከል የአትክልት ክፍል ነው። በርካታ ምሳሌያዊ ትርጉሞችም አሉት


ዘር (ልጅ)

ዘር (ልጅ) ቀጥተኛ የደምና ሥጋ ዝምድና ያለው ወይም የሩቅ ዘመድ የሆነ ሰው ነው።


ዘንባባ

“ዘንባባ” ረጃጅም፣ በቀላሉ የሚተጣጠፍ፣ ከጫፉ ጀምሮ እንደማራገቢያ ዓይነት ቅጠል ያበዛባቸው ቅርንጫፎች ያሉት ረጅም የዛፍ ዘር ነው።


ዘይት

ዘይት ከአንዳንድ ተክሎች ወይም ፍሬዎች ሊገኝ የሚችል ወፈር ያለ ፈሳሽ ነገር ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን አብዛኛውን ጊዜ ዘይት የሚገኘው ከወይራ ፍሬዎች ነው።


ዙፋን

ዙፋን አብዛኛውን ጊዜ ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ለመስጠት ንጉሥ የሚቀመጥበት የተለየ ወንበር ነው።


ዙፋን

ዙፋን አብዛኛውን ጊዜ ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ለመስጠት ንጉሥ የሚቀመጥበት የተለየ ወንበር ነው።


ዜና መዋዕል

“ዜና መዋዕል” የሚለው ቃል በዘመናት ውስጥ በጽሑፍ የሰፈረ ሰነድን ነው።


ዜጋ

አንድ ዜጋ በአንድ የተወሰነ አገር ወይም መንግሥት ውስጥ የሚኖር ሰው ነው። በተለይም የዚያ አገር ነዋሪ መሆኑን በልጽ ዕውቅና የተሰጠው ሰውን ያመለክታል።


ዝሙርት አዳሪነት፣ ግልሙትና

“ዝሙት አዳሪነት” ወይም፣ “ግልሙትና” ገንዘብ ለማግኘት ወይም፣ ለሃይማኖታዊ ሥርዓት የግብረ ሥጋ ግንኙነትን የሚፈጽም ሰው ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ ዝሙት አዳሪዎችና ጋለሞቶች ሴቶች ቢሆኑም፣ አንዳንዴ ወንዶችም ሊሆኑ ይችላሉ።


ዝቅተኛ፣ ዝቅተኝነት

“ዝቅተኛ” እና፣ “ዝቅተኝነት” የተሰኙት ቃሎች ድህነትን ወይም ዝቅ ያሉ ማንነትና ደረጃን ያመለክታሉ።


ዝግባ

“ዝግባ” የሚለው ቃል ቀይ ቡናማ እንጨት ያለው ሾጣጣ ጫፍ ያለውን ግዙፍ ዛፍ ያመለክታል። እንደ ሌሎች ሾጣጣ ዛፎች ሁሉ እንደ መርፌ የሾሉ ቅጠሎች አሉት።


የሐሰት ምስክር፣ ጠማማ ምስክር፣ ሐሰተኛ ወሬ

“ሐሰተኛ ምስክር” እና “ጠማማ ምስክር” ሰዎችን ወይም ሁኔታዎችን በተመለከተ እውነቱን የማይናገር ሰው ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እንዲህ ሲደረግ የሚታየው በመደበኛ ፍርድ ቦታ ነው።


የሕይወት መጽሐፍ

“የሕይወት መጽሐፍ” የሚለው ቃል እርሱ ያዳናቸውንና የዘላለም ሕይወት ያሰጣቸውን ሰዎች ስም የጻፈበትን መዝገብ ያመለክታል።


የመጠጥ ቍርባን

የመጠጥ ቍርባን ወይን ጠጅ መሠዊያ ላይ ማፍሰስን የሚያካትት ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ነው። ብዙውን ጊዜ የሚቀርበው ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከእህል መሥዋዕት ጋር በአንድነት ነው።


የመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን፣ ቀን

“ቀን” ቃል በቃል 24 ሰዓት ውስጥ ያለው ጊዜ ነው። ምሳሌያዊ ሆነ መንገድም ጥቅም ላይ ይውላል።


የመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ ወር

“ወር” ሲባል አራት ሳምንት ገደማ ያለው ወቅ ነው። እንደምንጠቀምበት የጊዜ አቆጣጠር (በጨረቃ ወይም በፀሐይ) መሠረት አንድ ወር ውስጥ ያሉ ቀኖች ሊለያዩ ይችላሉ።


የመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ፣ ሰዓት

ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዓቱ የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለው አንድ ነገር የተፈጸመበትን ጊዜ ለይቶ ለመናገር ነው።


የመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ፤ ሳምንት

ሳምንት ሰባት ቀኖች ያሉት ጊዜ ነው።


የመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ፤ ትጋት

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ትጋት” ይባል የነበረው አንድ የከተማ ጠባቂ ወይም ዘበኛ ጠላት ከሚሰነዝረው የትኛውም ጥቃት ለመጠበቅ ግዳጅ ላይ የሚሆንበት የሌሊቱ ጊዜ ነው።


የመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ፤ ዓመት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃል በቃል ጥቅም ላይ ከዋለ፣ “ዓመት” 354 ቀኖች የያዙ ጊዜን ያመለክታል። ይህ ጨረቃ በምድር ዙሪያ ለመዞር የሚወስድባትን ጊዜ መጸት እንደማይደርገው እንደ ጨረቃ አቆጣጠር ነው።


የሚቃጠል መሥዋዕት፣ በእሳት መሠዋት

“የሚቃጠል መሥዋዕት” የሚባለው መሠዊያው ላይ በእሳት ተቃጥሎ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ዐይነት ነው። የሚቃጠለው ለሕዝቡ ኀጢአት ስርየት ለመሆን ነው። “በእሳት መሠዋት” ተብሎም ይጠራል።


የሚያሰክር መጠጥ

“የሚያሰክር መጠጥ” የሚለው ቃል፣ የተብላሉ መጠጦችን ያመለክታል፣ “አልኮል” መጠጥም ይባላል


የሚያስደስት

«የሚያስደስ ነገር» ማለት ሰውን በእጅጉ የሚያስደት ወይንም በዙ ሐሴትን የሚያመጣ ነገር ማለት ነው በ አንድ ነገር መደሰት ማለት


የማኅፀን ፍሬ

የማኅፀን ፍሬ በሥጋና በደም ከሰዎች ወይም ከእንስሳት ለሚወዱ ሁሉ የሚሰጥ አጠቃላይ ቃል ነው።


የማይጠቅም

“የማይጠቅም” አንዳች ጠቀሜታ የሌለው ማለት ነው።


የምግብ ቁርባን

“የምግብ ቁርባን” የሚባለው ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚቀርብ እህል ወይም እንጀራ ነው።


የምጥ ጣር

“ምጥ” ላይ ያለች ሴት ልጅ ከመውለዷ በፊት ሕመም ይደርስባታል፤ ይህም “የምጥ ጣር” ይባላል።


የራስ ቅል

የራስ ቅል የአንድ ሰው ራስ አጥንት የሆነው ክፍል ነው


የስብሰባ ድንኳን

እግዚአብሔር በሲና ተራራ ሕጉን በሰጠ ጊዜ የስብሰባ ድንኳን እንዲሠሩ ለእስራኤላውያን ተናግሮ ነበር። ይህ ከእነርሱ ጋር የሚገናኝበት የተቀደሰ ቦታ ነበር። በምድረ በዳ በሚጓዙበት ጊዜ ይዘውት ይሄዱ ነበር፤ እግዚአብሔር ሲነግራቸው መልሰው ይተክሉት ነበር። * የስብሰባው ድንኳን የእንጨት ማዕቀፎች ላይ በተዘረጋ ጨርቅ የተሠራ ቤት ነበር።


የበላይ ተመልካች

የበላይ ተማልካች የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው የሌሎች ሰዎች መብትና ጥቅም መከበሩን የመቆጣጠር ሥራ በኅላፊነት የሚከታተል ሰው ነው።


የበደል መሥዋዕት

“በደል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኀጢአት ማድረግን ወይም ወንጀል መፈጸምን ነው።


የበጎ ፈቃድ ስጦታ

የበጎ ፈቃድ ስጦታ ማለት የአይሁድ ሕግ ከሚጠይቀው መሥዋዕት የበለጠ ወይም ያለፈ መሥዋዕት ማለት ነው።


የበጎ ፈቃድ ስጦታ

የፈቃደኝነት መሥዋዕት ማለትበሙሴ ሕግ ያልተጠየቀ የመሥዋዕት አይነት ነው። የበጎ ፈቃድ ስጦታ ማለት የአይሁድ ሕግ ከሚጠይቀው መሥዋዕት የበለጠ ወይም ያለፈ መሥዋዕት ማለት ነው።


የባሕር አውሬ

“የባሕር አውሬ” ውቅያኖስ ወለል ላይ ያሉትን የባሕር ሣሮችንና ተክሎችን የሚበላ ግዙፍ የባሕር እንስሳ ነው


የቤት እንስሶች

“የቤት እንስሶች” የሚባሉት ምግብና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮች ለማግኘት ሰፈር ውስጥ የሚያድጉ እንስሳት ናቸው።


የተማሩ ሰዎች፣ ኮኮብ ቆጣሪዎች

ማቴዎስ በሚያቀርበው የክርስቶስ ልደት ታሪክ መሠረት እነዚህ፣ “የተማሩ” ወይም፣ “ያወቁ” ሰዎች ኢየሱስ በቤተ ልሔም በተወለደ ጊዜ እዚያ ድረስ ስጦታዎች ያመጡለት “ጠቢብባን ሰዎች” ነበር። ምናልባትም ከዋክብትን የሚያጠኑ ኮከብ ቆጣሪዎች ለሆኑ ይችላሉ።


የተቀደሰ

“የተቀደሰ” የሚለው ቃል ቅዱስ የሆነና ለእግዚአብሔር ክብር የተለየ ነገርን ያመለክታል


የተጠላ፣ መጥላት

“የተጠላ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የማይወደድና የተናቀ ነገር ነው። አንድን ነገር “መጥላት” ያንን ነገር አጥብቆ አለመውደድ ማለት ነው።


የተጻፈ

“እንደ ተጻፈ” ወይም፣ “የተጻፈው” የተሰኙት ቃሎች አዲስ ኪዳን ውስጥ ተደጋግመው ጥቅም ላይ ውለዋል፣ ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት በዕብራውያን ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉ ትእዛዞች ወይም ትንቢቶች ነው።


የኅብረት መሥዋዕት

“የኅብረት መሥዋዕት” እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር እንዲያቀርቡ ከታዘዙት በርካታ የመሥዋዕት ስጦታዎች አንዱ ነበር። “የምስጋና መሥዋዕት” ወይም፣ “የሰላም መሥዋዕት” ተብሎም ይጠራል።


የኅብረት መሥዋዕት፣ የሰላም መሥዋዕት

የኅብረት መሥዋዕት ብሉይ ኪዳን ውስጥ የሰላም መሥዋዕት ተብሎ ይጠራል። ተባዕት ወይም እንስት እንስሳ መሥዋዕት የሚቀርብበት ነው።


የኅጢአት መሥዋዕት

የኅጢአት መሥዋዕት ለተፈጸመው ኅጢአት ይቅርታ ለማግኘት ይቀርብ የነበረ መሥዋዕት ነበር


የአይሁድ መሪዎች፤ የአይሁድ ባለ ሥልጣኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች

የአይሁድ መሪዎች ካህናትንና የሕግ ምሑራንን የመሳሰሉ የሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።


የእህል ቍርባን

የእህል ቍርባን የሚባለው ብዙውን ጊዜ ከሚቃጠል መሥዋዕት በኋላ ለእግዚአብሔር የሚቀርበውን የስንዴ ወይም የገብስ ዱቄት ነው።


የእውነት ቃል

“የእውነት ቃል” የእግዚአብሔር ቃል ወይም ትምህርት ሌላ መጠሪያ ነው።


የእግር መረገጫ

“የእግር መረገጫ” አንድ ሰው እግሮቹን በተለይም በሚቀመጥ ጊዜ እግሮቹን የሚያሳርፍበት ነገር ነው። መገዛትንና ዝቅ ያለ ማንነትን የሚያመለክት ትርጕም ያለው ምሳሌያው ቃልም ነው።


የካህናት አለቆች

ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ጊዜ የካህናት አለቆች ከፍ ያለ ሥልጣን የነበራቸው የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።


የወይራ ፍሬ

የወይራ ፍሬ ከወይራ ዛፍ የሚገኝ ትንሽ ሾጣጣ ቅርጽ ያለው ፍሬ ሲሆን፣ አብዛኛውን ጊዜ የሚገኘው በሜድትራኒያን ባሕር አካባቢዎች ነው።


የወይን እርሻ

የወይን እርሻ ወይም ልማት ወይን የሚበቅልበት ወይን፣ በእንክብካቤ የሚያድግበት ቦታ ነው።


የወይን ዛፍ

“የወይን ዛፍ” ወይን የሚያፈራ የዛፍ ዓይነት ነው።


የወይን ፍሬ

ወይን ፍሬ የወይን ሐረጉ እዚህና እዚያ ተበታትነው የሚያድጉ ትናንሽ ክብ ፍሬዎች ናቸው። ወይን ጠጅ የሚሆነው እነዚህ ፍሬዎች ተጨምቀው ነው።


የዋህ፣ የዋህነት

“የዋህ” የሚለው ቃል ጨዋ፣ እሺ ባይና መከራን በትዕግሥት የሚቀበልን ሰው ያመለክታል። መናደድ ኀይል መጠቀም ተገቢ መስሎ ቢታይ እንኳ ጨዋ ሆኖ ለመገኘት የዋህነት ታላቅ ችሎታ ነው።


የዕጣን መሠዊያ


የደም መፍሰስ

“የደም መፍሰስ” በግድያ፣ በጦርነት ወይም በሌላ አደጋ የሰዎችን ሞት ያመለክታል።


የገሊላ ባሕር

የገሊላ ባሕር ምሥራቃዊ እስራኤል ያለ ሐይቅ ነው። የገሊላ ባሕር በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ወደ ደቡብ ከዚያም ወደ ሙት ባሕር ይፈስሳል።


የግብረ ሥጋ ኅጢአት

“የግብረ ሥጋ ኅጢአት” የሚባለው በወንድና በሴት መካከል ካለው ጋብቻ ውጪ የሚደረግ ማንኛውም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ነው። እንዲህ ያለው ከእግዚአብሔር ዕቅድ ውጪ ነው።


ያልተገረዘ፣ አለመገረዝ

“ያልተገረዘ” እና “አለመገረዝ” አካላዊ ግርዘት ያላደረገ ወንድን ያመለክታል። ይህ ቃል በምሳሌያዊ አንጋገርም ጥቅም ላይ ይውላል።


ያልተፈቀደ

“ያልተፈቀደ” ነገር የሚያደርግ ሰው ሕግ ያፈርሳል።


ያልታመነ፣ አለመታመን

“ያልታመነ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እንዲያደርግ እግዚአብሔር ያዘዘውን ነገር የማያደርገውን ሰው ነው። እንዲህ ማድረግ አለመታመን ነው።


ይሁዳ፣ የይሁዳ ሃይማኖት

የአይሁድ ሕዝብ የሚለማመደውን ሃይማኖት ማለትም የአይሁድ ሃይማኖትን ለማመልከት አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ዘመን አንስቶ እስከዚህ ዘመን ድረስ፣ “ይሁዲ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።


ደስታ፣ ደስተኛ

ደስታ የደስታ ስሜት ወይም ከእግዚአብሔር የሚመጣ ጥልቅ ርካታ ነው። ከዚሁ ጋር ታያያዥ የሆነው፣ “ደስተኛ” የሚለው ቃል በጣም ደስ የተሰኘ ሰውን ያመለክታል።


ደብዳቤ፣ መልእክት

ደብዳቤ ብዙ ጊዜ ከጸሐፊው ርቀው ላሉ ወገኖች ወይም ሰዎች የሚላክ መልእክት ነው። መልእክት የተለየ ዐይነት ደብዳቤ ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ የሚጻፈው ማስተማርን ለመሰሉ የተለዩ ዓላማ ነው።


ደጃፍ

“ደጃፍ” የሚባለው የበር ታችኛው ክፍል ነው። ወደ አንድ ቤት ሲገባ ደጃፉን መርገጥ ይገባል።


ደጋንና ቀስት

ይህ ከደጋን ገመድ ቀስትን ማስፈንጠርን የሚያካትት መሣሪያ ዐይነት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጠላትን ለማጥቃት ወይም ለምግብ የሚሆን እንስሳን ለመግደል ያገለግል ነበር።


ደፋር፣ በድፍረት፣ ድፍረት

እነዚህ ቃሎች አስቸጋሪና አደገኛ ቢሆን እንኳ እውነትን ለመናገርና ትክክለኛውን ለማድረግ ደፋርና ጎበዝ መሆንን ነው የሚያመለክቱት።


ዳኛ፣ ፈራጅ

አስተዳደራዊ፣ ሕጋዊ ወይም መንፈሳዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ትክክልና ስሕተት የሆኑ ነገሮችን የሚወስን ሰው ዳኛ ወይም ፈራጅ ይባላል።


ድምፅ

አንድ ሰው ሲናገር ድምፅ ይጠቀማል፤ ስለዚህም ብዙ ጊዜ “ድምፅ” ንግግርን ወይም ሐሳብ ማስተላለፍን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።


ድብ

ድብ ጥቁር ቡናማ ጠጉርና ጠንካራ ጥርሶችና ጥፍሮች ያሉት ባለአራት እግር ግዙፍ እንስሳ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ድብ በእስራኤል በብዛት ይገኝ ነበር


ድነት

“ድነት” የሚለው ቃል ከክፉና ከአደጋ መዳንና ማምለጥን ያመለክታል


ድንኳን

ድንኳን ተንቀሳቃሽ መጠለያ ሲሆን፣ የሚሠራው ምሰሶዎች ላይ በማንጠልጠሉና ከእንርሱ ጋር በተያያዙ ጠንካራ ጨርቅ ነበር።


ድንጋይ

ይህ ቃል የሚያመለክተው ከሰማይ የሚወርድ ጠጣር ነገርን ነው።


ድንግል

ድንግል የግብረ ሥጋ ግንኙነት ያላደረገች ሴት ናት።


ድኝ

“ደኝ” ቢጫ መልክ ያለው ንጥረ ነገር ሲሆን፣ እሳትን በማቀጣጠልም ይረዳል


ድፍረት፣ ደፋር

“ድፍረት” አስቸጋሪ፣ አስፈሪ ወይም አደገኛ ነገሮችን በጉብዝና መጋፈጥ ወይም አንድ ነገር ማድረግ ማለት ነው።


ገለባ

ደረቅ የእህል ዘር መከላከያ ሽፋን ነው። ገለባ ለምግብነት አይጠቅምም፤ ስለዚህም ከእህሉ እንዲለያይ ይደረግና በኋላ ይጣላል።


ገብስ

“ገብስ” እንጀራ ወይም ዳቦ ለማዘጋጀት የሚጠቅም የእህል አይነት ነው


ገዢ፣ መግዛት

ገዢ፣ አገርን፣ አካባቢን ወይም ክልልን የሚገዛ ሰው ነው። “መግዛት” ሰዎችን ወይም ነገሮችን መምራት ወይም ማስተዳደር ማለት ነው።


ገዢ፣ ገዦች፣ ግዛት

ገዢ እንደ አገር መሪ፣ መንግሥት ወይም ሃይማኖታዊ ድርጅት ላይ ሥልጣን ያለውን ሰው የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ነው


ጉቦ፣ መማለጃ

“ጉቦ” ወይም መማለጃ፣ ትክክል ወይም ተገቢ ያልሆነ ነገር እንዲያደርግ እዚያ ሰው ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ገንዘብን የመሰለ አንዳች ዋጋ ያለው ነገር መስጠት ማለት ነው።


ጉድጓድ

ጉድጓድ ወደ መሬት በጣም ዝቅ ብሎ የተቆፈረ ድንጋይ ነው።


ጉድጓድ፣ ውሃ ማጠራቀሚያ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ጉድጓድ” እና “ውሃ መያዣ” ሁለት የተለያዩ የውሃ መገኛ ቦታዎችን ነበር የሚያመለክተው።


ጊዜ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ጊዜ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የተወሰኑ ነገሮች የተፈጸሙበትን ወቅት ወይም ዘመን ለማመልከት ነው። “ዕድም” ወይም፣ “ዘመን” ወይም “ወቅት” ጋር የሚመሳሰል ትርጕም አለው።


ጊደር

ጊደር ገና ያልወለደች ወጣት ላም ናት። ወራሽ ወራዕ የሚባለው የአንድ የሞተ ሰው ንብረት ወይም ገንዘብ የመቀበል ሕጋዊ ዕውቅና የተሰጠው ሰው ነው።


ጋሻ

ጋሻ ከሚወረወር ፍላጻና ከሌሎችም ጠላት ከሚሰነዝራቸው ጥቃቶች ራሱን ለመከላከል አንድ ወታደር በጦርነት ይይዘው የነበረ ነገር ነበር ለአንድ ሰው ጋሻ መሆን እርሱን ከአደጋ መከለከል ማለት ነው


ጌታ

ጌታ የሚለው ቃል ሰዎች ላይ ባለቤትነት ወይም ሥልጣን ያለውን ሰው ያመለክታል።


ግመል

ግመል ጀርባው ላይ አንድ ወይም ሁለት ሻኛ ያለው ግዙፍ ባለ አራት እግር እንስሳ ነው።


ግራር

“ግራር” የተሰኘው ቃል በጥንት ዘመን በከነዓን ምድር ይበቅል የነበረው በብዛት ይገኝ የነበረው ቁጥቋጦ ወይም ዛፍ ስም ነው። ዛሬም ቢሆን በዚያ አካባቢ በብዛት ይገኛል።


ግብር

ግብር ከለላ ለማግኘትና በሕዝቦቻቸው መካከል መልካም ግንኙነት እንዲኖር አንድ መንግሥት ወይም ገዢ ለሌላው የሚያቀርበው ስጦታ ነው።


ግብዣ

ብዙውን ጊዜ ግብዣ የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች የሚቀርቡበት ታዋቂ ሰፊ ድግስ ነው


ግዙፍ

ግዙፍ የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ያልተለመደ ቁመትና ጉልበት ያለውን ሰው ነው።


ጎረቤት

አብዛኛውን ጊዜ ጎረቤት የሚባለው በአካባቢው የሚኖር ሰው ነው። ይበልጥ አጠቃላይ በሆነ መልኩ፣ በምትኖሩበት ማኅበረ ሰብ ወይም የሰዎች ስብስብ ውስጥ የሚኖር ሰውን ያመለክታል።


ጎርፍ

ብዙውን ጊዜ ጎርፍ የሚባለው ምድሩን ሁሉ የሚሸፍን ብዛት ያለው ውሃ ነው። የአንድን ነገር ብዛት ወይም በድንገት ነገር ለማመልከትም ምሳሌያው በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።


ጎሳ

“ጎሳ” ከአንድ አባት የተገኙ ረጅም ሐረግ ያለው ቤተ ሰብ አካሎች ናቸው።


ጎተራ

“ጎተራ” ምግብ ወይም ሌሎች ነገሮችን ለማከማቸት የሚያገለግል ማስቀመጫ ነው


ጠላት/ባለጋራ

“ጠላት/ባለጋራ” አንዳንድ ሰው ወይም አንድን ነገር የሚቃወም ሰው ወይም ሰዎች ማለት ነው።


ጠማማ፣ የተጣመመ

“ጠማማ” ግብረ ገባዊ ወልጋዳነት ወይም ገዳዳነት ያለውን ሰው ወይም ተግባር ለሚመለከት ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። “የተጣመመ” - ወልጋዳ ማለት ነው።


ጠባቂ

“ጠባቂ” አንድ ነገር በጥንቃቄ የሚመለከት፣ ረጋ ብሎና ቀረብ ብሎ በማስተዋል የሚመረምር ማለት ነው። ቃሉ በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።


ጠብ

ጠብ በሰዎች መካከል ያለ አካላዊ ወይም ስሜታዊ ግጭት ማለት ነው


ጠንቃቃ

“ጠንቃቃ” የሚለው ቃል ስለሚሠራው ነገር ረጋ ብሎ የሚያስብና ትክክለኛ ውሳኔ የሚያደርግ ሰውን ይገልጣል።


ጠንካራ፣ ጥንካሬ

“ጠንካራ” የሚለው ቃል እንደ ዐውዱ ሁኔታ የተለያዩ ትርጕሞች ይኖሩታል። ብዙዎን ጊዜ የሚያመለክተው አስቸጋሪ፣ አዳጋች ወይም የማይበገር ነገርን ነው።


ጢቢብ፣ ጥበብ

“ጠቢብ” የሚለው ቃል መልካምና ግብረ ገባዊ ነገሮችን የሚረዳና በተረዳው መሠረት የሚኖር ሰው ነው። እውነትና ግብረ ገባዊ የሆኑ ነገሮችን መረዳት፣ “ጥበብ” ይባላል።


ጣዖት፣ ጣዖት አምላኪ

ጣዖት እርሱን ለማምለክ ሰዎች የሚያበጁት ነገር ነው። ከአንዱ እውነተኛ አምላክ ይልቅ ለአንዳች ሌላ ነገር ክብር ሲሰጥ ያ ጣዖት አምልኮ ይባላል።


ጥላ

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ጥላ” ብርሃን ሲጋረድ የሚፈጠረውን ጨለማ ያመለክታል። በርካታ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት


ጥልቆ/ጥልቁ

“ጥልቅ/ጥልቁ”የሚለው ቃል በጣም ሰፊና ጥልቅ ጉድጓድን ወይም ማለቂያ የሌለው ሸለቆን ያመለክታል


ጥሩር

ጥሩር የሚባለው በጦርነት ጊዜ ወታደሩን ለመከለል ደረትን የሚሸፍን መሥራሪያ ነው። እስራኤላዊው ሊቀ ካህን ይለብስ የነበረው ልዩ ዐይነት ልብስ ክፍል ጥሩር ይባል ነበር።


ጥርስ ማፋጨት

ጥርስ ማፋጨት ማለት ጥርሶችን በማያያዝ ወደ ፊት ወደ ኋላ በማድረግ ወይም ግራና ቀኝ በማድረግ እርስ በርሳቸው እንዲፋጩ ማድረግ ማለት ነው። ይህ ብዙውን ጊዜ የሚያሳየው ከባድ ስቃይን (ሕመምን) ወይም ቊጣን ነው።


ጥቅልል መጽሐፍ

በጥንት ዘመን ጥቅልል ከአንድ ረጅም የፓፒረስ ገጽ ወይም ከቆዳ የሚሠራ የመጽሐፍ ዓይነት ነበር። ጥቅልሉ ላይ ከተጻፈ ወይም ከተነበበ በኋላ ሰዎች ጫፉ ላይ ትንሽ በትር መሳይ ነገር በማኖር ይጠቀልሉት ነበር


ጥቅም፣ ጠቃሚ

በአጠቃላይ “ጠቃሚ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሚገኝ መልካም ነገርን ነው። ለራሱ መልካምነገር የሚያስገኝ ወይም ለሌሎች መልካም ነገር የሚያስገኝ ከሆነ አንድ ነገር ጠቃሚ ነው ይባላል።


ጥድ

ጥድ ዓመቱን ሙሉ አረንጓዴ የሆነ፣ ዘሩን የሚይዝበት ሾጣጣ መያዣዎች ያሉት የዛፍ ዓይነት ነው።


ጥፋት

ጥፋት የሚለው ቃል ምንም ይግባኝ ወይም ማምለጫ የሌለው ፍርድና ኩነኔን ያመለክታል።


ጦር

ጦር በአንድ በኩል ሹል ብረት ያለው ሆኖ ጠላት ላይ የሚወረወር ረጅም እጀታ ያለው መሣሪያ ነው


ጨለማ

ቃል በቃል፣ “ጨለማ” የብርሃን አለመኖር ማለት ነው። ይህ ቃል የተለያዩ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።


ጽድቅ የሌለበት፣ ኀጥእ

“ጽድቅ የሌለበት” ኀጢአተኛና ምግባረ ምልሹ ማለት ሲሆን፣ “ኀጥእ” ኀጢአት ማድረግን ወይም፣ ኀጢአተኛ መሆንን ያመለክታል።


ጽድቅ የሌለበት፣ ኀጥእ

“ጽድቅ የሌለበት” ኀጢአተኛና ምግባረ ምልሹ ማለት ሲሆን፣ “ኀጥእ” ኀጢአት ማድረግን ወይም፣ ኀጢአተኛ መሆንን ያመለክታል።


ጽድቅ የሌለበት፣ ኀጥእ

“ጽድቅ የሌለበት” ኀጢአተኛና ምግባረ ምልሹ ማለት ሲሆን፣ “ኀጥእ” ኀጢአት ማድረግን ወይም፣ ኀጢአተኛ መሆንን ያመለክታል።


ጾም

መጾም ምግብን ወይም አንዳንድ የምግብ ዐይነቶችንና መጠጦችን ለተወሰነ ጊዜ ማቆም ነው።


ፈረሰኛ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን “ፈረሰኛ” የሚባለው ብዙውን ጊዜ ፈረስ ላይ ሆኖ ወደ ጦርነት የሚሄድ ሰው ነበር።


ፈረስ

ፈረስ ግዙፍ ባለ አራት እግር እንስሳ ሲሆን፣ መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን በአብዛኛው ለእርሻ ሥራና ለሰዎች መጓጓዣ ያገለግል ነበር።


ፈራጅ፣ ፈራጆች

ፈራጅ ሕግን በሚመለከቱ ጉዳዮች የመዳኘትና የመወሰን ሥልጣን እንዲኖረው የተሾመ ባለ ሥልጣን ነው።


ፊት

“ፊት” የሚለው ቃል የአንድ ሰው ራሱ ከፊት በኩል ያለውን ክፍል ነው፤ ቃሉ አያሌ ምሳሌያዊ ትርጉሞች አሉት።


ፍሬ፣ ፍሬያማ

ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ፍሬ” የሚበላ የተክል ክፍል ነው። “ፍሬያማ” ብዙ ፍሬ ያለው ማለት ነው። እነዚህ ቃሎች ምሳሌያዊ በሆነ ንግግር ውስጥ ጥቅም ላይ ይውላሉ።


ፍትወት

ፍትወት በጣም የጋለ ምኞት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ ኀጢአት ወይም ግብረ ገባዊ ካልሆነ ነገር ፍላጎት ጋር ይያያዛል።


ፍየል

ፍየል መጠነኛ ቁመት ያለው፣ ከበግ ጋር የሚመሳሰልና በዋነኛነት ደረጃ ወተትና ሥጋ ለማግኘት ሰዎች የሚያረቡት ባለ አራት እግር እንስሳ ነው። የፍየል ግልገል “ወጠጤ” ይባላል።


ፍጡር

“ፍጡር” ሰዎችንና እንስሳትን ጨምሮ እግዚአብሔር የፈጠረውን ሕያው ነገር ሁሉ ያመለክታል።


ፍጹም

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ፍጹም” የሚለው ቃል በክርስትና ሕይወታችን አስተዋዮችን በሳሎች ሆኖ መገኘትን ነው። አንዳንዴ “ፍጹም” የሚለው ቃል የተሟላና እንከን የሌለበት እስኪሆን ድረስ በክርስትና ሕይወት ማደግ ማለትም ይሆናል።